uz
Feedback
ደራሲው...∞

ደራሲው...∞

Kanalga Telegram’da o‘tish

በአጫጭርና እረዥም ልብ ወለዶች፦ ሳይኮሎጂንና ፍልስፍናን የሚኮመኩሙበት ቻናል እነሆ!

Ko'proq ko'rsatish
1 349
Obunachilar
+524 soatlar
+187 kunlar
+11530 kunlar
Postlar arxiv
ጭቃን ያደረቀችው ፀሐይ ቅቤን ታቀልጣለች አንቺ ነው ብለሽ ጭንቅላትሽ ውስጥ ስለሳልሽው ሰው ተጠያቂ አይደለሁም። ለጭቃነትሽ መድረቅ ወይም ለቅቤነትሽ መቅለጥ ተጠያቂው.. የገዛ ምናብሽ እንጂ እኔ አይደለሁም!
@lewi_derest

ጋሽ ስብሀትን የምወዳቸው በአንድ ነገር ብቻ ነው.. ከእራሳቸው የሚደብቁት ቃል የላቸውም.. ሁሉንም ቃል ለስነ-ፅሁፋቸው ይጠቀሙበታል! ማስረጃ ከፈለጋችሁ፦ ትኩሳት ገፅ 153
@lewi_derest

ፖድካስቶች ላይ "Egoን ስለ መግደል" እንደትክክል ነገር በኩራት ይሰብኩታል። Ego! መዳን ነው ያለበት እንጂ መሞት የለበትም! ትክክለኛው ሳይኮሎጂ የሚያስተምረው ይሄንን ነው! ምክንያቱም የትኛዋም "እኔ" የምንላት ጥቃቅን ነገር ሳትቀር Ego ናት... Ego ማለትኮ እኔ ማለት ነው.. የቃሉም ትርጉም እኔ ማለት ነው! Egoን የመግደል ሂደት በራሱ የunconscious መጋዘናችሁን በshadow ማጨቅ ነው የባሰ የስነ-ልቦና ቀውስ ውስጥ ይገታል! Ego ይታመማል የታመመን Ego ማከምና ማዳን ነው እንጂ Egoን መግደል የሚል ሀሳብ በጣም የተሳሳተ ሀሳብ ነው! Egoን መግደል እኮ ማንነትን (እኔነትን!) መግደል ማለት ነው! ይሄ ደግም ማንነት የለሽ! ሰዋዊነታችንን ትርጉም የሚያሳጣና የትርጉም ቀውስ ውስጥ የሚከተን ነው ! እና እባካችሁ ኢጎን መግደል በሚል ሀሳብ እንዳትያዙ!
@lewi_derest

ፖድካስቶችን የማየት ልማድ አለኝና ምን ታዘብኩ መሰላችሁ... ብዙ ፖድካስቶች ላይ Egoን ስለመግደል በስሱም በጨረፍታም ይነካኩታል... እናንተ ምን ታስባላችሁ? ኢጎአችንን መግደል አለብን በሚለው ትስማማላችሁ? ለምን?

"ማሂን የደፈራት ማን ማን ነው? የነገረኝ ሰው ቢያንስ ቅጣት ይቀየርለታል የሰረቀበት ጣቱን ብቻ ነው የምቆርጥለት... መቼስ ከመሞት ይሻላል አይደል?" አልኩኝና መናገር የሚፈልግ ካለ ተመለከትኳቸው... ከሦስቱ በስተቀር ሌሎቹ ሁሉም መናገር ፈልገው ነበር.. ገባኝ "አንተ... አንተና አንተ ናቸውሁ አይደል የደፈራችኋት? ተሳሳትኩ እንዴ?" ብዬ የቀሩትን አራቱን ተመለከትኳቸው... አራቱም እነሱ እንደሆነ በጭንቅላታቸው ንቅናቄ ገለፁልኝ... "ይቅርታ አድርጉልኝ የሚቀየረው ቅጣቱ ሳይሆን ኤሌክትሪኩን የማስርባችሁ ቦታ ነው... ከዛ በተረፈ ማናችሁም በሕይወት አትተርፉም..." ብዬ በቀሌን ጀመርኩ... የሁሉንም ሱሪ እንዲያወልቁልኝ ለሰዎቼ ነገርኳቸው... ማሂን የደፈሯትን ሦስቱን ሰዎች ቀጥታ ኤሌክትሪኩን ቆለጣቸው ላይ ቋጠርኩት... የተቀሩት ላይ ደግሞ እግራቸው ላይ... ከዛ መቆጣጠሪያውን አበራሁት... እንደዛ ቀን ደስታዬ እረ....ጅም ሁኖ አያውቅም በዛ ከተባለ አምስት ደቂቃ ነበር አሁን ግን ያለማቋረጥ ከአንድ ስአት በላይ ደስተኛ ሁኜ ነበር ምክንያቱም እንደዛ አጥንቴ ድረስ የተሰማኝ ሀዘኔታ ለረጅም ደቂቃዎች ሲካስ ነበር... ፊታቸው በላብ ተጠምቆ... ደም ስራቸው ተገታትሮ ሲታገሉ ከማየት በላይ ምን ቀረኝ... ኧረ ደግሞ የገረመኝንና በጣም ያሳቀኝን ልንገራችሁማ ሰው ሲናደድ.. ሲደነግጥ.. ሲያለቅስ ምናምን ፊቱ ቀይ ይሆናል...ከመካከላቸው ሁለቱ ጥቁር ናቸው.. የእነሱ ፉት ሳይቀር ከመሰቃየታቸው የተነሳ የቀላው.." ታሳሪው ሁላ በዚህች ንግግሬ አሽካካ.. እኔም አብሪያቸው እስቃለሁ... በቃ እስር ቤት ለእኔ ገነቴ ነው.. ማሂ ሁሌም እየመጣች ትጠይቀኛለች... በመጣች ቁጥር በኩራት የምታወራልኝ... "ያኔ በቴሌቪዥን እነዛ ውሾች እንደቋንጣ አንጠልጥለሀቸው ሲታዩ የተሰማኝ ደስታ...." ትላለች... "ምን ስትል ኤሌክትሪኩን አሰብከው ግን አንተን ይንሳኝ ማርዬ ጭንቅላት አለህ..." ትለኛለች... ትስቃለች ትጫወታለች.. ግን ሳቅና ጨዋታዋ ውስጥ ትልቅ የጎዳት ሀዘን እንዳለ ያስታውቅባታል። አንድ ቀን ተፈትቼ አብረን እንኖር ይሆናል.. ማን ያውቃል ማርገዝ የምትችልበት እድሜዋ ላይም ሊሆን ይችላል የምፈታው! ✍ሌዊ https://t.me/lewi_derest

አሳዘነችኝ ማዘኔ አጥንቴ ድረስ ዘለቀ... ስላፈቀርኳት አይደለም... ግን ይሄ አሁን እሷ ላይ ያየሁት መልክ የእኔም የሆነኛው ሕይወቴ ውስጥ የነበረ መልክ ነው!
በቀል..! ሁሉም ሰው "እንዴት ለሴት ብሎ እንዲህ ያደርጋል!" ይሉኛል... እነሱ የማይገባቸው ነገር ግን አለ!... ሴት ብዬ ወይም ለእሷ ብዬ አልነበረም ያደረኩት። አልክድም ማሂን አፈቅራታለሁ.. አውቃለሁ ወደድኩህ ወደድኩሽ ተባብለን አብረን ከሆንን... ከንፈሮቻችን መቃመስ ከጀመሩ ገና ሳምንታችን ነው! ግን እነሱ እንደሚሉት ትኩስ ፍቅር አውሮኝ አልነበረም... ማሂ አቤል የሚባል የአስራ አንድ አመት ወንድም አላት... ቤተሰቦቿን ስራዬ ብላ ቤቷ ወስዳ ነው ያስተዋወቀችኝ። ቤተሰቦቿ ሀብታም ቢሆኑም ግን ሰዋዊነታቸው አልተፋቀም... ማነህ? ምንድነህ? አላሉኝም ነበር.. ልጃችን ወዳሀለች ውደዳት ብቻ ነበር ያሉኝ... ከአቤልም ጋር በጣም ተግባብተን ነበር...  እሱም እንደእኩያው እኔም እንደእኩያዬ እስከመተያየት ነበር ቅርርባችን። ይቅርታ ቆይ አንዴ ማሂ ደወለች ላውራትና ታሪኩን እቀጥልላችኋለሁ... "ሄሎ ማሂ..." "ማ.. ማርቆስ..." እያለቀሰ ነበር "አቤልዬ ምን ሆንክ? ማሂ ምን ሁና ነው?" "ቶሎ.. ቶሎ እቤት ና" በቃ እሄን ብቻ ነበር የተናገረው ስልኩ ተዘጋ... ወደቤት ሄድኩኝ... ቤታቸውን ሰው አጥለቅልቆት ነበር... ተደናገጥኩ.. ሰዎቹን ሁሉ ገፈታትሬ ወደሳሎን ስገባ ሦስት እሬሳዎች... ተጠቅልለው ተደርድረዋል... ማሂን ነርሶቹ ወደ አንቦላንሱ እንድትገባ ይለምኗታል... "ለምን እታከማለሁ? ለምን? ለመዳን? ቤተሴቤ ሙቶ ለምን እድናለሁ? አልሄድም!" ትጮሀለች... ደርቄ ቀረሁ.. ፖሊሱ ፖሊስነቱ ትዝ ሳይለኝ ገፍትሬው እሬሳዎቹን ከተጠቀለሉበት ጥቁር ነገር ዚፑን ከፍቼ አየኋቸው... የኔ ትንሽ አቤልዬም ዓይኖቹን ጨፍኗል... አለቀስኩ... የሚወዱትን ሰው ሲያጡ ማንኛውም ሰው እንደሚያለቅሰው እየጮኹክ አለቀስኩ... ወደማሂ ስመለከትና ማሂም በለቅሶዬ ጩኸት ወደእኔ ስታይ ተገጣጠምን.. ፊቷ ላይ አለመቻል አየሁ... ብችል ኑሮ! የሚል ቁጭት... ተንደፋድፋ መታ አቀፈችኝ... "ገደሉብኝኮ! ማርዬ ቤተሶቼን ገደሉብኝ!" ድምጿ ኡፍፍፍ አልገባችሁም አጥንቶቼን ሳይቀር ሰነጣጠቃቸው... አሳዘነችኝ ማዘኔ አጥንቴ ድረስ ዘለቀ... ስላፈቀርኳት አይደለም... ግን ይሄ አሁን እሷ ላይ ያየሁት መልክ የእኔም የሆነኛው ሕይወቴ ውስጥ የነበረ መልክ ነው! የትኛው ሕይወትህ ላይ ብትሉኝ አላውቅም ግን ይሄንን መልክ የሆንኩት ያክል ተሰምቶኛል.. የሆነ ጊዜዬ ላይ እንዲህ የነበርኩ ያክል ነው ውስጤ የራደብኝ... "እነማን ናቸው?" አልኳት ያ ያለቅስ የነበረው እኔ ጠፋ ዕንባዬ ከዓይኖቼ አይደለም ከጉንጮቼ እራሱ የደረቁበት ፍጥነት ለእኔም አልገባኝም... እረጋ ብዬ ፖሊሱን ስለሁኔታው ጠየኩት... ቅድም እንደዛ በለቅሶ ሳብድ ያየኝ አልመስልህ አለው! "በቅድሚያ ግን ማህሌት ወደሆስፒታል እንድትሄድ አግባባት" "ማሂ ምን ሁናለች?" "ደፍረዋታል ተገቢውን ሕክምና ማግኘት አለባት...." አላልኳችሁም ባሂን ስለማፈቅራት አልነበረም ለበቀል የተነሳሁት.... ይታያችሁ የማፈቅራትን ሴት እንደደፈሩብኝ ስሰማ ውስጤ የጨመረም የቀነሰም ነገር አልነበረም... እንደዛ የበቀል እሳት ውስጤ የነደደው ማሂ ውስጥ ያየሁት የሆነኛው መልኬን ስለነበር ነው! ማሂ እንድትታከም አሳምኛት ወደአንቦላንሱ ገባች... ፖሊሱ ስለተፈጠረው ነገር ሲነግረኝ.. ሰፈራቸው ማሂን ወደድኩሽ እያለ የሚያስቸግራት ልጅ ነበር.. በርግጥ ለእኔም ነግሳኛለች ግን ፍቅረኛ እንደያዘች ሲያውቅና ሰፈር ውስጥም በተደጋጋሚ ከእኔ ጋር ስለሚያያት... ማስቸገሩን ትቶ ነበር.. ለካ እሱ እየተዘጋጀ ነበር... የሰፈር ጓደኞቹን ሰብስቦ... በነሱ ቤት አልታወቁም ጭንብል አድርገው የነማሂ ቤት በማታ ይገባሉ... ከዛ እናትና አባቷን ብርና ጌጣጌጥ እንዲሰጧቸው ካደረጉ ብኋላ ያ ወደድኩሽ ምናምን የሚለው ልጅ ማሂን ሊደፍራት ሲል.. እናትና አባቷ ከተንበረከኩበት ተነስተው ከሌቦቹ ጋር ግብግብ ሲጀምሩ በጩቤ ደጋግመው የወጓቸው... አቤልዬም የኔ ትንሽ ተደብቆ ለእኔ ደውሎ ሲያወራኝ አይቶት አንዱ ደንግጦ እንዳመጣለት አንገቱን ይወጋዋል... ማሂንም ደፍረው የያዙትን ይዘው ይወጣሉ... ደደብ ደደብ ናቸው! ጭንብል ያደረጉት ለጌጥ ነው እንዴ? እንዴት ዛቻቸውን አያስተካክሉም! "በሰፈራችን ሌላ መቶ ሲበላሽ እያየንማ ዝም አንልም!" ቀሽሞች ፖሊሱን ትቼው ወጣሁ... በዚህ ልክ ደደብ ከሆኑ ቢያንስ አንዲቸው ሰፈር ውስጥ ይኖራሉ ብዬ መፈለግ ስጀምር... ሁለቱ የሆነን ሰው በችኮላ አዋርተውት.. ክንብንባቸውን አስሬዬ እያስተካከሉ ወደሚቅሙበት ቤት ገቡ... ያዋሩትን ሰው ተከትዬ ሄጄ አወራሁት... "ሰላም የቅድሞቹን ልጆች የት ነው የምታውቃቸው?" አልኩት "እነቾቤ የሰፈር ልጆች እኮ ናቸው!" "አንተም የእነሱ ጀማ ነሀ?" አጠያየቄ አስደነገጠው ፋወለኛ እንደሆኑ ያውቃል እኔም ተጠያቂ መሆን እንደማይፈልግ ስለማውቅ ነው አውቄ ከእነሱ አንዱ እንደሆነ እንዳሰብኩ ያስመሠልኩት "ኧረ አይደለሁም! እኔ ደላላ ነኝ ዛሬ እስከማታ ከሰፈር ወጣ ያለና ሰው የማይበዛበት አከባቢ ቤት እንድፈልግላቸው እየነገሩኝ ነበር እዚሁ ሰፈር ስለማያቸው እንጂ ሌላ ጉዳይ የለንም" አለኝ... "እኔ እንደዛ አይነት ቤት አውቃለሁ.." ብዬው ወደቤቱ ይዤው ሄድኩኝ.. እኔ የምኖርበት አከባቢ ሰው የማይኖርበት አንድ ባዶ ግቢ ነበር... ለምን እንደሆነ እኔጃ ሰው ከገባባት እረጅም ጊዜ የሆነው ግቢ ነው... "እንደነገሩኝ ከሆነ የሚሆናቸው ይመስለኛል"አለኝና ፎቶ አንስቶ ላከላቸው... ተስገብግበው ብር ላኩለት.. ሰደላላው ለእኔ የቤቱን ኪራይ ላከልኝና እንደሚያመጣቸው ነግሮኝ ሄደ... እስኪመጡ ተደብቄ ጠበኳቸው... ጫታቸውንና ውሃ ተሸክመው መጡ... እኔም የተወሰኑ ሰዎችን አዘጋጅቼ ሌሊት ላይ ገባንና ሁሉንም አሰርናቸው... ከዚህኛው ጥግ እስከዛኛው ጥግ ሁለቱ ግድግዳዎች ላይ ተጠንካራ ብረት አሰርንና ሁሉንም አንጠለጠልናቸው ልክ እንደቋንጣ... አሁን በቀል ተጀመረ.. "እናንተ ጉልበተኞች ናችሁ አይደል በቃ ከእናንተ በላይ ማንም የለም? የሰውን ነፍስ በከንቱ የምታደክሙት ይሄንን የዱርዬ ደደብ ጭንቅላታችሁን ተማምናችሁ ነው አይደል?" ደካማ የሆነ የኤሌክትሪክ ፍሰት ያለውን ገመድ ቀድሜ አዘጋጅቼ ነበር... "እኔ ስለኤሌክትሪክ ብዙም እውቀት የለኝም ግን እነዚህ ገመዶች ከ5 እስከ 10 አፔር የሚደርሱ የኤሌክትሪክ ፍሰት አላቸው ይህ ማለት ሰውነታችሁ ላይ ተጣብቀው ከአንድ እስከ ሁለት ስአት ቢቆዩ ምን የሚፈጠር ይመስላችል?" ተራ በተራ አየኋቸው... "መጀመሪያ ንዝረቱ በማሽን ማሳጅ እየተደረጋችሁ ያክል ለስለስ ያለ ነው... እየቆየ ሲሄድ ግን ደማችሁን እየመጠጠው መላ ሰውነታችሁ እየተቃጠለ... ንዝረቲ ጭንቅላታችሁን ሰላም የሚነሳ.... መላ ሰውነታችሁ በዚህ ንዝረት ሲኦል ይገባል... ደግሞ ደስ የሚለው በአንዴ አይገድላችሁም..... ቢያን ከአንድ ስአት በላይ ያሰቃያችኋል... በተለይ ጭንቅላት መረበሹ እንዴት ደስ ይላል መሠላችሁ... ሃሃሃሃሃሃ" ሁሉም በፍርሃት ከተንጠለጠሉበት ተወራጩ... በከንቱ ይደክማሉ ቢወርዱምኮ መልሼ እሰቅላቸዋለሁ ይሄንን እንዴት አያስቡም? ለነገሩ...

አሳዘነችኝ ማዘኔ አጥንቴ ድረስ ዘለቀ... ስላፈቀርኳት አይደለም... ግን ይሄ አሁን እሷ ላይ ያየሁት መልክ የእኔም የሆነኛው ሕይወቴ ውስጥ የነበረ መልክ ነው!....Loading

ወረቀቱ ከኔ ፃፊው ሳይቸግረኝ.. ነገር ወዲያ ወዲህ ሆነና ቸገረኝ! ምን ያደርጋል ፖስታ ነጋዴ ቢያመጣው.. መገናኘት ነበር ናፍቆት የሚያወጣው! 🔥
@lewi_derest

አሁን ላይ breakup የማድረግም አዲስ relationship ውስጥ የመግባትም ፍላጎት ስለሌለኝ እንደፈለግሽ! እንድታውቂው ያክል ግን፦ ፍቅር : ይታገሣል ÷ቸርነትንም ያደርጋል ፤ ፍቅር ፡ አይቀናም ፤ ፍቅር ፡ አይመካም አይታበይም፤ የማይገባውን አያደርግም፥ የራሱንም ፡ አይፈልግም ፥ አይበሳጭም ፥ በደልን : ኣይቈጥርም ፡ ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል፡ እንጂ ስለ ዓመፃ፡ደስ አይለውም ፤ ሁሉን፤ ይታገሣል ÷ ሁሉን ያምናል ÷ ሁሉን ተስፋ፡ ያደርጋል : በሁሉ፡ይጸናል ።"
@lewi_derest

የሆነች ሴት አቀፈችኝ... "አይዞሽ የኔ ቆንጆ... አይዞሽ እኔ ነኝ... እያለች አባበለችኝና.... "አሁን ሰው ሳያየን ቶሎ እንቅበረው ተነሽ..." ብላኝ እሬሳውን በፌስታል በያዘችው ጨርቅ ጠቀላለልንና በር ላይ የቆመው መኪና ውስጥ ገተነው እሩቅ ሄድን የማለቀው ቦታ የማላቀው አባቴን ጥዬ የማላቀው ወይ ያልገባኝን ሕይወት መኖር ጀመርኩ። የሕይወት እናት እኛ ቤት ልጇን ይዛ መታ መኖር ጀመረች... ስራዋን ግን አላቆመችም.. የቤት ኪራይ ባይኖርብንም ለምግብና ለአልባሳት እንዲሁም ለአንዳንድ ነገሮች ብር ስለሚያስፈልገን እሷ አሁንም በሴተኛ አዳሪነት መስራቷን ቀጥላለች... የሆነ ቀን ታመመች.. የበሽታዋ ብዛት የጉድ ነው... በስተመጨረሻም ግን የበሽታዎቹ መብዛት መንስኤው ኤች አይ ቪ ነው ተባለ... በድጋሚ ተስፋ ቆረጥኩ... የሞት አፋፍ ላይ ሁና ለዶክተሩ "እኔን ተወኝ ልጆቼን.. ልጆቼን መርምርልኝ ዶክተር ልጆቼን አድንልኝ" ስትለው እሰማታለሁ... አለቀስኩ... ያለቀስኩት ግን እሷ አሳዝናኝ ሳይሆን "ልጆቼን" ስላለች ነው... ልጄን ብትልኩ ልክ ነበረች እሷ ግን የእውነት እናት ነበረች! ላልወለደቻትም የምትጨነቅ እናት! ይህን እያለች ሞተች... እኔ ኳን የመያዝ እድሌ ዝቅተኛ ነው ለሒዊዬ ግን ፈራሁ የማሕፀና ፍሬ ነቻ! የሕይወት እናት መሞቷ ቢያሳዝነኝም እኔም ሒዊዬም ከኤች አይቪ ነፃ መሆናችን አፅናናኝ... ሕይወትን ለማሳደግ ችግሮች ሲበዙብኝ ብዙ ጊዜ እንደእናታችን ልሰራ አስብና በሽታው አስደንግጦኝ እተወዋለሁ... ትምህርቴን ከ11ኛ ክፍል አቋርጬ የቀን ስራም ምንም እየሰራሁ ሕይወትን እንደእናትም እንደእህትም አሳደኳት... ሕይወት በስተመጨረሻም በሕይወትዬ ካሰችኝ... አሁን ሒዊዬ የኔ ጀግና አለች የተባለች ባለሀብት ነጋዴ ሁናለች... ሁለት አመት አውሮፕላን አበረረችና ይበቃኛል እነግዳለሁ አለች... አምንባታለሁ... የሚያዋጣትን እሷ ታውቅ ነበር... አሁንማ የሀገራት ነጋዴ ሁናለች! ሕይወት አንብባ እንደጨረሰች መፅሀፉን ልክ እንደወንጌል ሰባኪ ፓስተር በእጇ ወደላይ ይዛ... "ይህ መፅሐፍ እናትም እህትም ሁና ላሳደገቺኝና ለዚህ ላበቃቺኝ ለምህረትዬ መታሰቢያ እንዲሆን በማሰብ ነው በቀብሯ ቀን መፅሐፏን የማስመርቀው!" አለችና እንባ ተናንቋት ትንሽ አልቅሳ... "ርዕሱ እረዘመ አይደል?(ከመፅሐፉ ላይ ርዕሱን እንደማንበብ አደረጋት) "በውሸተኛ ታሪክ ላይ የተመሠረተ የእህቴ ባዮግራፊ!" ይህንን ርዕስ የመረጥኩት በእናቴ በእህቴና በእኔ ሕይወት ውስጥ ብዙ ልክ ያልሆኑና ስህተት የሆኑ አጋጣሚዎች በተደጋጋሚ ስለተከሰቱ ነው በተለይ ደግሞ እህቴን ወንጀለኛ የሚያደርጋት ድርጊት ስላለ እሷን ላለመውቀስ ስል ነው በውሸተኛ የሚለውን ቃል መጠቀም የፈለኩት!" አለችና ሕይወት ከመድረኩ ወረደች... እንዲህ ያለ ቀብር ታይቶ ስለማይታወቅ ሚዲያዎች ተቀባበሉት መፅሐፉም በብዛት ተሸጠ.... ስድስተኛ ዙር የታተመውን መፅሐፍ ለአንባቢያን በአርባዋ ቀን በመቃብር ስፍራዋ ይፋ እንደምታደርግ ተናገረች... መፅሐፉን ያነበቡትና መፅሐፉ ያጓጓቸው ሁሉ በመቃብሯ ታደሙ... በስተመጨረሻም ያቺ ጡት ሳትጥል እናቷን ልታጣ የነበረች ሕፃን ዛሬ ታሪክ ሰራች ሕይወቷን የታደገችላትን ሴት ቀብር ያማረ አደረገችው ሀገር የሚያከብራትና የሚያደንቃት ሴት አደረገቻት... እንዳውም "የምሕረት መታሰቢያ" የሚሉ የንግድና የሶሻል ሚዲያ ስሞች ተበራከቱ...
✍ሌዊ
https://t.me/lewi_derest

አትሂጂ ብያት ነበር... ብቻዬን አልቅር ብዬ ነበር... ሳለቅስስ አላደርኩም?... ትራሴ የእንባ ቅቤ ሲጠጣ ያደረባቸው ሌሊቶችስ የዋዛ ነበሩ?
ፍርሃት! ለምን እንደሆነ የማይገቡኝ ግን ደግሞ ስሜቶቼን የሚያምሱብኝ ብዙ ጉዳዮች ነበሩኝ። የጨበጥኳቸው ሰዎች እጃቸው ሲላላብኝ እንዳይለቁኝ በመፍራት ሲቃ ተውጬ አውቃለሁ! ፍርሃት ከውጭ ሲታይ ደካማነት ይመስለናል አይደል? ፍርሃትኮ ብርቱ ነው! ለተጋፈጠው  ሲኦል ነው! በፍርሃት ቁንጣን ይዞኝ ያውቃል! ቀልድ አይደለም ፍርሃቱን እንዲጋፈጥ የተገደደ ሰው የፍርሃትን ቁንጣን ያውቀዋል... ሁለት ጉርሻ ጎርሼ.. ያ የፍርሃት ስሜት ያለማቋረጥ ውስጤን ሲያምሰው... ሠላሳ ጊዜ ሽንትቤት መመላለስ ይቃጣኛልኮ... እግሮቼ መቆም አቅቷቸው ሲብረከረኩብኝ... አቅም ሳጣ... መቆም መቀመጥ ሲሰለቸኝ... ብዙ ብዙ ስሆን እራሴን አውቀዋለሁ። ጨብጫቸው ከነበሩት እጆች ውጪ እራሴን ሳየው ጠላሁት... ግን በቃ ሕይወት እቺ ናት... ለነገ እንጂ ለእኔ ለምህረት ፍላጎት ግድ የላትም! ስለዛሬ እንጂ ስለትናቱ አታስብልኝም! ከትናንት ፍርሃቴ ጋር ዛሬን እንድጋፈጥ ታነጋብኛለች... መሽቶ በነጋ ቁጥር ከትናቴ መራቄ እያደር ፍርሃቴን ይጨምርብኛል... እቺ ክፉ ሕይወት ያለመራራት ከፍርሃቴ ጋር እንድጋፈጥ አስገደደችኝ... ለምን እንደምፈራ አላውቅም ግን ቤታችን የመጣ እንግዳ እንኳን ሁለት ወይም ሦስት ቀን አድሮ ሲሄድ... መፍራት እጀምራለሁ... ባልሄደ እላለሁ... አትሂጂ ብያት ነበር... ብቻዬን አልቅር ብዬ ነበር... ሳለቅስስ አላደርኩም?... ትራሴ የእንባ ቅቤ ሲጠጣ ያደረባቸው ሌሊቶችስ የዋዛ ነበሩ? ግን ፍርሃት በእንባ አይወጣም! አባቴ እናቴ ከሞተች ብኋላም ያው እራሱ አባቴ ነው! ሀዘን ይለውጠዋል ብዬ ነበር... ሠልስት.. ማግስት... ምናምን የሚባሉ የለቅሶ ቤቶች ወግ ካለቀ ብኋላ አባቴ ሴት ይዞ መምጣት ጀመረ... ሴት ማምጣቱ አልከፋኝም ግን የሚመጡትንም ሴቶች ልክ እንደእናቴ እየደበደበ ያስለቅሳቸው ነበር... አንዳንዶቹ ግን እያለቀሱም እየተሳደቡም ትተውለት ይወጣሉ.. ልክ እናቴ ብታደርግ ብዬ እንደምመኘው... ሌሎቹ ግን ይለምኑታል የዛኔ የሚሰማኝ የእነሱ ልመናና ለቅሶ ሳይሆን የእናቴ ነው የሚያቃጭልብኝ... አሁንም እናቴ እዛ ውስጥ እየተደበደበች ይመስለኛል... "እኔስ አንዴ ሙቼልህ ትገላገላታለህ እቺ አንድ ፍሬ ልጅ ግን አታሳዝንህም? እሷ ፊት...." "ያዘንሽላት አትመስይም?" በርግጫ ይላታል ታቃስታለች እያቃሰተች... "ላንድ ልቼ ልኑርበት እባክህ ተወኝ.. በሴት አምላክ በወለደችህ..." እንዲህ እየለመነችው እንኳን እግሩ ስር ናት ለመሸሽ አትሞክርም። እቺኛዋ ሴት ምንም ብላ ትለምነው ምንም ግን የሚሰማኝ ይሄ የእናቴ ድምፅ ነው... ተነስቼ "እናቴን ተዋት!" ልለው ይቃጣኛል "ፖሊስ ጠርቼ አሳስርሀለሁ" ምናምን ብዬ ላስፈራራው... ግን ፍርሃቴ ያሸንፈኛል... እኔንም እዛው... በቃ ለእናቴም በፍርሀቴም አሁን አሁን ደግሞ መኝታቤት ለምትቀጠቀጠዋ ሴት ሁላ ጭምር አለቅሳለሁ... እንደለመደው የዛሬም አንዷን ይዞ መጣ.. እንደለመድኩት ማጥናቴን ትቼ ደብተርና መፅሐፎቼ ፍራሹ ላይ እንደተበታተኑ ትቻቸው ብርድ ልብሱን ገልጬ ተጠቀለልኩ ፍራሹ ላይ የነበሩት መፅሐፎች በደዚህና ወደዛ ሲወድቁ በብርድልብሱ ይታወቀኛል እኔ ግን በፍርሃቴ ውስጥ ሁኜ ግድም አልሰጡኝም... ሁሌም በብርድልብሴ ተጠቅልዬ "እባክህ ፈጣሪዬ እንዳይመታት እባክህ" ብዬ እፀልያለሁ አባቴ ግን እግዜርም የማያስቆመው ሰይጣን ነው መሰለኝ ይህ ፀሎቴ ሰምሮ አያውቅም... ጀመረው ደግሞ "ጯ" የሚል የጥፊ ድምፅ... ጥፍውን አስከትላ.. "እናትህ አፈር የበላች! ምናባህ ሁነህ ነው የምትመታኝ" ጮኸችበት በጥፊ የቀለጠ ፊቷን እያሻሸች ይመስለኛል... በቃ ዛሬ እሬሳ ላይ ነው አልኩኝ ፍርሃቴ ጨመረ... በእርግጫ ሲጥላትና ከሆነ ነገር ጋር ተጋጭታ ስትወድቅ እሰማለሁ... በቃ ገደላት... ሌላ ፍርሃት... "እናትህ ትበዳ ውሻ የውሻ ልጅ..." ከመኝታ ቤቱ እየሮጠች ወጣች ማንኪያዎች ሲንኳኩ እሰማለሁ... አሁን ይበልጥጥጥጥ ፈራሁ... በብርድልብሴ አጮልቄ አየኋት... እንደፈራሁት ከመሳቢያው ቢላ አወጣችና "አንጀትህን እዘረግፍልሀለሁ እኔ ሊሊ እፈራህ መስሎሀል" እያለች ወደመኝታ ቤቱ እሮጠች... እሱ ወደሷ ሲወጣ እሷ ወደውስጥ ስትገባ በር ላይ ተገናኙ የወጋችው መስሎኝ ካቅሜ በላይ የሆነው ፍርሃቴ ሳላውቀው በጩኸት አሸነፈኝ.... "ዋይይይይይይይ" ደንግጣ ዞረች እንዴት እንደተቀመጥኩ አላውቅም ግን ከጥቅልሌ ወጥቼ ፍራሹ ላይ ቁጭ ብዬ አፈጥባታለሁ... "ለዚህች እንኳን አታዝንም? ቆሻሻ!" ብላው ቢላውን ከእኔ እንደመደበቅ አድርጋ ጠረጴዛው ላይ አስቀምጣ ወታ ሄደች። የዛን ቀን አባቴ ለብቻው ሲጮህ.. እቃ ሲወረውር ሲሰብር ቆይቶ ተመልሶ ወጣ... በዛው አደረ ዋለ.. ማታ እንደለመደው ሴት ይዞ መጣ... እንደገና ለቅሶ ዋይታ... ከዛች ቀን ብኋላ በእያንዳንዷ ሴት ለቅሶ የእናቴ ድምፅ ስለሚሰማኝ ያቺን ቢላ አስባታለሁ... አንዳንዴማ ከመሳቢያው አውጥቻት ሁላ የመኝታቤቱ በር ላይ ስደርስ በፍርሀት እቼ አልይዝ ብሎኝ ተመልሼ ተጠቅልዬ እዬዬ ብዬ አልቅሻለሁ መንገድ ላይ ፖሊስ ሳይ ተናግሬበት ላሳስረው እንዴ? ብዬ ፈጥኜ እራመድና ፖሊሱ አጠገብ ስደርስ አንዳች የማላውቀው ፍርሃት አርበትብቶኝ ደርቄ እንደቆምኩ እርቆኝ ይሄዳል። "እባክህ ልጅ አለችኝ ትንሽዬ ትንሽዬ... እባክት ተወኝ... ገና ጡት አልጣለችም ለልጄ ስትል..." እሱናቴ ዝም ብሎ ይረግጣታል... ደግሞኮ የሚገርመኝ እነሱ እንጂ እሱ አንዲት ቃል አይናገራቸውም.. እናቴን ብቻ ነበር በቃልም በዱላም የሚደበድባት "ኧረ በሕፃን ነፍስ ይዤሀለሁ... እሷን ላሳድግ ብዬ እንጂ ደልቶኝኮ አልወጣሁም..."አይሰማትም እምደማይሰማት ሲገባት እኔን ወደማይሰማኝ ፈጣሪ ትፀልይ ጀመር... "ሕይወትዬ የኔ ልጅ አልደረስኩልሽም! እህህህ የኔ ልጅ ፈጣሪ ይሁንሽ... ልጄን አደራ ፈጣሪዬ ልጄን አደራ... አንተ ጥላ ከለላ ሁናት... ሒዊዬ የኔ ልጅ...." አሁን አልቻልኩም... ቆይ ግን ፈጣሪ ፀሎት በዝቶበት ነው የእኛን የማይሰማን? እሱ ሁሉን የሚያይ የሚሰማ ነው አላሉንም ነበር? ጠበኩኝ ግን ፈጣሪ ከአባቴ ሊጠብቃት አልቻለም... እንግዲያውስ እኔ እጠብቃታለሁ ብዬ ከመሳቢያው ቢላውን አወጣሁ... እየፈራሁ ነው ግን በተመሳሳይ ጊዜ ደግሞ ተናድጃለሁ... የፍርሃትና የቁጣ ስሜት ሲዋሀዱ... በቃ የመጨረሻ አውሬ ያደርጋሉ.. የፈሪ ዱላ ይሉታል ፍርሃት ያልገባቸው... ብቻ ዘልዬ አባቴ ላይ ተከመርኩበት ለምን ያክል ጊዜ እንደሆነ አላውቅም ብቻ በደመነፍስ ደጋግሜ ወጋሁት... ልጅቷ... "ደረስክልኝ ፈጣሪዬ! ልጄን ልጄ ጋር ልሩጥ...." ትታኝ ወጣች... በደም እንደተጨማለኩ የገባኝ አሁን ነው... ደነገጥኩ... ፍርሃት ከውስጤ ንቅል ብሎ ጠፋ ግን ድንጋጤው አለቅሽ ብሎኝ ነበር.... ለምን ያክል ስአት ከነደሜ ከአባቴ እሬሳ አጠገብ እንደተዘረፈጥኩ በውሉ አላቀውም... በሩ ተከፍቶ የሆነ ሰው ገባ ደነገጥኩ ያ ፍርሃቴ ተመልሶ መጣ... መላ ሰውነቴ ተንዘፈዘፈብኝ... "የኔ ጥፋት አይደለም.. የኔ ጥፋት አይደለም ሊገላት ነበር አዎ ደሞኮ ሕፃን ልጅ አላት የምታጠባት... አዎ የኔ ጥፋት አይደለም!" እንዳመጣልኝ መቀባጠር ጀመርኩ...

አትሂጂ ብዬ ነበር... ብቻዬን አልቅር ብዬ ነበር... ሳለቅስስ አላደርኩም?... ትራሴ የእንባ ቅቤ ሲጠጣ ያደረባቸው ሌሊቶችስ የዋዛ ነበሩ? ....loading

ይሄ ቻናል ይለያል ነው የምላችሁ✌ https://t.me/Evangadi21

photo content
+4

ለፕሮግራም በግልና በግሩፕ መለበስ የሚችሉ ምርጥ ቱታዎቼን እኛጋር በተመጣጣኝ ዋጋ ያገኛሉ ይዘዙን ያሉበት ድረስ እናመጣለን... 0944240243 DM👉 telegram
+9
ለፕሮግራም በግልና በግሩፕ መለበስ የሚችሉ ምርጥ ቱታዎቼን እኛጋር በተመጣጣኝ ዋጋ ያገኛሉ ይዘዙን ያሉበት ድረስ እናመጣለን... 0944240243 DM👉 telegram

አሁን ሲገባኝ ግን ከደመነፍሴ ነፃነት በፊት ሊታከሙ የሚገቡ ነገሮች ነበሩኝ.. ያ ቴራፒስቴ ግን ዘሎ ዋናው ላይ ጉብ አለና አውሬዬን ከነበሽታው ነፃ አደረገው! ስነ-ልቦና የሚታከመው እንደታማሚው ሁኔታ እንጂ ቴራፒስቱ እንደሸመደደው እውቀት አልነበረም ለካ! ✍ሌዊ https://t.me/lewi_derest

ያኔ ንብረቴ የተቃጠለ ቀን ያኔ መኝታ ቤት ያየሁትን ያየሁ ቀን ያኔ ነበርኮ ፂሜን መቆረጥ ያቆምኩት ለልብሴም ለፀጉሬም ግድ ያልነበረኝ.. ሽታው የሚቀፈኝን ሲጋራ ከመጠጥ ጋር የተወዳጀሁትኮ ያኔ ነበር... ጥቁር ልብስ ለብሼ አይኔ ደም መስሎና ፊቴ ፈገግታን ካየ አመታት ከማስቆጠሩ የተነሳ ከፊቴ ላይ ግልፅ ሀዘን እየተነበበ ከሰዎች ብር እየቀፈልኩ እነሱም "እምፅ" አስርም ሀያም ሲሰጡኝ እሩጬ ሲጋራ ስገዛ እንዲሁ እኖራለሁ... አልገባህ ያለኝ ግን የእሷ እንደዚህ መሆን ነው... ፀፀት ነው መሰለኝ.. እየቆየች እሷም እኔ ወደሆንኩት መሆን ገባች... ቆንጆ ቤት ውስጥ የምንኖር ሁለት እብዶች ተባልን... የተኮራረፉ እብዶችም አሉን... ጓደኛዬ ጠላቴ መሆኑንን እየገረመኝኮ አንድ ሺህ አንድ ጊዜ ነግሪያት ነበር... በዚህ ልክ ይሄዳል ብዬ ባልጠብቅም ግን ጠላቴ እንደሆነ ነግሪያት ነበርኮ... ጠላቴ እንደሆነ እያወቀች... ይሄማ የስሜት መሳሳት ብቻ አልነበረም... ውስጡ ጥላቻ.. የሆነች ስስ በቀል ቢጤም ነበረችበት እንጂማ ጠላቴ እንደሆነ እያወቀች ሰው መሆኗ አያሳስታትም! .......................................... ብዙ ሰዎች ልጅነታቸውን ይናፍቃሉ ልጅነት ግን ይናፍቃል ወይ? እናቴ እኔን ስትወልድ ባጋጠማት የሕክምና ስህተት ምክንያት ድጋሚ መውለድ እንደማትችል ተነገራቸው... ለእናትና ለአባቴ የመጀመሪያም የመጨረሻም ልጅ እኔ ስለሆንኩ አይከለክሉኝም እንደፈለኩ እጫወታለሁ.. ከልጆች ጋር ስጣላ እንኳን አባቴ ስለሚቆጣልኝና ስለሚፈሩት ማንም ልጅ ከእኔ ጋር መጣላት አይፈልግም ነበር። መሳቅ መጫወት ብቻ ነበር የማውቀው! ለመጀመሪያ ጊዜ ውሴን ቅር ያለው መቼ እንደሆነ ታውቃላችሁ? በአስር አመቴ ነበር.... እነመኮ ሰፈራችን የሚያምር ቤት ሰርተው የገቡ ቀን... ቤታቸው ከእኛ የበለጠ እንደሚያምር ሳይና መኮ ብዙ ደስ የሚሉ መጫዎቻዎች ስላሉት አብረውኝ የሚጫወቱት ሁሉ ትተውኝ እሱጋር የሄዱ ቀን! መኮ አባቴ ፊት ገፍትሮ ሲያስወድቀኝና ሳለቅስ አባቴ እሱን ሳይቆጣው እኔን ሲያባብል አባቴ የመኮ አባት መኪና ስላለው እንዳይገጨው ፈርቶ ይመስለኝ ነበር... ጭራሽ እኛ ትምህርት ቤት ገባ... ጭራሽ እኛ ክፍል ሆነ... ለጥያቄና መልስ ውድድር አስተማሪዋ "አብርሽ ይቸኩላል መኮንን ይወዳደር" አለች... ከፋኝ! ግን ሲያሸንፍ ክፍላቸው ያልሆኑት የሰፈር ጓደኞቻችን ሲጨፍሩ አብሬ ጨፈርኩ።   ሦስተኛ ክፍልኮ 1ኛ ነበር የወጣሁት.... አሁን ግን 2ኛ ሆንኩኝ ለምን? መኮ 1ኛ ስለወጣ! በእያንዳንዱ ነገር ውስጤ ቅር ይለው ነበር ግን ሁሉም ጓደኞቻችን ቅሬታ አላይባቸውም ሲስቁና ሲጫወቱ እኔም ከእነሱ ጋር ያንኑ አደርጋለሁ... ያ ቅር ቅር ክፍት ክፍት የሚለኝ ስሜት ያስፈራኝ ስለነበር በመኮ ለመደሰትና ለእሱ በማሽቃበጥ የማመልጠው ይመስለኝ ነበር... ከሌሎቹ ይልቅ እኔ በጣም ቀረብኩት! እሱ እንደሚለው ምርጡ ጓደኛው ነኝ እውነታው ግን እንደዛ የምቀርበው ወድጄው ሳይሆን ከፍርሃቴ ለመሸሽ ነበር... ይሄ ነገሬ ሳላውቀው አብሮኝ አደገና በውስጤ የምቀናበት በውጪ ግን ቅን የምሆንለት ሰው ሆንኩኝ... ያኔ ልጅ እያለሁ በጨዋታ መሀልና በጓደኞቼ ወይም ለጓደኞቼ ይሰሙኝ የነበሩት ስሜቶች አዋቂነቴን ይነጥቁኛል ብዬ አስቤያቸው አላውቅም ነበር! ትልቅ ሰው ሆንኩና ፍርሃቴ ተቀየረ... ክብር የሌለኝ ሁሌም የመኮ ወሬ አመላላሽ እንጂ የእኔ የምለው ነገር የሌለኝ ሰው መሆን አስፈራኝ... በጣም ተጨነኩና የስነ-ልቦና ባለሞያ አማከርኩኝ! Shadow work ያስፈልግሀል አለኝ!... ጓደኛህን እንቢ ማለት ጀምር አለኝ... ሆን ብለህ የእሱን ነገር አበላሽበት! የዛኔ በልጅነትህ ትፈራው የነበረው ነገር እንደማይፈጠር ስትረዳ የዛኔ shadowህ አጥር አይሆንብህም አለኝ። ያንኑ አደረኩኝ... የሻዶዬ አጥር ሲፈርስ ግን የተፈታው አውሬ ነበር... የሆነ የማላውቀው አንዳንዴማ እኔ እራሴ ሳስበው የሚያስፈራኝ የአውሬ ማንነት ኖረኝ... ምን ያመጣል ብዬ ፊት ለፊቱ የማደርገውን የማደርግ አውሬ ወጣኝ... አንዲት የሳይኮሎጂን ፅንሰ-ሐሳብ ስለተረዱ ብቻ ሰዎችን ማከም የሚችሉ የሚመስላቸው ደንቆሮዎች እንደእኔ አይነት አውሬን እየፈቱ ወደሕዝቡ ይለቃሉ! ለመኮ ደወልኩለትና ላጠፋሁበት ነገር ይቅርታ ልጠይቀው እንደምፈልግ ነግሬው ለምሳ ተቀጣጠርን... ምሳ አብረን ከበላን ብኋላ እንዳልተቀየመኝና ወደራሴ ተመልሼ ይህንን በማድረጌ እንዳውም እንደተደሰተ ነገረኝ... እኔ ግን ቆንጆ ሴራ ነበረችኝ... ሌሊት ላይ ሞያሌ አከባቢ የላኳቸው ሰዎች ደወሉልኝና ሹፌሩን እንዳስቆሙትና ምን እንዲያደርጉ እንደምፈልግ ጠየቁኝ... "ስልኩን ተቀበሉትና በእሱ ስልክ ወደ እኔ ደውሉ" አልኳቸው እንዳልኳቸው አደረጉ... "ከዛ Add call በልና የምነግርህ ቁጥር ላይ ደውል" አልኩት አጋቹን። መኮ የሚያስበው እኔ ሞያሌ ከሹፌሩ ጋር ሁኜ በሹፌሩ ስልክ እንዳወራሁት ነው... እሱን ለመበቀል ምሳ ከእሱ ጋር በልቼ... ክንፍ አብቅዬም ቢሆን ሞያሌ መድረስ እንደምችል እንዲያውቅ ነው! ከዛ እየቀለድኩና እየሳኩኝ ባሰብኩት ልክ ማሰብ ሲጀምር ንብረቱን አመድ አደረኩለት... በዋስትናም የወደመበትን ንብረት እንዳያገኝ እንዳውም እሱ ተጠያቂ እንዲሆን የእሱ ጠላቶች እንደዚህ እንዳደረጉት የሚያሳውቅ ፅሁፍና ለመኮ ደግሞ ልጅነቴን ምን ያክል እንዳከሸፈው ለማሳየት ያስለመድኩትን የሕፃን ልጅ ፎቶ አስቀመጥኩለት። እቃው ስንት ስአት ተጭኖ እንደሚወጣና የማን እቃ እንደሆነ መረጃ የሰጠኝ ልጅ.. ለመኮ የክስ ደብዳቤ እንደተላከለት ሲነግረኝ... በሩ አከባቢ ጠብቄ ለሞተረኛው ጓደኛው እንደሆንኩና እሱጋር እየገባሁ እንደሆነ ነግሬው ወረቀቱን ተቀበልኩትና በሩን ማንኳኳት ጀመርኩ... አንዴ እዚህ አንዴ ሞያሌ ደግሞ እዚህ የምገኝ መንፈስ እንደሆንኩ እንዲያስብ የክስ ደብዳቤውን በእጄ ለእጂ ልሰጠው ፈልጌ ነበር ግን ሚስቱ ነበረች በሩን የከፈተችው! ስታየኝ ደነገጠች... መኮ እንደሌለ ስትነግረኝ የክስ ደብዳቤውን ፊቷ ላይ ወርውሬባት ልሄድ ስል እራሷን ስታ ዘደቀች... አውሬዬ ከእንቅልፉ አይነቃም! አቅፌ ወደመኝታ ቤት ወሰድኳትና ልብሷን አወላልቄ የማደርገውን እያደረኳት እያለ መኮ በሩን በርግዶት ገባ... እውነት ለመናገር እንዲህ እንዲያየኝ አልፈለኩም ነበር... አለ አይደል በቃ ሚስትህንኮ ብዬ ፎቶ ማሳየት ብቻ ነበር የፈለኩት... ግን ይህን ሰው እኔ ብቻ ሳልሆን ሕይወትም ልትቀጣው ፈለገች መሰለኝ በዓይኑ አየኝ... የንብረቱ ነገር አቅም እንዳሳጣው ገባኝ... ዘና ብዬ ልብሴን ለባበስኩና ከርዝዞ ወደተቀመጠበት ተጠግቼ.. "በስምህ ልጅ ቢኖርህ እንኳን DNAውን ወደእኔ እስከመቀየር እበቀልሀለሁ!" አልኩትና በእርካታ ትቼው ወጣሁ... ከዛ ብኋላ መኮ ሰውም አልሆነም ቆሻሻ በማይጣልበት ልክ እራሱን ጣለ እየቆየችም ከአንድ ወንዝ አይደል ብሂሉስ ሚስቱም እንደሱ ሁና አረፈችው... አልፎ አልፎ አያቸዋለሁ አሁንም እንደተኳረፉ ነው! ለምን እንደሆነ አላውቅም ከሰብአዊነት ይልቅ የእሱ ከእኔ በታች መሆን ነበር የሚሰማኝ ይሄ ደግሞ ያረካኝ ነበር! ስነ-ልቦናን በፎርሙላ አታክመውም! እንደታማሚው ስሜትና ሀሳብ እንጂ እንደባለሞያው እውቀት የሚታከም የስነ-ልቦና ቀውስ የለም!

ያኔ ልጅ እያለሁ በጨዋታ መሀልና በጓደኞቼ ወይም ለጓደኞቼ ይሰሙኝ የነበሩት ስሜቶች አዋቂነቴን ይነጥቁኛል ብዬ አስቤያቸው አላውቅም ነበር
ልጅነት ይናፍቃል ወይ? መኮ ሌሊት ስልክ ሲያወራ በሰመመን ሰምቼው ነበር... አንድ ሁለቴም ነቅጄ አማትቤ ነው መልሼ የተኛሁት... እንቅልፍ ሳይተኛ እንዳደረ ገብቶኛል ጭራሽ ገና ወገግ ከማለቱ ተነስቶ ወጣ.... እሱ እንደወጣ ከደቂቃዎች ብኋላ በር ተንኳኳ... ሲጨናነቅ ስላደረ የውጩን በር ቁልፍ እረስቶት ነው ብዬ አሰብኩ እንጂ እሱማ በር አኳኩቶ አያውቅም ነበራ... በሩን ስከፍከተው አብርሃም ነው... የሆነ ወቅት ከመኮ ጋር እልል ያሉ ጓደኛሞች ነበሩ.. ባልተቤቴ እንደነገረኝ ከሆነ ከመሬት ተነስቶ ጠላት እንደሆነበትና በስራው ላይ ትናንሽ ነገሮችን በግልፅ እያበላሸበት እንደሆነ ነግሮኛል። ይቅርታ ሊጠይቀውና ምን እንዳስቀየመው ሲጠይቀው አይናገርም ግን የሆነ ጥፋት ካጠፋበት ብኋላ የሆነ ነገር ተከልክሎ ያዘነ ሕፃልጅ ፎቶ ያስቀምጥለታል ወይም ይልክለታል..." በቃ አሁንም ችግር ፈጥሮበት ነው ብዬ አሰብኩ..... "ይሄንን ወረቀት ለባልሽ ስጪው..."ብሎ ፊቴ ላይ ወረወረው... እራሴን ያዞረኝ ጀመር... ሰሞኑን ምን ሁኜ እንደሆነ አላውቅም እያዞረ ይጥለኛል... ከዛሬ ነገ ለመኮ እነግረዋለሁ.. ሆስፒታል እሄዳለሁ እያልኩ.... ዛሬም... የውጭ በር ላይ የተጨፈኑ ዓይኖቼ መኝታ ቤት ተገለጡ... ከዛች ቀን ብኋላ ግን ሕይወቴ ሲኦል ነበረች... አንዳንዴማ "አባቴ ይሙት ሙቻለሁ.. ያኔ በር ላይ እራሴን ስቼ እንደወደኩ አልተነሳሁም ሙቻለሁ!" እላለሁ ምክንያቱም ከዛች መውደቅ ብኋላ ምንም የማላቃቸው ነገሮች ጥፋተኛ አድርገውኛል... ባለቤቴ ፊት ሲነሳኝ... እየሰከረ ሲመጣ.. እራሱን ሲጥል ስለከሰረ ብቻ መስሎኝ ነበር ላፅናናው ስሞክር... ጥንብዝ ብሎ ሰክሮ ይመጣና "ዞርበይ አንቺ ሸርሙጣ!" ይለኛል። ይሁን ኪሳራው ከስካሩ ጋር ይሁን ሰው አይደል! እል ነበር ሲደጋገምብኝ ግን አቃተኝ... እንደሰከረ አውቃለሁ.. ግን የእውነት እንዲያወራኝ ፈልጌ ነበር... እንደለመደው ሸርሙጣ አለኝ በጥፊ አላስኩት.... "ምቺኝ.. ምቺኝኝኝ... ያ ውሽማሽ እንዳልነበርኩ አድርጎኝ የለ... ጨርሺለት ጨርሺለት ይሄው..." እየተኮላተፈ እጁን ዘርግቶ ግደይኝ አለኝ... ገመትኩ ውሽማሽ? ጨርሺለት? በኪሳራው ብቻማ አይደለም... ጠዋት ባልሰከረበት ልጠይቀው ሄድኩኝ... የሚተኛው የልጆቻችን የላኝ ክፍል ውስጥ ነው መኝታ ቤቱን ዝር ብሎበት አያውቅም። "ውጪልኝ!" ብቻ ነው ያለኝ... እኔ ግን ማወቅ ፈልጌ ነበርና "አልወጣም" አልኩትና እንዲነግረኝ  ጠየኩት... በደህና ጥፊ አጋጨኝና.. "የሰማ ያየን ይጠይቃል.. ያየ ያደረገውን ያጠይቃል.. አድራጊው ግን የመጠየቅ መብት የለውም! ውሻ!" ብሎኝ ወጣ... እኔ ግን ከጥፊው በላይ የክፍሎ መሽተት የፀጉሩ መቆሸሽ... የልብሱ መቀዳደደ ውስጤን እረበሸው... ምን እንዳደረኩት አላውቅም ለምን እንደዚህ እንደሚሆንብኝ አልገባኝም... ግን የሆነ የበደልኩት የጎዳሁት ነገር እንዳለ ይሰማኛል.. ይቅርታውን ለማግኘት ስብሰለሰል ፀፀት ሆድ አባሰኝና ሳላውቀው እኔም እንደሱ ሁኜው አረፍኩት... ነፍሴን በፀፀት ስጋዬን በሲጃራና በመጠጥ መላጥ ጀመርኩ... ................................................. ለምን እንደሆነ አላውቅም ግን አብሮ አደጌ ሀይለኛ ጠላቴ ሁኖብኛል... በፊት በፊት እየሳቀ እያስመሰለ ነበር ነገሮቼን ሲያበላሽ የነበረው.. አብሮኝ የተጨነቀ እየመሰለ ለብቻው በደስታ ሲዘል የነበረው... አሁን ግን ጥላቻውን በግልፅ አድርጎታል! የሆነ ቀን ሌሊት ስምንት ስአት አከባቢ ስልክ ተደወለልኝ... "ሄሎ.." አልቁኝ በእንቅልፍ በተጨናበሰ ድምፅ "መኮ ጓደኛዬ ሃሃሃሃሃሃ..." ግራ ገብቶኝ ስልኩን ከጆሮዬ አንስቼ አየሁት... አልተሳሳትኩም... የሹፌሩ እንጂ የጓደኛዬ ስልክ አልነበረም... ግራ መጋባቴ ጨመረ እንዴ ምሳኮ አብረን ነው የበላነው... እንዴት ከሹፌሩ ጋር አብሮ እንደሆነ አልገባህ አለኝ... "አብርሽ?" አልኩት "በጣም የምትወደኝ ጓደኛህ ነኛ?" አለኝ ሰክሮም መሰለኝ... "አዎ አብርሽ ግን ምን ሁነህ ነው በዚህ ስአት?" "እኔ ግን በጣም ነው የምጠላህ..." ሰክሮ እንዳልሆነ አውቃለሁ.. እሱ ሲሰክር እንዲህ አይሆንም... እንኳን የሚጠላውን ሰው ቀርቶ ያደናቀፈውን ዲንጋይ እኳን ተደፍቶ እየሳመ ይቅርታ የሚጠይቅ የይቅርታ አብሾ ያለበት ሰው ነው! "ለምን?" "ሃሃሃሃ ለሱ ጊዜው እረፍዷል አሁን ማለት ያለብህ እንደምትጠላኝ በምን ታሳየኛለህ ነው... በለኛ በለኝ! በምን እንደማሳይህ ታውቃለህ?" "አብርሽ ቆይ...." የሆነ ትልቅ ፍንዳታ ና የሆነ የሚጮህ ሰው ጩኸቱን እንኳን ሳይጨርስ ስልኩ ተቋረጠ...ደጋግሜ ብደውልም ስልኩ አይሰራም አብርሽም ስልክ አያነሳም እንቅልፍ እንቢ ብሎኝ አደረ... በጠዋት ተነስቼ ወደ አብርሽ ቤት ሄድኩኝ... ሚስቱ አሁን ነውኮ የወጣው አለችኝ... "እርግጠኛ ነሽ? እቤት ነበር?" "አዎ በጠዋት የምሄድበት አለኝ ብሎ በጊዜ ነው እንዳውም ትቶኝ የተኛው" የበለጠ ግራ ተጋባሁ... ወደቤቴ እየተመለስኩ ስልክ ተደወለልኝ... "አዎ ነኝ!" በኮንቲነር እቃ ያስጫንኩበት ድርጅት ነበር "አዝናለሁ ያስጫንከው እቃ ከነሹፌሩ ተቃጥሏል!" አለኝ ድርቅ ብዬ ቀረሁ.. "ስለዚህ?" አልኩኝ እቃው እጄ እስካልገባ ዋስትና እንዳለኝ ሳስታውስ "አቶ መኮንን ያስጫኑት እቃን ከጭነት መኪናውና ከሹፌሩ ጋር እንዲቃጠል ያደረጉት ሽፍታዎች ሳይሆኑ የእርስዎ ጠላቶች ናቸው... ስለዚህ ዋስትና ሊሉ ከሆነ እንዳውም የነፍስና የንብረት ካሳ ድርጅቱ በሕግ ይጠይቆዎታል!" ብሎኝ እርፍ "ምን ማለት ነው እኔ ጠላት የለኝም... ደግሞ በምን አወቃችሁ?" ንብረቱ ከተቃጠለበት በግምት አስር አስራ ምስት ሜትር ከፊትም ከኋላም እራቅ ብሎ... "መኮንን ሆይ ጠላቶችህ ተበቅለውሀል" የሚል ፅሁፍ ከሕፃን ልጅ ምስል ጋር አስፓልቱ ላይ በቀይ ቀለም ተፅፏል ፎቶዎቹን ኢሜይል አድርገንሎታል... የፍታብሔር ክስ ደብዳቤም ወደቤትዎ ልከናል!" ብሎኝ ስልኩ ተዘጋ አልቻልኩም... ያለኝን ብር ሁሉ ነበርኮ ለእቃዎ ያወጣሁት... ከድርጅቴ ውጪ ገንዘብ የለኝምኮ... አሁን ከየታባቴ አምጥቼ ነው የነፍስና የንብረት የምከፍለው? ያ ሁሉ ንብረቴ በቃ መሀል አስፓልት አመድ ሁኖ ቀረ? እንዲሁ እየተብሰለሰልኩ ወደቤቴ ገባሁ... መኝታ ቤት ያየሁት ነገር ነው ከሀሳቤ አንቅቶ እቤት እንደደረስኩ ያወኩት። ምን ማድረግ እንዳለብኝ አላውቅም ጭንቅላቴ ዞረብኝ... አሁንም ድረስ... ጆሮዬ ላይ የሚያቃጭለው ግን አብርሃም ወደጆሮዬ ጠጋ ብሎ... "በስምህ ልጅ ቢኖርህ እንኳን DNAውን ወደእኔ እስከመቀየር እበቀልሀለሁ!" የሚለውን ቃል ነው። ቆይ ምን አድርጌው ነው? ምንም አላውቅም! ሊነግረኝም አይፈልግም... ንብረቴን ሁሉ አሳጣኝ... ጭራሽ ደግሞ ሚስቴ እንኳን ካደችኝ... ጭነት ያዘዝኩበት ድርጅት ከሰሰኝ ማምለጥ አልቻልኩም... ድርጅቴንና መኪናዬን ሽጬ እዳዬን ከፈልኩ... የቀረኝ ቤቴ ብቻ ነው... ሚስት ተብዬዋ ያደረገችውን ነገር ካደረገች ብኋላም እንኳን ከቤቴ አልወጣችም... እኔም ያደረገችውን ሆን ብላ ስላደረገችው ምን ብዬ እናገራታለሁ? ተውኳት... እንዲህና እንዲያ ብዬ የመጨቃጨቅ አቅም የለኝ...