ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Kanalga Telegram’da o‘tish
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Ko'proq ko'rsatish670
Obunachilar
-224 soatlar
+57 kun
+130 kun
Postlar arxiv
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የጥቃት ዓላማ ያደረጉ የጥላቻ ንግግሮች እንዲቆሙ ምእመናን ጠየቁ !
መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም
በተለያዩ የማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ዒላማ ያደረጉ የጥላቻ ንግግሮች እና መልእክቶች በአፋጣኝ እንዲቆሙ እና መንግስትም ሕጋዊ እርምጃ እንዲወስድ ቲኤምሲ ያነጋገራቸው ምእመናን ገልጸዋል።
ማናቸውም ቤተ እምነቶች መብቶቻቸው እንዲከበር እንደሚፈልጉትና የሃይማኖታቸውን አስተምህሮ በነጻነት ማስተላለፍ ሕገ መንግስታዊ መብታቸው እንደሆነ የጠቆሙት አስተያየት ሰጪ ምእመናኑ በተመሳሳይም ሁሉም ቤተ እምነቶች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን እምነት እና አስተምህሮ ባከበረ መልኩ ሊንቀሳቀሱ እንደሚገባ ገልጸዋል።
ሁሉም ኢትዮጵያውያን የሃይማኖት ነጻነታቸውን ተጠቅመው በማናቸውም መልኩ ሃይማኖታቸውን ማራመድ ሕገ መኖግስታዊ መብታቸው ቢሆንም የሌላውን እምነት ማንቋሸሽ፣ ማኮሰስ እና ማጥላላት ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው እና ግጭት ቀስቃሽና ጸረ ሰላም እንቅስቃሴ መሆኑ ነው የተገለጸው።
ባለፉት ጊዜያት ከአንዳንድ ቤተ እምነት ተከታዮች ስለ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፣ ስለ ቅዱሳን፣ ስለ ንዋያተ ቅድሳት ብሎም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት በምታስተምቸው ትምህርቶች ላይ ትኩረት
በተለይም መዋቅራዊ ድጋፍ እየተሰጠው በሚመስል መልኩ የጥላቻ ንግግሮች ተባብሰው መቀጠላቸው እና ይኸው ጥላቻም በኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ብቻ ሳይሆን በሜንስትሪም እና በመጽሐፍትም ጭምር ሲካሄድ መቆየቱ እና እየተካሄደ መሆኑ በርካታ ምእመናንን ያሳዘነና ያስቆጣ መሆኑ ተመላክቶአል።
መንግስት እነዚህን የጥላቻ አራማጆች እና ጸረ ሃይማኖት ግለሰቦችን በሕግ አግባብ እንዲጠይቅም ምእመናን ጥሪ አቅርበዋል።
"አቤቱ አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ ከአንተ ዘንድ ከሰማይ የሚገኝ ሰላምን ሁሉ በሁላችን ልቡና አሳድርብን። በእርስዋም የሕይወትን ሰላም ስጠን።ለሀገራችን ኢትዮጵያም ሰላሟን አጽናላት።"
ሥርዓተ_ቅዳሴ
🍁🍁🍀🍀✨🍁🍁🍀🍀✨🍁🍁🍀🍀✨
"አሳ ያለ ውሃ መዋኘት እንደማይችል፣ ወፍ ያለ አየር መብረር እንደማትችል ሁሉ ክርስቲያንም አንዲት እርምጃ እንኳ ያለ ክርስቶስ መሻሻል አይችልም።"
✨ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ
"ስለ እግዚአብሔር ብለህ ለሰዎች ታዘዝ እንጂ ስለ ሰዎች ብለህ ለእግዚአብሔር አትታዘዝ፡፡"
✨ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
"ሰይጣን ክርስቶስ በልብህ ውስጥ ያለ መሆን አለመሆኑን ያውቃል፡፡ ይኸውም ስትቆጣ ወይም ስትጮህ ወይም የማይረቡ ከንቱ ነገሮችን ስትናገር ሲያይህ ጠላት በአንተ ዘንድ እግዚአብሔር እንደሌለ ያውቃል ያን ጊዜ በውስጥህም በውጭህም ያለውን ሳይቀር ይገዛል ፤ መዝጊያ እንደሌለው ቤት እንደ ክፉ ሌባ ይገባና ውስጥህን ይበረብረዋል፡፡"
✨ቅዱስ ባስልዮስ
"በገነት ውስጥ አዳምን በመፈለግ እንደሄደው፣ እግዚአብሔር ዛሬም በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ሰዎችን ይፈልጋል።"
✨ቅዱስ አምብሮዝ
"ጌታ ሆይ ወርቅ ትሰጠኝ ዘንድ አልለምንህም ሀብት ንብረትም አልለምንህም እነርሱ ድኅነትን የሚያስገኙ አይደሉም። ይቅርታህን ማግኘት ግን ከወርቅ ይልቃል። የኃጢአት ሥርየትን ማግኘትም ከብር ይበልጣል።"
✨ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
🍁🍁🍀🍀✨🍁🍁🍀🍀✨🍁🍁🍀🍀✨
✨ ምኩራቤን አንጻልኝ ✨
ጌታ ሆይ የሀጢአት መነገጃ የበደል መረማመጃ የሆነው የልቤን ምኩራብ አንጻልኝ! ንብረታቸውን እንደገለባበጥክ በኔም ሕይወት የተተሰገሰጉና የሰይጣን መጠቀሚያ የሆኑ ክፉ አመሎቼን ገለባብጠህ ጣልልኝ !
ጌታ ሆይ የአባቴ ቤት የንግድ ቤት አታርጉ ብለህ እንደገሰጽካቸው እኔንም ለሚፈታተኑ ሥጋዬን ደሞዝ አርገው የሚሰለጥኑ ለጸላዕያኑ "ቤቴን የሀጢአት ቤት አታድርጉት " ብለህ በጌትነትህ ገስጽልኝ
ጌታ ሆይ ለበዓል ወደ ቤተ መቅደስ እንደወጣህ የኔንም የመዳኔን ፋሲካ የንስሐን ፋሲካ የመለወጥን ፋሲካ ትከብርበት ዘንድ ወደኔም ና
ጌታ ሆይ ሐዋርያቶችህ የቤትህን መነወር አይተው "የቤትህ ቅናት በላችኝ " የሚለውን ቃል እንዳሰቡ የተነወረው የኔንም ሰውነት ሐዋርያቶችህ "የቤትህ በሀጢአት መነወር በላን" ብለው ስለወደኩት ስለ ሀጢአተኛው ልጃቸው በቀኑልኝ
ጌታ ሆይ የኔንም ምኩራብ አንጻው የእኔም ልቡና ያንተን የቅጣት ጅራፍ ያይደለ የምህረት እጆችህን ይናፍቃልና በቸርነትህ ማረኝ
/ኢዮብ ዘገነተ ጽጌ/
የፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት አባል የሆንሽ እህታችን መዘምርት ቃልኪዳን አለማየሁ እንኳን ደስ አለሽ። አባታችን ቸሩ መድኃኔዓለም እረድቶ እንኳን ለዚህች ቀን አደረሰሽ ። አምላካችን መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ በዕውቀት በሞገስ በጥበብ ጠብቆ ከዚህ በላይ ለቁም ነገር ያብቃሽ። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አትለይሽ።
Congratulation🧑🎓🧑🎓🧑🎓
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨በዚህ ሳምንት ጌታችን ወደ ምኵራብ ገብቶ ማስተማሩ የሚነገርበት፤ ‹‹ቤቴ የጸሎት ቤት ይባላል፤ እናንተ ግን የሌቦች ዋሻ አደረጋችሁት›› ብሎ በምኵራብ ይሸጡ፣ ይለውጡ የነበሩትን የገሠፀበት፤ ቤተ መቅደስን የከብት መንጃ የወርቅና የብር መነገጃ ያደረጉ ሰዎችን ከነሸቀጣቸው ከቤተ መቅደስ ያስወጣበት፤ ቤተ መቅደስ የእግዚአብሔር ማደሪያ፣ የስሙ መጠሪያ፣ የጸሎት ሥፍራ መኾኗን ያስረዳበትና ያወጀበት፤ በቤተ መቅደስ የንግድ ሥራ ማከናወን እንደማይገባ ያረጋገጠበት ዕለት ነው፡፡
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
''ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ ወመሐረ ቃለ ሃይማኖት ወይቤሎሙ ምጽዋተ አበድር እመሥዋዕት አነ ውእቱ እግዚኣ ለሰንበት ወአቡሃ ለምሕረት እግዚኣ ውእቱ ለሰንበት ወልደ እጓለ እመሕያው ኢትግበሩ ቤተ አቡየ ቤተ ምስያጥ ቤትየሰ ቤተ ጸሎት ይሰመይ ቦአ ምኩራቦሙ ወገሠፆሙ ያርምሙ አንከሩ ምህሮቶ ሞገስ ቃሉ ወጣዕመ ነገሩ ወሣዕሣዓ አፉሁ::''ትርጓሜ:-
''ጌታችን ኢየሱስ ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ፤ የሃይማኖት ቃልን አስተማረ። "ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን እወዳለኹ፤ የሰንበት ጌታዋ የምሕረት አባቷም እኔ ነኝ፤ የሰው ልጅም የሰንበት ጌታዋ ነው፡፡ ያባቴን ቤት የንግድ ቦታ አታድርጉት፤ ቤቴስ የጸሎት ቤት ይባላል!" እያለ የሃይማኖትን ቃል አስተማራቸው። ወደ ምኩራባቸውም ገብቶ ዝም ይሉ ዘንድ ገሠፃቸው፤ እነርሱም ትምህርቱን፣ የቃሉን ግርማ፣ የአነጋገሩን ጣዕምና የአንደበቱን ቅልጥፍና አደነቁ።''የዕለተ ሰንበት መዝሙር (ከጾመ ድጓ) ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በጾም ሰዓታችሁ ጊዜ ይሁንም አይሁንም ሦስት ነገሮችን በሕሊናችሁ ትይዙ ዘንድ እመክራችኋለሁ፡፡
እነርሱም፡-
☞ ክፉ ከመናገር መከልከልን፣
☞ ማንንም ሰው እንደ ጠላት ከማየት መቆጠብንና
☞ እንደ ልምድ አድርጋችሁ ከያዛችሁት መሐላ ትርቁ ዘንድ እመክራቸኋለሁ፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
መልካም ቀን🙏
መዋረድንም አውቃለሁ መብዛትንም አውቃለሁ፤ በእያንዳንዱ ነገር በነገርም ሁሉ መጥገብንና መራብንም መብዛትንና መጉደልን ተምሬአለሁ።
ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ።
መልካሙን ሁሉ የምትሰሙበት ቀን ይሁንላችሁ🙏
በሚገጥሙን መጥፎ ነገሮች መሰናክሎች የምንማረር ሳይሆን ሁሉም ነገር ለበጎ ነው የሚል የማይሰለች ልብ እግዚአብሔር ያድለን አሜን🙏🙏
#ለዝክረ_ስምከ
#መድኃኔዓለም ዓለም ሆይ ምስጋና የሁል ጊዜ ተግባራቸው የሆነ ሰማያውያን መላእክት እና ምድራውያን ጻድቃን ሰማዕታት ተመራምረው ለማይደርሱበት ለስም አጠራርህ ሰላም እላለሁ
#መልክዐ_መድኃኔዓለም
በሥርዓተ ቅዳሴ ላይ ስንት ጊዜ እንደሚደወል ምሳሌውንስ ያውቃሉ?
በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓት መሠረት በቅዳሴ ጊዜ አምስት ጊዜ ይደወላል።
፩. የመጀመሪያው የተጋብዖ ደውል ይባላል። ልክ ቅዳሴው ገና ሳይጀመር የሚደወለው ደውል ሲሆን የነብያት የስብከታቸው ምሳሌ ነው። ይህ ደውል ሁሌም የሚደወለው ሌሊት ነው። "ለምንድን ነው" ቢሉ ሌሊት የጨለማው ዘመን፣ የኦሪት ምሳሌ ነው። ሌሊት ድምጹን መስማታችን እግዚአብሔር ጨለማ በሆነው ጊዜያችን እንኳን እንደማይተወንና ድምፁን እንደማያሸሽብን ማሳያ ነው።
፪. ቅዳሴውን ልንጀምር ስንል ማለትም "ይህች ሰዓት ምን ያህል የምታስፈራ ናት?" ሲባል ይደወላል። ይሄ ደግሞ ቅዱስ ገብርኤል እመቤታችንን ያበሰራት የብስራቱ ምሳሌ ነው።
፫. ሶስተኛው ደውል የሚደወለው ደግሞ ለእግዚኦታ ነው። ይሄኛው ደውል ደግሞ የእመቤታችን እና የቅዱስ ዮሐንስ ክርስቶስ በተሰቀለ ጊዜ ያለቀሱት የእምባቸው ምሳሌ ነው።
፬. እንዲሁም ዐራተኛው የሚደወለው ልክ ወንጌል ተነቦ ካለቀ በኋላ “ፃኡ ንኡሰ ክርስቲያን" / "የክርስቲያን ታናናሾች የሆናቹ ውጡ" ሲባል ይደወላል። ንኡሰ ክርስቲያን የሚባሉት ቤተክርስቲያናችን ገና አምነው ያልተጠመቁ ሰዎች ቅዳሴውን ማስቀደስ የሚችሉት እስከዚህ ክፍል ብቻ ነው። እሱ ክፍል ላይ ደውል ይደወላል። ይህም የሐዋርያት የስብከታቸው ምሳሌ ነው።
፭. የአምላክ ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም ሲወርድም ይደወላል። ይሄ ደግሞ ኒቆዲሞስና ዮሴፍ ክርስቶስን ሲገንዙት ያመሰገኑት ምስጋና ምሳሌ ነው። “ቅዱስ እግዚአብሔር፣ ቅዱስ ኃያል፣ ቅዱስ ሕያው ዘኢይመውት” እንላለን። ያ ኒቆዲሞስና ዮሴፍ ክርስቶስን ሲገንዙት ያወጡት የምስጋና ድምጽ አምስተኛው ደውል ነው። ስለዚህ፣ ይሄ እየተደወለ ወደ ቤተመቅደስ ከቤተ መቅደስ ወጥተው ቤተልሔም ይሄዳሉ። ከቤተልሔም ኅብስቱን ይዘው ሲመጡ ደግሞ ክርስቶስ ከምድር ወርዶ ቤተመቅደስ የተባለ ጎሎጎታ ላይ ሊሰዋ እንደመጣ ምሳሌ ነው።
ዲያቆን ዘላለም ታዬ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
"አቤቱ አንተን እናመሰግና ለን፡፡ ከሁሉ በላይ የምትሆን የአብ የባሕርይ ልጅ ኢየ ሱስ ክርስቶስ ጌትነትህ ለዘለዓለም የሚሆን ለአብ ከመ ንፈስ ቅዱስ ጋራ በቃላችን ይህንን ምስጋና ሦስተኛ ጊዜ ለአንተ እናቀርባለን፡፡ ፍጥረቱ ሁሉ በመራድ በመ ንቀጥቀጥ በመፍራት ያመሰግንሃል፡፡ ነፍስ ሁሉ የሚ ፈራው የሚያመልከው የጻድቃን ነፍሳት በአንተ አምነ ው ጸንተው ይኖራሉ፡፡ ነፋሳት እየነቀነቁ ያመጡትን የ . ጐርፉን ፈሳሽነት ጸጥ ያደረግክልን ክጥፋት አድነህ የ " ሕይወት ወደብ የሆንከን የዘላለም ደኅንነት አለኝታ ያ ለበት መማፀኛ በባሕር የተጨነቁትን የምታድን በደረቅ በምድረ በዳም ያሉትን የምታድን በጽኑ ግዞት ቤት ካሉትም ጋራ አብረሃቸው የምትኖር ከሞት ማሠሪያ (ከኀጢአት ከክህደት) የፈታሐን የለየኸን ችግረኞችን የ ሚያለቅሱትንም የሚያረጋጋቸው ደስ የሚያሰኛቸው የደከሙትንም በመስቀሉ የሚያድን ከአመንበት ከእኛ መዓቱን ሁሉ የሚያርቅ ነቢያት ሐዋርያት በኅቡእ ያመሰገነህ አቤቱ አንተን እናመሰግናለን፡፡ ለአንተ ምስ ጋና እናቀርባለን፡፡ አንተን አምነን በመንግሥተ ሰማያ ት እናርፍ ዘንድ ፈቃድህንም እየሠራን በትእዛዝህም ጸንተን እንኖር ዘንድ መኖርን ስጠን፡፡ ሁሉን በቸርነትህ ጎብኝ፤ ትንንሾችንም ትልልቆችንም ገዢውንና ሕዝ ቡንም ጠባቂ የሚሆን ንጉሡንም ሠራዊቱንም ጠብቅ።"
ኪዲን ዘነግ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
፲፪ኛ ዓመት በዓለ ሢመተ ፓትርያርክ
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፲፪ኛ በዓለ ሢመት ዛሬ የካቲት ፳፬ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በመከናወን ላይ ይገኛል።
መዋለል
ልቡና ከሃይማኖት ሲለይ ዋለሌ አውታታ ይሆናል።
ልቡና በሃይማኖት ሲጸና በተስፋ የተሞላ ይሆናል።
እንደ ውኀ ስፍር ቅርጽ በሌለው ሀሳብ መዋተት የአማኝ ባሕርይ አይደለም።
አማጽ የሚቆምበት ጽኑ የሀሳብ አለት ያለው፣የሚያልፍ ነፋስ የማይወዘውዘው፣የሚያልፍ ጎርፍ የማይንደው ልብ ነው።ማቴ.፯፥፳፭
ዋለሌ ሰው ግን በድቡሽት መሬት ላይ እንደታነጸ ቤት በትቂት ጎርፍ እና ነፋስ ስለሚቦረቦር ቋሚ ጠባይ የለውም።
ዋለሌ ሰው ዛሬ ሌላ ነገ ሌላ ነው።
በጽኑዕ ልቡና ያለ ሰው ግን ዛሬም ሆነ ነገ ያው እርሱ ነው።
"ስለዚህ ይህን ቃሌን ሰምቶ የሚያደርገው ሁሉ ቤቱን በዓለት ላይ የሠራ ልባም ሰውን ይመስላል።ዝናብም ወረደ ጎርፍም መጣ ነፋስም ነፈሰ ያንም ቤት ገፋው በዓለት ላይም ስለ ተመሠረተ አልወደቀም።ይህንም ቃሌን ሰምቶ የማያደርገው ሰው ሁሉ ቤቱን በአሸዋ ላይ የሠራ ሰነፍ ሰውን ይመስላል።ዝናብም ወረደ ጎርፍም መጣ ነፋስም ነፈሰ ያንም ቤት መታው፥ ወደቀም። አወዳደቁም ታላቅ ሆነ።"ማቴ.፯፥፳፳፬-፳፯ እንዲል።
መልካም ቀን🙏
✨🍃✨🍂✨🍃✨🍂✨🍃✨🍂✨
ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ለዐቢይ ጾም ሁለተኛው እሑድ በአዘጋጀው ምስጋና አማካኝነት ዕለቱ ‹‹ቅድስት›› የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ ትርጉሙም
‹‹የተለየች፣ የተመረጠች፣ የከበረች›› ማለት ነው። መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ገጽ ፯፻፹፬ቅድስት የሚለው ቃል ዕለቱ ‹‹ቅድስት›› ተብሎ የተሰየመበት ምክንያት ስለ ዕለተ ሰንበት እንዲሁም ስለ እግዚአብሔር አምላክ ፍጹም ቅድስና የሚያወሳ በመሆኑ ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላክም ፍጥረታቱ የእርሱን ስም በማመስገን ይኖሩ ዘንድ ለቅድስና ሕይወት ፈጥሯቸዋልና በሰንበት እሑድ ክርስቲያኖች የቅድስና ተግባራትን ከሌላው ቀን አብዝተው ይፈጽማሉ፡፡ ዕለት ከተግባር፣ ስም ከክብር የተባበረባት ክብርት ሰንበት ቅድስት ስለሆነች ቅዱስ ያሬድ “ቅድስት” ብሎ ጠራት። ይኸውም የምትቀድስ፣ ከብራ የምታከብረን፣ አክብረናት የምንከብርባት በመሆኗ ነው። ለዚህም ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓ
“ግነዩ ለእግዚአብሔር ወጸውዑ ስሞ ወንግርዎሙ ለአሕዛብ ምግባሮ፤ ሀቡ ስብሐተ ለስሙ፤ አክብሩ ሰንበተ ተገበሩ ጽድቀ፤ ዝግቡ ለክሙ መዝገበ ዘበሰማያት ኀበ ፃፄ ኢያማስኖ ወኢይረክቦ ሰራቂ፤ ድልዋኒክሙ ንበሩ ዘበላዕሉ ጸልዩ ኀበ ሀሎ ክርስቶስ”ትርጉም፦
“ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ስሙንም ጥሩ፤ ሥራውንም ለአሕዛብ ንገሯቸው፤ ለስሙም ምስጋናን አቅርቡ ሰንበትን አክብሩ፤ እውነትንም አድርጉ፤ ብል የማያበላሸው ሌባም የማያገኘው በሰማያት ያለ መዝገብን ለእናንተ ሰብስቡ፤ ተዘጋጅታችሁም ተቀመጡ፤ ክርስቶስ ወዳለበት ወደ ላይ አስቡ፡፡“ስለዚህ ሰው ሰንበትን አክብሮ ጾሞ ጸልዮ፣ ቅድስናን ጠብቆ መኖር እንዲችል እግዚአብሔር የፍቅሩ መገለጫ የሆኑ ትእዛዛቱ ይነግሩናል። ተጨማሪ ያንብቡ ✨🍃✨🍂✨🍃✨🍂✨🍃✨🍂✨
👉👉👉 ተንሥኡ ለጸሎት 👈👈👈
እነዚህ ሁለት የግእዝ ቃላት ሁለቱም የራሳቸው መነሻ ግስ አላቸው።
ተንሥኡ ተንሥአ ተነሳ ካለው ግስ የወጣ ሲሆን ተነሱ የሚል ትርጉም አለው።
ለ አገባብ ስትሆን ፍቺዋ ለ ነው።
ጸሎት ጸለየ ለመነ ካለው ግስ የተገኘ ሲሆን ልመና ማለት ነው።
ስለዚህ በጠቅላላ ትርጉሙ ለጸሎት ተነሱ ይሆናል። ቃሉን ስናየው ከመጸለያችን በፊት መነሳት እንዳለብን ያስረዳናል። ይህንንም ትንቢተ ዮናስ 1÷6 ለይ <ተነስተህ አምላክህን ጥራ።> ብሎ ከመጸለይ በፊት መነሳት እንዳለበት ለነቢዩ ዮናስ ከተነገረውን ቃል ጋራ አንድ ሆኖ እናገኘዋለን። ስለሆነም ከመጸለይ አምላክን ከመጥራት ከመለመን ከመጾም ከመስገድ በፊት መነሳት አለብን። ከምንድነው የምንነሳው? የሚለውን ስናይ ያው በቀጥታ ፍቺው ከተኛንበት አልጋ ከተቀመጥንበት ወንበር ነው። ቆሞ መጸለይ እንዲገባ መፅሐፍ ያዝዛልና። ምስጢራዊ ትርጉሙ ግና ከተኛንበት የኃጢአት አልጋ በንስሐ እንንቃ። ከተቀመጥንበት የስንፍና ወንበር እንነሳ ማለት ነው። አሁን ያለነው የመጀመሪያው የጾሙ ክፍል በሆነው በዘወረደ ቅዳሜ ነው። ነገ ቅድስት ሳምንት ይገባል። ታዲያ በመሸጋገሪያው የጾም ሳምንት በመዘጋጃው የጾም ጊዜ ስንቶቻችን ከኃጢአት ከስንፍና ከቸልተኝነት ተነስተናል። ውዶችዬ የመዳን ቀን ዛሬ ያውም አሁን ነው። ነገ የእኔ የአንተ የአንቺ ላትሆን ትችላለች። ነገ ማለታችንን ትተን ዛሬን እንኑር። ከተኛንባቸው የኃጥያት የስንፍና አልጋዎች ነቅተን ነገ ሳንል ዛሬ ያውም አሁን ንስሐ እንግባ። ምናልባትም ይህንን እድል ድጋሜ አናገኘው ይሆናል። ስለዚህ እንነሳ። የዲያቆኑን አዋጅ ሰምተን ከመቀመጫችን ብቻ ሳይሆን ከኃጢአታችንም እንንቃ።
👏👏👏 ለጸልት ተነሱ👏👏👏
በትምህርት ሚኒስቴር በኩል ወደ እንግሊዝ ሀገር ኦክስፎርድ ኦስሄትሮፕ የሚባል የካቶሊክ ኮሌጅ በ1961 ዓ.ም ተልከው በእንግሊዝ ሀገር ለአራት ዓመታት ትምህርታቸውን ተከታትለው (Bachelor of Divinity in Basic Philosophy Super mental and Developmental Psychology) ዲግሪ ተቀብለው ወደ ሀገራቸው ተመለሱ፡፡
ከሀገርና ከቤተክርስቲያን የተቀበሉትን ታላቅ አደራ አክብረው ሀገራቸውን ለማገልገል በውጭ ሀገር የቀሰሙትን ሥልጣኔና ልምድ ለሀገራቸው የሚያውሉ ምሁራን በርካታ ናቸው፡፡ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ካፈራቻቸው ሊቃውንት መካከል አንዱ ናቸው፡፡ ብፁዕነታቸው በምዕራቡ ዓለም በትምህርት ቆይታቸው በትምህርትና በልምድ ያካበቱትን ዕውቀት በተግባር ላይ ለማዋል የቻሉ ምሁር ናቸው፡፡ በዚህም መነሻ የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል አስተዳዳሪ፣ የሰበታ ቤተ ደናግል የበላይ ኀላፊና የቦርድ አባል ሆነው አገልግለዋል፡፡ በባሕል ሚኒስቴርም በቋንቋ ጥናት አካዳሚ ውስጥ መርሐ ልሳን ተብሎ በሚታወቀው ክፍል በመምህርነት ሠርተዋል፡፡
በተፈሪ መኰንን ት/ቤት ውስጥ ከውጭ ሀገር በልዩ ልዩ ምክንያት ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ኢየሱሳውያን ያስተምሩ ስለነበር ብዙ ጊዜ የሃይማኖት ግጭት ይፈጠር ነበር፡፡ አንዳንዶቹ ተማሪዎች በመንፈሳዊ ዕውቀታቸው ጠንካሮች ስለነበሩ በሚያቀርቡት ጥያቄ በተማሪዎቹና በመምህራን መካካልም በየጊዜው ግጭት ይፈጠራል፡፡ ዐፄ ኃይለ ሥላሴም ጉዳዩን ሲያጣሩ የግብረ ገብነት መምህር እንደሌላቸው በተማሪዎቹ ስለተነገራቸው በአባ ሐና አቅራቢነት በዚያን ጊዜ ስማቸው አባ መዐዛ ቅዱሳን ወደ ጃንሆይ ቀርበው በግብረ ገብነት መምህርነት እንዲቀጠሩ ስለፈቀዱ ለተፈሪ መኮንን ት/ቤት የግብረ ገብ መምህር ሆነው ተቀጥረው ከ1949 ዓ.ም እስከ 1954ዓ.ም ድረስ በግብረ ገብነት አስተማሪነታቸው አገልግለዋል፡፡
ብፁዕነታቸው በተፈሪ መኮንን ት/ቤት እያስተማሩ የምስካዬ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም በተጓዳኝ በትምህርት ቤቱ ግብረ ገብ የሚያስተምሯቸውን ተማሪዎች ሰፋ ያለ የሃይማኖት ትምህርት የሚቀስሙበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ሲሉ በምስካዬ ኅዙናን መድኃ ኔዓለም ገዳም ወጣቶችን ስለሃይማኖት ማስተማር ጀመሩ፡፡ የዚህ አገልግሎት ፍጻሜም አንጋፋውን የተምሮ ማስተማር ሰንበት ት/ቤት ለመመሥረት አብቅቶታል፡፡ ብፁዕነታቸውም የዚህ ሰንበት ት/ቤት ከመሥራቾቹ አባላት አንዱ ናቸው፡፡ ብፁዕነታቸው በወቅቱ ለምስካዬ ኅዙናን መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ቋሚ ሰባኬ ወንጌል በመሆንም አገልግለዋል፡፡
ቅድስት ቤተክርስቲያን በሬዲዮ ትምህርት በምታስተምርበት ወቅት፤ አባ መዐዛ ቅዱሳን (የአሁኑ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል) በርቱዕ አንደበታቸው በብሥራተ ወንጌል ሬዲዮ “ማኅበራዊ ኑሮ በቤተክርስቲያን'' እና “የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት” በተሰኙ አርእስተ ትምህርት ይሰጡ ነበር፡፡ ብፁዕነታቸው በሕይወት ዘመናቸው ካከናወኗቸው ተግባራት ለምእመናን በሬዲዮ ስብከተ ወንጌልን በማስተላለፍ የሰጡት አገልግሎት ከፍተኛ ደስታ እንደፈጠረላቸው ይናገሩ ነበር፡፡
በአርሲ ሀገረ ስብከት ከ1975 ዓ.ም ጀምሮ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በመሆን ለ33 ዓመታት አገልግለዋል፡፡ በአርሲ ሀገረ ስብከት ቆይታቸውም በምእመናን የሚወደዱና የሚከበሩ ታላቅ አባት ነበሩ፡፡ ወደ አርሲ ሀገረ ስብከት በመጡበት የመጀመሪያ ሳምንታት ውስጥ በሀገረ ስብከቱ ውስጥ ያሉትን ዐበይት ችግሮች ካጠኑ በኋላ በሀገረ ስብከቱ ውስጥ አንድም የወጣቶች እንቅስቃሴ የሚደረግበት አጥቢያ አለመኖሩንና ሰንበት ት/ቤቶችም የተዘጉና ወጣቶችም በቤተክርስቲያን አካባቢ እንዳይታዩና ከፍተኛ ክትትልና ቁጥጥር ይደረግባቸው እንደነበረ ካወቁ በኋላ የተሾምነው ምእመናንን ልንጠብቅ ነው እንጂ ልንበትን አይደለም፤ በቤተክርስቲያን ላይ ማንም ሊያዝዝ አይችልም ስለቤተክርስቲያን ኃላፊነቱ የእኛ ነው" በማለት አቋማቸውን በአደባባይ ከመግለጻቸውም በላይ በዘመኑ በሥልጣን ላይ ከነበሩት የደርግ ሹማምንት ፊት ለፊት በመጋፈጥ ልጆቻቸውን ከጥቃት ታድገዋል፤ ተቋርጦ የነበረው የሰንበት ትምህርት ቤት እንዲቀጥል አድርገዋል፡፡
ብፁዕነታቸው የነገይቱ ቤተክርስቲያን ተረካቢ ወጣቶች መሆናቸውን ጠንቅቀው የሚያውቁ ስለሆነ በሀገረ ስብከታቸው ውስጥ ባሉ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ለወጣቶች ልዩ ትኩረት በመስጠት ሰንበት ትምህርት ቤቶች እንዲጠናከሩ አድርገዋል፡፡
ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ወደ አርሲ ሀገረ ስብከት ተመድበው ሲመጡ የነበሩት አብያተ ክርስቲያናት ቁጥር 117 ብቻ የነበሩ ሲሆን እርሳቸው በሕይወት በነበሩባቸው ዘመናት ከ300 በላይ አዳዲስ አብያተ ክርስቲያናትን በማስከተል ምእመናን በርቀት ምክንያት ሳይንገላቱ በአቅራቢያቸው ከቤተክርስቲያን አገልግሎት ተሳትፎ እንዲኖራቸው ከማድረጋቸውም በላይ ሁሉም አብያተ ክርስቲያናት የይዞታ ማረጋገጫ እንዲያገኙ አድርገዋል::
ብፁዕ አቡነ ናትናኤል በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ዕረፍት ምክንያት ከነሐሴ ወር 2004 ዓ.ም አጋማሽ ጀምሮ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ተመርጠው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ሆነው እስከተሾሙበት የካቲት 24 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ በዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክነት ቅድስት ቤተክርስቲያን በመምራት አባታዊ ግዴታቸውን ተወጥተዋል፡፡
ብፁዕነታቸው ባደረባቸው ሕመም ምክንያት የካቲት 21 ቀን 2008 ዓ.ም ዐርፈው ሥርዓተ ቀብራቸው የካቲት 24 ቀን 2008 ዓ.ም በደብር ቅዱስ ደብረ መዐዛ ኣቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም^ ተፈጽሟል፡፡
የብፁዕ አባታችን በረከታቸው ይደርብን፡፡
አሜን!!!
መልአከ ሰላም አባ ኪሮስ ወልደአብ
ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ሊቀ ጳጳስን እንዘክራቸው
(ከ1923-2008 ዓ.ም)
#Ethiopia | የቀድሞ አባ መዐዛ ቅዱሳን የኋላው ብፁዕ አቡነ ናትናኤል በምሥራቅ ትግራይ ክለተ አውላሎ አውራጃ አውዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አጥቢያ ከአባታቸው አቶ ገብረ ሕይወት ፀዓዱ እና ከእናታቸው ወይዘሮ ወለተ ክርስቶስ ቢሻው ግንቦት 12 ቀን 1923 ዓ.ም ተወለዱ፡፡ ወላጆቻቸው ልጆችን እየወለዱ በተደጋጋሚ ይሞቱባቸው ስለነበር በጭንቀት ውስጥ ሳሉ ነው ብፁዕነታቸው የተወለዱት፡፡
አባታቸው ገና በጨቅላነታቸው በመሞታቸው በእናታቸው ዘንድ በስስት እየታዩ ነው ያደጉት፡፡ ከዚህም የተነሣ ባለቤታቸውንና ልጆቻቸውን ያጡት እናትም የሁሉም ምትክ የሆኑት ልጃቸውን ካሣዬ ብለው ስም አወጡላቸው፡፡ ትንሹ ካሣዬም የእናታቸውን ፍቅር ሳይጠግቡ፤ እናትም በስስት የሚመለከቱትን የልጃቸውን ስም ጠርተው በዐይናቸው አይተው ሳይጠግቡ በለጋነት ዕድሜያቸው እናታቸውን በሞት ተነጠቁ፡፡ እናታቸው በልጅነታቸው በማረፋቸው ምክንያትም ከእኅታቸው ጋራ መኖር ጀመሩ፡፡ የእኅታቸው ፍላጎት ከብት እንዲጠብቁ፣ ዕድሜያቸው ለአቅመ አዳም ሲደርስም በሕግ በትዳርተወስነው እንዲኖሩና እያረሱ በግብርና ኑሮአቸውን እንዲገፉ ነበር፡፡
የካሣዬ ሐሳብ ደግሞ ከአድማስ ባሻገር ነበር፡፡ ይኸውም በአካባቢያቸው ባሉት አብያተ ክርስቲያናትን እንደሚመለከቱት ሁሉ ከሊቃውንቱ እግር ሥር ቁጭብሎ መማር፣ ቤተክርስቲያንን ማገልገል፣ ጉባኤ አስፍቶ ወንበር ዘርግቶ ማስተማር ነበር ::
ብፁዕነታቸው አባቴ በጣም መንፈሳዊ ሰው ነበሩ፡፡ ከልጅነቴ ጀምሮ አባታችን እያሉ ይጠሩኛል ስለእኔ ግን ትንቢት ተናግረዋል፡፡ አንዳንድ ሰዎችም ትልቅ አባት ይሆናል ብለው ይናገሩ እንደነበረ ነግረውኛል፡፡ በወቅቱ እኔ ልጅ ስለነበርኩ ይናገሩት የነበረውን አላስታውሰውም በማለት ተናግረዋል፡፡
የትምህርት ፍላጎታቸውን ለመወጣት ወደ አለቃ መብራቴ ዘንድ በመሔድ በአቡነ አሳይ ቤተክርስቲያን ንባብና የቃል ትምህርት ጀመሩ፡፡ የኔታ ሰሎሞን የሚባሉ የአቋቋም መምህራቸው ያላቸውን የትምህርት ፍላጎት በመረዳት፤ ነገ ለቤተክርስቲያን የሚጠቅሙ ሆነው ስለታዩአቸው ወደ ሌላ ሔደው እንዳይሰናከሉ በማሰብ ከእርሳቸው ዘንድ እንዲማሩ ስለሚፈልጉ ርቀው ወደ ቆሎ ትምህርት ቤት እንዳይሔዱ አይቀጡ ቅጣት ቀጥተው ሦስት ዋስ አስጠርተዋቸው በዚያው እንዲቆዩ አደረጓቸው፡፡
በልጅነታቸው አባትና እናታቸውን ያጡት ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ግን ልባቸው ለትምህርት አድልቷልና ቤተክርስቲያንን እናት፣ እግዚአብሔርን አባት አድርገው ከተወለዱበትና ከአደጉበት ወላጆቻቸውንም ካጡበት ቀዬአቸው ትምህርትን ፍለጋ ለመኮብለል ወሰኑ፡፡ ስለዚህም ተጨማሪ ትምህርት ለመቅሰም
ከመምህራንና ከቤተሰቦቻቸው ተደብቀው በጥንቱ ቆሎ ተማሪ ልማድ ስማቸውን ቀይረው ጎጃም (በጌምድር) ትምህርት ፍለጋ ተሰደዱ፡፡ በቆሎ ትምህርት ቤትም መዐዛ ቅዱሳን ተብለው ተጠሩ፡፡
ወደ ጎንደር እና ጎጃም ተሻግረው ከየኔታ ኃይሉ ስሜ በየላ ኢየሱስ፣ ከየኔታ መኰንን ላስታ አመራ ማርያም ከእነዚህ ከሁለቱም ጾመ ድጓና ምዕራፍ ከተማሩ በኋላ እንደገና ወደ ቅኔ ቤት ገቡ፡፡ ክህነት የተቀበሉትም ሁለት ጊዜ ምዕራፍና ጾመ ድጓ ዘልቀው ቅኔ እስከ ዘእይዜ ከቆጠሩ በኋላ ነበር፡፡ በደቡብ ጎንደር እና ወሎ ተዘዋውረውም በጉባኤ ቤቶች የዜማ፣ የአቋቋም ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፡፡ የሰሜን ጎንደር ደባርቅ ወረዳ ደረስጌ ማርያም አቅንተውም ከየኔታ መንበሩ ዘንድ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፡፡ የቅኔ ዕውቀታቸውን ለማስፋፋትም ከአዲስ አበባ ስማዳ ወረዳ ደብረ ዕንቁ በማምራት ከታላቁ ሊቅ ከየኔታ ጌጡ ዘንድ ተምረዋል፡፡ የብሉይ ኪዳንና ዐራቱን ብሔረ ኦሪትና ዳዊት ትርጓሜን ተምረዋል፡፡
ቅዱሳት መጻሕፍትን ለመማር አዲስ አበባ በሚገኘው ታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም ገብተው ሐዲሳትን በመጀመሪያ ከመጋቤ ሐዲስ ወ/ሚካኤል፣ ከመ/ር ገብረ ማርያም ዓለሙ፣ ቅዳሴ ማርያምና ውዳሴ ማርያም ከመምህር ይኄይስ፣ ኪዳን ትምህርተ ኅቡዓት ከመምህር ከየኔታ ገብረ ማርያም፣ ከመምህርገብረ ሕይወት ፍትሐ ነገሥት ተምረዋል፡፡
ለራሳቸው እየተማሩ ከቤታቸው ያሉትን ተማሪዎች እያስተማሩ ቆይተዋል፡፡ የመጻሕፍት ተማሪ ሆነው መጻሕፍተ ሐዲሳትን እየተማሩ ሌሊት ከማቴዎስ ወንጌል ጀምሮ እስከ ራእየ ዮሐንስ መጨረሻ ድረስ እንዲሁም ትርጓሜ ፍትሐ ነገሥትን በእጃቸው ጽፈዋል፡፡ መዝሙረ ዳዊት ትርጓሜን በቀዳማይ ኃይለ ሥላሴ ፊት እንዲተረጉሙ ተፈቅዶላቸው በሚገባ በመወጣታቸው ከንጉሠ ነገሥቱ እጅ ሽልማት ተቀብለዋል፡፡
ዓላማቸው በተመረቁበት በሐዲሱ ተማሪ አብዝተው ጉባኤ አስፍተው ማስተማርነበር፡፡ ነገር ግን በቅድስት ሥላሴ መምህራን ማሠልጠኛ እድል አግኝተው ለሁለት ዓመታት ትምህርታቸውን ተከታትለው በዲፕሎማ ተመርቀዋል፡፡
ቅኔ ቤት ገብተው ከየኔታ መንበሩ ደረስጌ ስሜን ጃና አሞራ ገብተው ሲማሩ አንድ ዘመዳቸው “ምሰሶ ታቃፊ ሆነህ እንዳትቀር ዲቁና ተቀበል" ያላቸው ትዝ እያላቸው ዲቁና የተቀበሉት ካደጉና ከተማሩ በኋላ ነው፡፡ ይኸውም ከጎንደር ሸዋ (አዲስ አበባ) ድረስ በእግራቸው ተጉዘው በመምጣት በሚያዝያ ወር በ1938 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም ከአቡነ ይስሐቅ ዲቁና ተቀብለዋል፡፡
አቡነ ባስልዮስ በጸመ ፍልሰታ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ይዘዋቸው በመሔድም ውዳሴ ማርያም እና ቅዳሴ ማርያም እየተረጎሙ እዚያው ከርመው ሦስቱን ታላላቅ መዓርጋት ቅስና፣ ምንኲስና ቁምስና በ1953 ዓ.ም ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ ተቀብለዋል፡፡
ጵጵስና ጥር 13 ቀን 1971 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለሃይማኖት ለኤጲስ ቆጶስነት ከተመረጡት 13 አባቶች መካከል አንዱ ሲሆኑ፤ የትግራይ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሆነው ተሾሙ፡፡ በትግራይ ሀገረ ስብከትም እስከ 1975 ዓ.ም አገልግለዋል፡፡
ዘመናዊ ትምህርት ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ወደፊት ጵጵስና የሚሾሙ ሰዎች ውጭ ሀገር ሔደው የውጭውን ትምህርትና ልምድ እንዲቀስሙ ያስፈልጋል በማለት ለአቡነ ባስልዮስ አሳሰቧቸው፡፡ ሊቃውንት ሲመረጡም በንጉሡ አማካይነት ተጠቁመው ውጪ ሀገር ከሚሔዱት መካከል አንዱ ሆኑ፡፡
አባ መዐዛ ቅዱሳን በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ትምህርት በቂ ችሎታ አላቸው ከሚባሉ መምህራን አንዱ ናቸው፡፡ እኒህ የቤተክርስቲያን ሊቅ ዕውቀታቸውን በበለጠ በዓለም ዐቀፍ ቋንቋ ለማሻሻል ባላቸው ፍላጎት መሠረት ወደ ኢየሩሳሌም አንግሊካን ቤተክርስቲያን ሴንት ጆርጅ ኮሌጅ ተላኩ፡፡ ወደፊት ጵጵስና የሚሾም ብለው ጃንሆይ በተናገሩት መሠረት የኤጲስ ቆጶስነት ትምህርት እንዲሠለጥኑ ነበር የተላኩት፡፡ ሁለት ዓመት ተኩል የቤተክርስቲያን አስተዳደር(Church History and Administration) ተምረው ተመለሱ፡፡ ከውጭ ሀገር እንደተመለሱ ከ1951-1960 ዓ.ም በተማሩት ትምህርት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የካህናት አስተዳደሪ ሆነው ቤተክርስቲያንን በማገልገል ምእመናንን በማስተማር ሐዋርያዊ ግዴታቸውን ሲፈጽሙ ቆይተዋል፡፡
በዚሁ መካከል በ1958 ዓ.ም የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ምክትል አስተዳዳሪ ሆነው ተሹመዋል፡፡ የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ምክትል አስተዳዳሪ ሆነው እንኳን በበጎ ፈቃደኝነት ምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም እየተመላለሱ ያስተምሩ ነበር፡፡ በኋላም በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ዋና አስተዳዳሪ በመሆን አገልግለዋል፡፡
