ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Kanalga Telegram’da o‘tish
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Ko'proq ko'rsatish672
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+37 kun
-130 kun
Postlar arxiv
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ጳጉሜን የሚለው ስያሜዋ ግን “ሄፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ መሆኑን አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ተነግሯል፡፡ “ኤፓጉሜኔ” ማለት ጭማሪ ማለት ነው፡፡ በግእዝ ቋንቋችን ተውሳክ ማለት ነው፡፡ ተውሳክ ማለት ተጨማሪ ማለት ነው፡፡ “ወሰከ - ጨመረ” ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ነው፡፡ (ምንጭ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ገጽ ፱፻፭)፡፡ ምዕራባዊያኑ ጳጉሜን ተጨማሪ ቀን አድርገዋታል፡፡ እኛ ግን የወር ተጨማሪ አድርገናታል፡፡ በጽርዕ ኤፓጉሜኔ ትባል እንጂ ሊቃውንት ግን ተረፍ ይሏታል፡፡ ጳጒሜን የአሮጌው ዓመት ማብቂያ የአዲሱ ዓመት መንደርደሪያ ዕለት እንደሆነች የክርስቶስ ልደትም የዓመተ ፍዳ ማቆሚያ የዓመተ ምሕረት መጀመሪያ በመሆኑ ዕለታቸው ራሱ በተመሳሳይ ቀን ተቀምሮ ይውላል፡፡
የጳጉሜን ወር ‹‹የምሕረት ወር›› ስለመባሏ፡-
ኢትዮጵያ በዓለም ብቸኛዋ የ፲፫ ወራት ጸጋ ባለቤት ስትሆን የጳጉሜን ወርም በኢትዮጵያውያን ዘንድ የምሕረት ወር ተብሎ ይታመናል። በተለይም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ መሠረት ጸሎት የሚያርግበት ዕለተ ምጽአት የሚታሰብበት የምሕረት ወር መሆኑን ታስተምራለች፡፡ በተለይም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት መሠረት ምእመናኑ በጳጉሜን ጸበል በመጠመቅ ድኅነት በማግኘታቸው የምሕረት ወር መሆኑን ምእመናን ያብራራሉ፡፡
🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲
(መዝ ፳፯ )
------------
፩ እግዚአብሔር ብርሃኔና መድኃኒቴ ነው፤ የሚያስፈራኝ ማን ነው? እግዚአብሔር የሕይወቴ መታመኛዋ ነው፤ የሚያስደነግጠኝ ማን ነው?
፪ ክፉዎች፥ አስጨናቂዎቼ ጠላቶቼም፥ ሥጋዬን ይበሉ ዘንድ በቀረቡ ጊዜ፥ እነርሱ ተሰናከሉና ወደቁ።
፫ ሠራዊትም ቢሰፍርብኝ ልቤ አይፈራም፤ ሰልፍም ቢነሣብኝ በዚኽ እተማመናለኹ።
🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱
53 ዓመታትን በአገልግሎት
ቅዳሜ ጷግሜን 1 እና እሁድ ጷግሜን 2 ከቀኑ 8:00 ሰዓት ጀምሮ በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል አዳራሽ እንገናኝ።
"አገልግሎት ስላለን አንታክትም!"
እንኳን ለፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት 53ኛ ዓመት የምስረታ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
👑👑👑👑👑👑
👑 አብርሂ ፍኖተ ወንጌል👑
👑👑👑👑👑👑
ሊቀ መዘምራን ላእከ ማርያም ወልደ ኢየሱስ
ከ1915-2004 ዓ.ም
ሊቀ መዘምራን ላእከ ማርያም ወልደ ኢየሱስ በአርሲ ክፍለ ሀገር በጢዮ ወረዳ ልዩ ስሙ ጨቢ አቦ በተባለ አካባቢ ከአባታቸው መምህር ወልደ ኢየሱስ ዘነበ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ወለተ ሩፋኤል ብስራት ነሐሴ 16 ቀን 1915 ዓ. ም. ተወለዱ፡፡
ከአባታቸው ከመምህር ወልደ ኢየሱስ ዘነበ ንባብ፤ ውዳሴ ማርያም ንባብና ዜማ ፤መዝሙረ ዳዊትና ግብረ ዲቁና በመማር ለስልጣነ ክህነት ከበቁ በኋላ በአካባቢያቸው በሚገኘው ዱግዳ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በዲቁና ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡
ገና በለጋ እድሜያቸው ትምህርትን ፍለጋ ወደ ወሎ ክፍለ ሀገር ላስታ ገረገራ ቅዱስ ጊዮርጊስ በመሔድ ከመምህር ሰይፉ የመጻሕፍተ ሐዲሳትን ትርጓሜ ፤ ከሌሎችም ታዋቂ መምህራን ድጓንና ጾመ ድጓን ተምረዋል፡፡ ወደ ጎንደር በማቅናት ዙር አምባ ገዳም ከታላቁ መምህር ቀለመወርቅ ዝማሬ መዋሥዕት በመማር አጠናቀዋል፡፡ ወደ ደብረ ታቦር በመሔድም የተክሌ አቋቋም ሊቅ ከሆኑት መምህር ቀለመወርቅ ዘንድ ገብተው አስመስክረዋል፡፡ ጎንደር አደባባይ ኢየሱስ ከታዋቂው የቅኔ መምህር በቅጽል ስማቸው የቅኔው ማዕበል መምህር ፈንቴ ቅኔ አስመስክረዋል፡፡ በዋሸራ ከሚገኙት የቅዳሴ መምህር አባ አላምረው ዘንድ የደብረ ዓባይ የመዝገብ ቅዳሴ ተምረዋል፡፡ ሞጣ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ደግሞ ከመልአከ ገነት ጥሩነህ ለተማሪዎቻቸው ዝማሬ መዋሥዕትን እያስቀጸሉ ከእሳቸው የአቋቋም ስልቶችን በሚገባ አጣርተው ለማስመስከር በቅተዋል፡፡
ወደ መምህርነት ከገቡ በኋላ ብዛት ያላቸው ደቀመዛሙርትን ያፈሩ ሲሆን የተክሌ የአቋቋም በቀላሉ ለመማር የሚያስችል ምልክት ፈጥረው ለደቀ መዛሙርቶቻቸው አስተምረዋል፡፡
በአዲስ አበባ በተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት በመምህርነት ያገለገሉ ሲሆን፤ በታእካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም፤ በደብረ ኀይል ቅዱስ ራጉኤል ፤ በብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተ ክርስቲያናት እየተዘዋወሩ በርካታ ደቀመዛሙርትን አፍርተዋል፡፡
ወደ ትውልድ ሀገራቸው አሰላ በመመለስም በአሰላ መንበረ ጵጵስና ር/ገ/ወአ/ደ/ም/ቅ/ማርያም ቤተ ክርስቲያን በመሪ ጌትነት ሲያገለግሉ የቆዩ ሲሆን፤ ከ1971 ዓ.ም. እስከ 1998 ዓ.ም. በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን በአስተዳዳሪነት አገልግለዋል፡፡
በጎንደርና ጎጃም የትምህርትና የመምህርነት ዘመናቸው ላበረከቱት አገልግሎት ከደብረ ወርቅ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በቅሎ ከነኮርቻው ተሸልመዋል፡፡
ባበረከቱት ፍጹም ቅንነት የተሞላበት አገልግሎታቸው የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከነበሩት ከቀድሞው ብፁዕ አቡነ ሉቃስ ቀሚስና ጥንግ ድርብ ከነካባው አልብሰዋቸው፤ የእጅ የወርቅ መስቀል በመሸለም ሊቀ መዘምራን የሚል የክብር ስምም ሰጥተዋቸዋል፡፡
መጻሕፍትን በማንበብና በመተርጎም ለቤተ ክርስቲያን ከፍተኛ ውለታ የዋሉ አባት ሲሆኑ የዓመቱን መጽሐፈ ስንክሳር ከግእዝ ወደ አማርኛ ለመተርጎም ሰባት ዓመታትን ፈጅቶባቸው አስመራ ለሕትመት በተላከበት ወቅት ጠፍቷል፡፡ ተስፋ ሳይቆርጡ በድጋሚ በሁለት ዓመታት ውስጥ በድጋሚ ተርጉመው ለሕትመት አብቅተዋል፡፡ እንዲሁም ግብረ ሕማማትንና ገድለ ዜና ማርቆስን ከግእዝ ወደ አማርኛ በመተርጎም ለሕትመት አብቅተው ቤተ ክርስቲያን እየተጠቀመችባቸው ትገኛለች፡፡ በተጨማሪም ገድለ ሐዋርያት፤ ተአምረ ኢየሱስ፤ ገድለ ቂርቆስ ፤ ገድለ ነአኩቶ ለአብ ፤ ገድለ ሊባኖስ፤ ገድለ ማርያም መግደላዊት፤ ድርሳነ ሐና ፤ ገድለ ዮሐንስ መጥምቅና ሌሎችም በርካታ መጻሕፍት ከግእዝ ወደ አማርኛ በመተርጎም ለቤተ ክርስቲያን አበርክተዋል፡፡
ሊቀ መዘምራን ላዕከ ማርያም ወልደ ኢየሱስ በአንድ ወቅት መጻሕፍትን ለመተርጎም የተነሳሱበትን ምክንያት ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ “በመኪና አደጋ እግሬ ተሰብሮ በነበረበት ወቅት ቁጭ ከምል ለምን መጻሕፍትን አልተረጉምም በሚል እግዚአብሔር አሳስቦኝ ተነሳሳሁ፡፡ ስንክሳርንና ሌሎችን አሥራ ሦስት መጻሕፍትን የተረጎምኩት ያኔ ነው፡፡ እግዚአብሔር ታላቅ ችሮታ ነው ያደረገልኝ፡፡ እግሬ ባይሰበር ኖሮ እነዚህን መጻሕፍት መተርጎም አልችልም ነበር፡፡ እግዚአብሔር የጎዳ መስሎ ይጠቅማል፡፡ የእግሬ መሰበር ትልቅ ጥቅም ለኔም ለቤተ ክርስቲያንም አስገኝቶልኛል፡፡” ብለው ነበር፡፡
በቅርቡም በጠና ታመው ሕመማቸው ፋታ በሰጣቸው ስዓት ለደብረ ሊባኖስ ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ይተረጉሙት የነበረው ዜና ሥላሴ የተሰኘው መጽሐፍ አብዛኛውን ክፍል ተርጉመው ያገባደዱት ሲሆን ሳይፈጽሙት ሞት ቀድሟቸዋል፡፡
በእርግና ምክንያት ጡረታ ከወጡ በኋላ ለቤተ ክርስቲያን ባበረከቱት ከፍተኛ ትጋትና አገልግሎት የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ሙሉ ደሞዛቸው እንዲከፈላቸው አድርገዋል፡፡
ሊቀ መዘምራን ላእከ ማርያም ወልደ ኢየሱስ በ1946 ዓ.ም. ከወ/ሮ ምሕረት በትዕዛዙ ጋር በስርዓተ ተክሊል ጋብቻ የፈጸሙ ሲሆን ስድስት ወንዶችና ስድስት ሴቶች ልጆችን አፍርተው ሠላሳ አንድ የልጅ ልጆችን ለማየት በቅተዋል፡፡
ነሐሴ 28 ቀን 2004 ዓ/ም በ90 አመታቸው ዐረፉ። የቅዱሳን አምላክ እግዚአብሔር ነፍሳቸውን በገነት ያኑርልን፡፡
በረከታቸው ትደርብን። አሜን።
<<ከመቀየም ይልቅ የዋህነትን የምትወድ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! የትዕግስትህን መጠኑን አውቀው ዘንድ የአፍ መዝጊያ ቁልፍ የሆነች ዝምታን ስጠኝ>>
<<ይህን ያህል ዝምታ እንደምን ያለ ዝምታ ነው? ይህን ያህል ትዕግሥት እንደምን ያለ ትዕግስት ነው?>>
"የህይወት መንገድ ለጨለመባችሁ
የድንግል ማርያም ልጅ ቸሩ መድኃኔዓለም እውነተኛውንና ቀጥተኛውን መንገድ ይምራችሁ። ቸሩ መድኃኔዓለም ላጣነው ማግኘትን ለተጨነቅነው መፅናናትን ለተረበሽነው ሰላምን ለታመምነው ምህረት ቸሩ መድኃኔዓለም ይስጠን ቸርነቱ አይለየን መልካም ቀን ይሁንልን🙏💜🤍
የፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት አባል የሆነው ወንድማችን መዘምር መስፍን እሸቱ ከዳግማዊ ሚኒሊክ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በማስተርስ ዲግሪ በዛሬው እለት ተመርቋን። ወንድማችን እና የሰንበት ት/ቤታችን አባላት እንዲሁም ወዳጆቹ እንኳን ደስ አላችሁ።
ቀሪው ዘመንህ የተባረከ እንዲሆንልህ እንመኛለን።🙏
👨🎓👨🎓👨🎓
"ነፍሴ ሆይ! የምትድኝበትን እኔ እነግርሻለሁ፥ ከዚህ ሁሉ ይልቅ ወደ ቅድስት ድንግል ጩኺ፣ እንዲህም በይ የብርሃን እናት ሆይ! በልጅሽ ፊት በደልሁ ኃጢአቴን አስተስርይልኝ፡፡"
አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ
"በሰው ላይ በአመፃ የምትነሣሣ ከሆነ በእግዚአብሔር ላይ እንደተነሣሣህ ቁጠረው፡፡ ለባልንጀራህ አክብሮትን የቸርኸው ከሆነ እንሆ እግዚአብሔርን አከበርኽ።"
ቅዱስ ኤፍሬም
+4
ፎቶ:- 16/12/2017 ዓ.ም
ሰንበት ት/ቤታችን በየአመቱ በሚያዘጋጀው የፍልሰታ ንፍሮ ዝግጅት በጉልበት፣ በገንዘብ ፣በሀሳብ የረዳችሁን ሁሉ ቸር ፣መሀሪ ፣ይቅር ባይ የሆነው አምላካችን መልካሙን ሀሳባችሁን ይፈጽምላቹ፤ እግዚአብሔር ያክብርልን🙏
የአመት ሰው ይበለን🙏
