cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ

ያልተነገረውን እንነግርዎታለን ስለ አፍሪካ በእንግሊዘኛ ቋንቋ፤ @sputnik_africa

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
1 187
Obunachilar
+624 soatlar
+397 kunlar
+34330 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

Photo unavailableShow in Telegram
🇰🇪 በናይሮቢ ምስጢራዊ ግድያ የተሳተፉት አካላት በህግ እንደሚጠየቁ የኬንያው ፕሬዝዳንት ቃል ገቡ። ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በዋና ከተማይቱ ናይሮቢ ደቡባዊ ክፍል በምትገኘው ሙኩሩ ውስጥ በሚገኝ መንደር ውስጥ በሚገኝ የቆሻሻ መጣያ ስፍራ ተገድለው የተገኙት የዘጠኝ ሴቶች አስመልክተው ያላቸውን ከፍተኛ ስጋ ገልፀዋል። "ኬንያውያን ወጣት ልጃገረዶችን ጨምሮ ህይወታቸውን አጥተዋል። ይህ ጉዳይ በፍጥነት መጣራት አለበት፣ እናም በዚህ አፀያፊ ተግባር የተሳተፉ አካላት እንዲቀጡ፣ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ እና ህጉም ሙሉ ለሙሉ መተግበር ይኖርበታል" ብለዋል ሩቶ። የኬንያ ፖሊስ ግድያውን ከአምልኮ ሥርዓት፣ ከተከታታይ ግድያዎች እና ከህክምና ባለሙያዎች ማጭበር ጋር ሊኖር የሚችለውን ግንኙነት እያጣራ መሆኑን ገልጿል። ተጎጂዎቹ በጆንያ እና በጥቁር ፖሊ ከረጢቶች የተጠቀለሉ እና በገመድ የታሰሩ ሲሆን አንዳንዶቹም ደግሞ ቃጠሎ የደረሰባቸው እና የመበስበስ ሁኔታዎች ውስጥ ያሉ መሆናቸው ተገልጿል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉@sputnik_ethiopia
Hammasini ko'rsatish...
👍 1🤔 1
Photo unavailableShow in Telegram
🇿🇦 ደቡብ አፍሪካ የኒውክሌር ኃይል አጠቃቀሟን ለማሳደግ ትልቅ ጥረት ታደርጋለች ሲሉ ሚኒስትሩ ተናገሩ የደቡብ አፍሪካ የኤሌክትሪክ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ኬጎሲየንትሾ ራሞክጎፓ ሀገሪቱ ያለባትን የኤሌክትሪክ ሃይል እጥረት ለመቅረፍ የኒውክሌር ኢነርጂ ኢንዱስትሪዋን እንደምታሳድግ ጠቁመዋል። "ግልጽ ያልሆነ የግዥ አሰራር ሂደቱን ማጣጣል አንፈልግም፤ እርግጥ ነው ሀገራችን በምትችለው መጠን እና ፍጥነት ልክ የኃይል አቅርቦቱን እናደርገዋለን። ''ሲሉ ራሞክጎፓ ከመጀመሪያው የብሄራዊ አንድነት መንግስት ስብሰባ በፊት ለሀገር ውስጥ ሚዲያዎች ተናግረዋል። አላማው በሚቀጥለው ወር የ2,500 ሜጋ ዋት ሃይል ማመንጫ የሚያስችል የግምጃ ቤት ፍቃድ ለማግኘት ሲሆን ከዚህ ቀደም የነበረው የግዥ ጥያቄ 9,000 ሜጋ ዋት ለማመንጨት የሚያስቻል ነበር ተብሏል። "የግዥ አሰራሩ የፋይናንስ ድጋፍ ለማግኘት ከብሔራዊ ግምጃ ቤት ማፀደቅን ይፈልጋል፤ ስምምነቱን መጠን መገመት ትችላላችሁ"ብለዋል ሚኒስትሩ። " ከነሀሴ መጨረሻ በፊት ወጥተን ይህን ማድረግ እንደፈለግን እንናገራለን" ሲሉ ራሞክጎፓ ባለፈው እሁድ ለሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ተናግረዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉@sputnik_ethiopia
Hammasini ko'rsatish...
👍 1
🇪🇬🇮🇱🇵🇸 እስራኤል በጋዛ በሲቪል ቦታዎች ላይ እያደረሰችው ያላቸው ጥቃት የተኩስ አቁም ጥረቱን ውስብስብ አድርጎታል ስትል ካይሮ ተናገረች “በፍልስጤማውያን ላይ እየደረሰ ያለው የመብት ጥሰት መቀጠሉ፤ የተኩስ አቁም ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በእጅጉ እንደሚያወሳስበው የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሰጠው መግለጫ አስታውቋል። በትላንትናው እለት የእስራኤል መከላከያ ሃይል በጋዛ ካን ዩኒስ ከተማ አቅራቢያ በሚገኘው አል ማዋሲ አካባቢ በፈጸመው ዒላማውን የተጠበቀ ጥቃት ከ70 በላይ ሰዎች መገደላቸውን እና ወደ 290 የሚጠጉ ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸው መዘገቡ ይታወሳል። ካይሮ የእስራኤል መንግስት በአል ማዋሲ ላይ ያደረሰውን ጥቃት“በጽኑ ታወግዛለች” እና እስራኤል “የንፁሃን ዜጎችን ህይወት ችላ ማለቷን እንድታቆም” አሳስባለች። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉@sputnik_ethiopia
Hammasini ko'rsatish...
1.32 MB
3.98 MB
8.19 KB
6.95 KB
👍 3🤯 1
❗️የሩሲያ የምስራቅ ጦር ቡድን በዶኔትስክ ህዝባዊ ሪፐብሊክ የሚገኘውን የኡሮዝሃይኖይ መንደርን ነፃ ማውጣቱን ገልጿል። መንደሩንም ከተቀበሩ ፈንጂዎች በማጽዳት ላይ መሆኑንም የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉@sputnik_ethiopia
Hammasini ko'rsatish...
👍 5
Photo unavailableShow in Telegram
🇺🇸 ኤለን መስክ ባለፉት ስምንት ወራት ውስጥ ሁለት ሰዎች ሊገድሉት ሞክረው እንደነበር ተናገረ 💬 "ከፊታችን አደገኛ ጊዜ ይጠብቀናል። በሁለት የተለያዩ አጋጣሚዎች ሁለት ሰዎች ሊገድሉኝ ሞክረዋል። ሰዎቹ ቴክሳስ ከሚገኘው ከቴስላ ዋና መስሪያ ቤት በ20 ደቂቃ ርቀት ላይ ከእነ ጦር መሳሪያቸው ተይዘዋል። "ሲል አሜሪካዊው ቢሊየነር በማህበራዊ ሚዲያው ላይ አጋርቷል። በትላንትናው እለት ትራምፕ ንግግር በሚያደርጉበት ወቅት እንደተተኮሰባቸው የሚዲያ የተጋሩ ምሥሎች አሳይተዋል። በኋላም የአሜሪካ የደህንነት አገልግሎት ሠራተኞች ከመድረኩ ላይ ይዘዋቸው ሲወርዱ በቀኝ ጭንቅላታቸው በኩል ደም ይፈስ ነበረ። ትራምፕ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ መገናኛ ብዙሃኑ ገልፀዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉@sputnik_ethiopia
Hammasini ko'rsatish...
🤣 3👍 2
Photo unavailableShow in Telegram
🇺🇸 ኤለን መስክ ባለፉት ስምንት ወራት ውስጥ ሁለት ሰዎች ሊገድሉት ሞክረው እንደነበር ተናገረ 💬 "ከፊታችን አደገኛ ጊዜ ይጠብቀናል። በሁለት የተለያዩ አጋጣሚዎች ሁለት ሰዎች ሊገድሉኝ ሞክረዋል። ሰዎቹ ቴክሳስ ከሚገኘው ከቴስላ ዋና መስሪያ ቤት በ20 ደቂቃ ርቀት ላይ ከእነ ጦር መሳሪያቸው ተይዘዋል። "ሲል አሜሪካዊው ቢሊየነር በማህበራዊ ሚዲያው ላይ አጋርቷል። በትላንትናው እለት ትራምፕ ንግግር በሚያደርጉበት ወቅት እንደተተኮሰባቸው የሚዲያ የተጋሩ ምሥሎች አሳይተዋል። በኋላም የአሜሪካ የደህንነት አገልግሎት ሠራተኞች ከመድረኩ ላይ ይዘዋቸው ሲወርዱ በቀኝ ጭንቅላታቸው በኩል ደም ይፈስ ነበረ። ትራምፕ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ መገናኛ ብዙሃኑ ገልፀዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉@sputnik_ethiopia
Hammasini ko'rsatish...
00:09
Video unavailableShow in Telegram
🇺🇸 ባይደን ትራምፕን “ለሀገር አስጊ ነው” ሲሉ ተደምጠዋል-በማግስቱ ትራምፕ ጥይት ተተኮሰባቸው። 🤔 እንዴት ያለ አጋጣሚ ነው! ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉@sputnik_ethiopia
Hammasini ko'rsatish...
6.95 KB
🤔 5
Photo unavailableShow in Telegram
🇲🇿 በሞዛምቢክ የሚገኘው የደቡባዊ አፍሪካ የልማት ማኅበረሰብ(ሳዲክ) የሰላም ተልዕኮ ነገ ሰኞ እንደሚያበቃ የዛምቢያ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አስታወቁ ሙላምቦ ሀይምቤ ይህን ያሉት የሳዲክ የፖለቲካ፣የመከላከያ እና የደህንነት ጉዳዮች የሚኒስትሮች ኮሚቴ ለሁለት ቀናት ባካሄዱት 26ኛው ስብሰባ ላይ ነው። 💬 " ሃይምቤ እንደገለጹት በሞዛምቢክ የሚገኘው የሳዲክ ወታደራዊ ተልእኮ እ.ኤ.አ ሀምሌ 15 ቀን 2024 ከፔምባ ካቦ ዴልጋዶ ግዛት ሙሉ በሙሉ ለቆ እንደሚወጣ የዛምቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኤክስ ገጻቸው ላይ አስፍረዋል። እ.ኤ.አ በ 2021 በሞዛምቢክ የሚገኘው የደቡብ አፍሪካ ልማት ማህበረሰብ ወታደራዊ ተልእኮ በነዳጅ ዘይት ወደ በለፀገችው ካቦ ዴልጋዶ ግዛት በመዝመት፤የአማፂ ቡድኑን እንቅስቃሴ ለመግታት ያለመ ነበር። የሳዲክ ተልዕኮ ከቦትስዋና፣ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ከሌሴቶ፣ከማላዊ፣ከደቡብ አፍሪካ፣ ከታንዛኒያ እና ከዛምቢክ የተውጣጡ ወታደሮችን ያካተተ ነበር። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉@sputnik_ethiopia
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
🇸🇴 በሶማሊያ እስር ቤት በተሰማ ተኩስ እና ፍንዳታ ሳቢያ በትንሹ አምስት ሰዎች መሞታቸው ተዘገበ በሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃዲሾ እስር ቤት የሚገኙ ታራሚዎች የጦር መሳሪያ ማግኘት ከቻሉ በኋላ ተኩስ እና ፍንዳታ መከሰቱን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን የዓይን እማኞችን እና ባለስልጣናትን ጠቅሰው ቅዳሜ ዕለት ዘግበዋል። ጥቃቱ የተፈፀመው ማለዳ አካባቢ በማእከላዊ ማረሚያ ቤት ውስጥ መሆኑን መገናኛ ብዙሀኑ ገልጸው፤ግርግሩ ከማእከላዊ እስር ቤት ተነስቶ ቀስ በቀስ ወደ ተቋሙ ዋና ክፍል ተዛምቷል። በአሁኑ ወቅት ሁኔታው ​​​​እንደቀጠለ ሲሆን፣ባለስልጣናት ሁኔታውን ለመቆጣጠር በሂደት ላይ መሆናቸውን የመገናኛ ብዙሃኑ አክለው ገልጸዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉@sputnik_ethiopia
Hammasini ko'rsatish...
😁 2👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
🇷🇺🇺🇸 ዩክሬን ፑቲንን ለመግደል ከአሜሪካን ገንዘብ እንደተቀበለች የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማሪያ ዛካሮቫ እንደተናገሩት የዩክሬን የጸጥታ አካላት ከአሜሪካን ገንዘብ በመቀበል፤በሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ላይ በርካታ ያልተሳኩ የግድያ ሙከራዎችን አድርገዋል ብለዋል። ይህንን መረጃ መጀመሪያ ያወጣው የዩክሬን ዋና የስለላ ዳይሬክቶሬት ኃላፊ ኪሪል ቡዳኖቭ (Kirill Budanov* )ነው። የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ የፕሬዚዳንት ፑቲን ደህንነት በከፍተኛ ሁኔታ ጥበቃ እንደሚደረግደረጃ ላይ እንደሚገኝ እና ምንም እንኳን ሙከራዎች ቢደረጉም በበቂ ሁኔታ መረጋገጡን አረጋግጠዋል። * ኪሪል ቡዳኖቭ (Kirill Budanov*) በሩሲያ የአሸባሪዎች እና ጽንፈኞች መዝገብ ውስጥ የሰፈረ ግለሰብ ነው። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉@sputnik_ethiopia
Hammasini ko'rsatish...
👍 1
Boshqa reja tanlang

Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.