uz
Feedback
ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Kanalga Telegram’da o‘tish

በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:-  @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Ko'proq ko'rsatish
669
Obunachilar
+124 soatlar
+37 kun
-330 kun
Postlar arxiv
"አምላክህ በሰፈርህ መካከል ይሄዳልና ስለዚህ ነውረኛ ነገር እንዳያይብህ ፊቱንም ከአንተ እንዳይመልስ ሰፈርህ የተቀደሰ ይሁን።"          ዘዳግም 23÷14

" ለእውነት እየታዘዛችሁ ግብዝነት ለሌለበት ለወንድማማች መዋደደ ነፍሳችሁን አንጽታችሁ እርስ በርሳችሁ ከልባችሁ አጥብቃችሁ ተዋደዱ!" ፩ኛ ጴጥ. ፩÷፳፪
" ለእውነት እየታዘዛችሁ ግብዝነት ለሌለበት ለወንድማማች መዋደደ ነፍሳችሁን አንጽታችሁ እርስ በርሳችሁ ከልባችሁ አጥብቃችሁ ተዋደዱ!" ፩ኛ ጴጥ. ፩÷፳፪

"የተባረክሽ ሐና ሆይ በጠዋት እና በማታ የሠራነውን ኃጢአት ይቅር ይለን ዘንድ ከአባታችን ከኢያቄም እና ከእመቤታችን ከድንግል ማርያም ጋር ወደ አምላካችን ወደ ንጉሣችን ክርስቶስ ስለ እኛ ጸልዪ ለም
"የተባረክሽ ሐና ሆይ በጠዋት እና በማታ የሠራነውን ኃጢአት ይቅር ይለን ዘንድ ከአባታችን ከኢያቄም እና ከእመቤታችን ከድንግል ማርያም ጋር ወደ አምላካችን ወደ ንጉሣችን ክርስቶስ ስለ እኛ ጸልዪ ለምኚልን።"

" ለእውነት እየታዘዛችሁ ግብዝነት ለሌለበት ለወንድማማች መዋደደ ነፍሳችሁን አንጽታችሁ እርስ በርሳችሁ ከልባችሁ አጥብቃችሁ ተዋደዱ!" ፩ኛ ጴጥ. ፩÷፳፪
" ለእውነት እየታዘዛችሁ ግብዝነት ለሌለበት ለወንድማማች መዋደደ ነፍሳችሁን አንጽታችሁ እርስ በርሳችሁ ከልባችሁ አጥብቃችሁ ተዋደዱ!" ፩ኛ ጴጥ. ፩÷፳፪

"አልጋህ ላይ ስትወጣ መቃብርህ ውስጥ እንደምትገባ  አስብ እንቅልፍ የሞት ወንድም ነውና።"     ቅዱስ ዮሐንስ ሐፂር

"የሌላውን ሰው ውድቀት ስታይ ፣ 'እኔስ ከዚህ እብስ የለምን?' ብለህ ራስህን ጠይቅ።"    አባ ሙሴ ጸሊም

+ ይማርህ አይመራመርህ! + ..........................................   በነገራችን ላይ ሰው ሲያስነጥስ "ይማርህ" ብቻ አይባልም።   ከዕለታት በአንድ ቀን በጉንፋን እየተሰቃየሁ በኃይለኛው ሲያስነጥሰኝ አንዷ ወዳጄ እንደማንኛውም ሰው "ይማርህ" ብላ መረቀችኝ። "አሜን" ብዬ ስመልስላት "አይመራመርህ" ብላ ጨመረችልኝ።   ሰው ሲያስነጥስ "ይማርህ" የሚባለው የልብ ምቱ በሚያስነጥስበት ጊዜ ለቅጽበት ስለሚያቆም ነው። ይህች አስተዋይ እህቴ "አይመራመርህ" ብላ የጨመረችው ደግሞ እግዚአብሔር ኃጢአትህን አይመራመርህ፣ አይተሳሰብህ አይቁጠርብህ ማለቷ ነው።   እውነቷን ነው። እግዚአብሔር እያንዳንዷ ኃጢአታችንን ቢቆጥርብን፣ ቢመራመረን፣ ቢቆጣጠረን ምን እንሆን ነበር?   በጌታ ቅዳሴ ላይ ዲያቆኑ ብዙ አስፈሪ ልብን ቀጥ የሚያደርጉ ትእዛዛትን ሲያውጅ ሰምተነው ይሆናል። ይ.ዲ:-   "የአሳብ ነውር ያለበት ቢኖር አይቅረብ!   "አሳቡ ድውይ የሆነ ቢኖር ይራቅ! " ኃጢአትን የሚሠራ ንጹሕም ያልሆነ ቢኖር ይወገድ!   "በኃጢአት የወደቀ ቢኖር አይርሳ፣ የማይረሳ ነውና! "ከኢየሱስ ትእዛዝ ልዩ የሆነ ቢኖር ይከልከል!!" ደግነቱ ፈርተን እንዳንሸሽ ቤተ ክርስቲያን እዚያው በምንመልሰው ተሰጥዖ ታጽናናናለች እንጂ ይህን ሰምቶ ማን ይቆም ነበር?   ዲያቆኑ እንዲህ እያለ ሲያውጅ በሚታወጁት ሁሉ ኃጢአቶች ተዘፍቀን የምንኖረው እኛ እንዲህ ብለን እንመልሳለን።   "አቤቱ እንደ ቸርነትህ ነው እንጂ እንደ በደላችን አይሁን"   ወገኖቼ! የእግዚአብሔር ቸርነት ሆኖ እንጂ በየደቂቃው የምናስበው የኃጢአት ሀሳብ ነውራችን እኮ ወደ እግዚአብሔር ባላቀረበን ነበር።   እንደ ቸርነቱ ሆኖ እንጂ ንጹሕ ስላልሆንን፣ ኃጢአት ስለምንሰራ ብቻ መወገድ ነበረብን። እግዚአብሔር ቸር ሆኖ ኃጢአታችንን ንስሐ ስንገባ ስለሚረሳልን እንጂ እንደ በደላችን ቢሆንማ ኃጢአት የሚረሳ እኮ አልነበረም።   እንደ በደላችን ቢሆንማ እንደ ዳታንና አቤሮን ምድር ተከፍታ ብትውጠን በተገባ ነበር። እንደ በደላችን ቢሆንማ የሰራነው ኃጢአት ሊያስቀስፈን በተገባ ነበር።   እንደ በደላችን ቢሆንማ እሳት ከሰማይ ወርዶ ቢበላን፣ ከምድረ ገጽ ብንጠፋ ለእኛ የተገባ ነገር ነበር።   እግዚአብሔር ግን ቸር፣ መሐሪ፣ ይቅር ባይ ስለሆነ፣ ምሕረቱ መዓቱን እየቀደመ ስለሆነ እንጂ አንዳችንም በሕይወት ባለኖርን ነበር።   የምንተነፍሰው፣ ተኝተን የምንነሳው፣ የምንበላው የምንጠጣው፣ ሁሉን ነገር የምናደርገው እንደ እግዚአብሔር ቸርነት እንጂ እንደ በደላችን ስላልሆነብን ነው። ዓለም እስከአሁን ያልጠፋችው "የእግዚአብሔር ቸርነት ምድርን ስለመላች" ነው። (መዝ ፴፪ (፴፫) ፥ ፭)   "አቤቱ ኃጢአትን ብትጠባበቅ በፊትህ ማን ይቆማል?"                        መዝ ፻፳፱ ፥ ፫   እግዚአብሔር አምላክ ይማረን፣ አይመራመረን!! ................................. ዲያቆን ዮሐንስ ደረጀ

“በምትሄድበት ሁሉ እግዚአብሔር አምላክህ ከአንተ ጋራ ነውና አይዞህ፤ በርታ፤ ጽና፤ አትፍራ፤ አትደንግጥ ብዬ አላዘዝሁህምን?”” ኢያሱ 1:9
“በምትሄድበት ሁሉ እግዚአብሔር አምላክህ ከአንተ ጋራ ነውና አይዞህ፤ በርታ፤ ጽና፤ አትፍራ፤ አትደንግጥ ብዬ አላዘዝሁህምን?””        ኢያሱ 1:9

ከ600 በላይ የሆኑ ምዕመናን ሥጋ ወደሙን በኅብረት ተቀበሉ። ‎የቅዳሴ ሥርዓቱ በጉራጌ ሀገረ ስብከት በእዣ ወረዳ ቤተ ክህነት በጉየ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን ብፁዕ አቡ
+1
ከ600 በላይ የሆኑ ምዕመናን ሥጋ ወደሙን በኅብረት ተቀበሉ። ‎የቅዳሴ ሥርዓቱ በጉራጌ ሀገረ ስብከት በእዣ ወረዳ ቤተ ክህነት በጉየ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን ብፁዕ አቡነ መልከጸዴቅ በተገኙበት ተከናውኗል። EOTCMK TV መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም ‎ብፁዕነታቸው በመርሐ ግብሩ ላይ ሲያስተምሩ ምዕመናን እንዲህ ባለው ቁጥር ተገኝተው ለቅዱስ ቁርባን መብቃታቸው የቤተ ክርስቲያኒቱን መንፈሳዊ ጥንካሬና የተተኪውን ትውልድ ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ‎ ‎በዚህ ዘመን ቤት ለቤት በመሄድና በማስተማር ንስሐ በመስጠት ሁሉንም ለዚህ ክብር ማብቃት ሰማዕትነት ነው ብለዋል። እንደዚህ አይነት መርሐ ግብሮች አስተማሪና አብነት ስለሆኑ ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አሳስበዋል። ‎ ‎ይህ አገልግሎት የሀገረ ስብከቱን የአገልግሎት ጥንካሬ ብቻ ሳይሆን የደብሩን ጠንካራ አገልግሎት እና የምዕመናኑን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው፤  ከሕፃናት እስከ አዋቂዎች፣  በርካታ ወጣቶች፣ የሰንበት ትምህርት ቤት አገልጋዮች  የዘለዓለም ምግብ የሆነውን ቅዱስ ቁርባን መቀበል መቻላቸው የቤተ ክርስቲያን ተልእኮ ስኬትን ያሳያል ብለዋል። ‎ ‎በተለይም ወጣቶች እንዲህ ባለው በጋራ ምስጢራት መሳተፋቸው ለቀጣይ መንፈሳዊ ሕይወታቸው ትልቅ መመሪያ እንደሚሆናቸው ተናግረዋል። ‎ ‎ይህ በሀገረ ስብከቱ እየታየ ላለው መንፈሳዊ መነቃቃትና ለምዕመናን የሕይወት ለውጥ ትልቅ ማሳያ ሲሆን የብፁዕነታቸው የሁልጊዜ መመሪያ ተቀብሎ ተግባራዊ በመደረጉ ደብሩ ግንባር ቀደምና እንደ ሀገረ ስብከት አብነት መሆኑ ተገልጿል። ‎ ‎በመጨረሻም በብፁዕነታቸው መመሪያ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል ። ‎ ዘገባውነ ከሀገረ ስብከቱ የሚዲያ ገጽ አግኝተነዋል።

✞ የታለ ፍቅራችን ✞ የታለ የታለ ፍቅራችን የታለ የታለ ፍቅራችን እዳላገለገልን እደየ ፀጋችን መጋዉን በተነ መለያየታችን         አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸► የአንዳችን ከአንዳችን ቢለያይም ፀጋው የመረጠን ጌታ የጠራን አንድ ነው እርሱ የሚያወርሰን እያለችን እርስት ሕብረታችን ጠፋ በኛ መለያየት [፪]         አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸► አሕዛብ ደንግጠው በትላንት ቅኔያችን ወደቤቱ ገብቶ የራቀ ሕዝባችን እዳይሰናከል መንጋው በመንደኛ ምሳሌ እንሁነው እዉነተኛ እረኛ[፪]         አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸► የማንኖረዉ ስለምንናገር የሕጉ ፍጻሜ ስለሌለን ፍቅር መንጋዉ ሳይለወጥ ዘመናት አለፉ ብርቱ የነበሩ ስቶቹ ሰነፉ [፪]         አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸► የአንድ እናት የአንድ አባት ልጆች ከተባልን ከአንድ ማዕድ በልተን ለምን ተለያየን እንግዳዉን ትምህርት ወደኛ ያመጣ የበግ ለምዱን ያውልቅ ከመካከል ይዉጣ[፪]               የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel

“እግዚአብሔርን በፍርሀት አገልግሉት፤ ለርሱ በመንቀጥቀጥ ደስ ያሰኛችሁ።”      መዝሙር 2:11

ርዕሰ ባህታዊ በቃልና በኑሮ ሆነሀል ምስክር እንደ ፀሐይ አበራህ በእግዚአብሔር ሀገር ሰማያዊ ነህ እንጂ አይደለህም ምድራዊ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ርዕሰ ባህታዊ በስሙ ለሚያምኑት አማላጅ ሆነሀል በፀሎትህም ሀይል ተማምነንብሀል የክብር ኮከብ ነህ የገዳም መብራት አስተምረኸኛል ምግባር ሃይማኖት የሚያልፈውን አለም የምድሩን ንቀሀል የታመንከው አምላክ ህያው አድርጎሀል በስጋ በነፍስህ እግዚአብሔር ከበረ የማስታረቅን ቃል ባንተ ላይ አኖረ በተጋድሎ ብዛት በፆም በፀሎት ትተጋ ነበረ በፀናች እምነት ስለቃልኪዳንህ በረከት ይወርዳል ያንተ ስም ሲጠራ አጋንት ይርዳል ገብረ መንፈስ ቅዱስ የእምነት አባት አናብስት አናብርት የታዘዙለት ከኒሳ ተነስቶ ኢትዮጵያ ደረሰ ፀጋው በረከቱ በእኛ ላይ ፈሰሰ ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ

‛‛በወጣትነትህ ጊዜ ለነፍስህ ካልተጋደልክ፥ በእርጅናህ ጊዜ ምን ፍሬ ልታፈራ ትችላለህ?’’              ✍️ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰላልዊ

2 ቀን ቀረው ተዘጋጅተዋል?
2 ቀን ቀረው ተዘጋጅተዋል?

ጥያቄ? በዚህ ባለንበት ዘመን አንድ ሰው ሀይማኖቱን በምን ምክንያት ሊቀይር ይችላል ብላቹ ታስባላችሁ?
Anonymous voting

"መፍራት ያለብንን እግዚአብሔርን ስለማንፈራ መፍራት የሌለብንን ሰይጣንን እንፈራለን " ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

5 ቀን ብቻ ቀረው! ፈጥነው ይመዝገቡ!
5 ቀን ብቻ ቀረው! ፈጥነው ይመዝገቡ!

📖📖📖 📝📝📝📖📖📖 ኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች የቅድስት ቤተ ክርስቲያን የወደፊት ተስፋዎች ናቸው። ቤተ ክርስቲያን ልጆቿን በሙሉ በጥንቃቄ መጠበቅና ወደ አምላኳ መምራት የኹል ጊዜ ሥራዋ መኾኑ የታወቀ ነው። በተለይም ደግሞ ወጣት ልጆቿን የዚህ ዓለም ርካሽ ሐሳብ ከቤተ ክርስቲያናዊ (Ecclestical life) እንዳያጎድላቸው፥ ከቀድሞ የበለጠ መሥራት አለባት። በጥሩ መሠረት ላይ ያልቆሙ ወጣቶች ስንኳንስ የሌላው ቀርቶ የራሷ የቤተ ክርስቲያን ጠላቶች ይኾናሉና። በዚህም መሠረታዊ ምክንያት ቤተ ክርስቲያን ክርስቶሳዊት መኾኗ በጉልህ ይታወቅ ዘንድ ወጣቶቿን በመንፈሳዊ ሕይወትም ኾነ በቤተ ክርስቲያናዊ መረዳት ተግታ መሥራት አለባት። ወጣቶች የምድራዊቷን ቤተ ክርስቲያን (Earthly Church) አባል ስለ ኾኑ፥ በንስሐ ሳሙና እየታጠቡ፥ ከክርስቶስ ሥጋና ደም እየተሳተፉ፥ በቅድስና ሕይወት እንዲኖሩ ማድረግ የቤተ ክርስቲያን እረኞች የተባሉ የካህናት ዋና ሥራ መኾን አለበት። ከቤተ ክርስቲያን ውጭ ያሉ አካላትም ቢኾኑ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ብልጫ በዋነኛነት የሚያዩት ከወጣት ልጆቿ ነውና። ስለዚህ በዚህ ጉዳይ በተለይም በዚህ የኃጢአት እሳት በተለያየ መንገድ በሚቀጣጠልበት ዘመን፥ ኦርቶዶክሳዊ የኾነ የወጣትነት አኗኗርን የሚመለከቱ ብዙ ሥራዎች ያስፈልጉናል። ወጣትነት በብዙ መንገድ ሊጠበቅ የሚገባው የሕይወት ክፍል ስለ ኾነ፥ በእያንዳንዱ የወጣትነት የሕይወት ክፍል ውስጥ የሚፈጠሩ ችግሮችን የሚፈቱ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮዎች ለወጣቱ በእጅጉ ያስፈልጋሉ። 📖📖 መጽሔተ_ወራዙት_ዘኦርቶዶክስ 📖📖          "የኦርቶዶክሳዊ ወጣቶች መስታወት"

📖📖📖 📝📝📝📖📖📖 ኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች የቅድስት ቤተ ክርስቲያን የወደፊት ተስፋዎች ናቸው። ቤተ ክርስቲያን ልጆቿን በሙሉ በጥንቃቄ መጠበቅና ወደ አምላኳ መምራት የኹል ጊዜ ሥራዋ መኾኑ የታወቀ ነው። በተለይም ደግሞ ወጣት ልጆቿን የዚህ ዓለም ርካሽ ሐሳብ ከቤተ ክርስቲያናዊ (Ecclestical life) እንዳያጎድላቸው፥ ከቀድሞ የበለጠ መሥራት አለባት። በጥሩ መሠረት ላይ ያልቆሙ ወጣቶች ስንኳንስ የሌላው ቀርቶ የራሷ የቤተ ክርስቲያን ጠላቶች ይኾናሉና። በዚህም መሠረታዊ ምክንያት ቤተ ክርስቲያን ክርስቶሳዊት መኾኗ በጉልህ ይታወቅ ዘንድ ወጣቶቿን በመንፈሳዊ ሕይወትም ኾነ በቤተ ክርስቲያናዊ መረዳት ተግታ መሥራት አለባት። ወጣቶች የምድራዊቷን ቤተ ክርስቲያን (Earthly Church) አባል ስለ ኾኑ፥ በንስሐ ሳሙና እየታጠቡ፥ ከክርስቶስ ሥጋና ደም እየተሳተፉ፥ በቅድስና ሕይወት እንዲኖሩ ማድረግ የቤተ ክርስቲያን እረኞች የተባሉ የካህናት ዋና ሥራ መኾን አለበት። ከቤተ ክርስቲያን ውጭ ያሉ አካላትም ቢኾኑ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ብልጫ በዋነኛነት የሚያዩት ከወጣት ልጆቿ ነውና። ስለዚህ በዚህ ጉዳይ በተለይም በዚህ የኃጢአት እሳት በተለያየ መንገድ በሚቀጣጠልበት ዘመን፥ ኦርቶዶክሳዊ የኾነ የወጣትነት አኗኗርን የሚመለከቱ ብዙ ሥራዎች ያስፈልጉናል። ወጣትነት በብዙ መንገድ ሊጠበቅ የሚገባው የሕይወት ክፍል ስለ ኾነ፥ በእያንዳንዱ የወጣትነት የሕይወት ክፍል ውስጥ የሚፈጠሩ ችግሮችን የሚፈቱ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮዎች ለወጣቱ በእጅጉ ያስፈልጋሉ። 📖📖 መጽሔተ_ወራዙት_ዘኦርቶዶክስ 📖📖          "የኦርቶዶክሳዊ ወጣቶች መስታወት"