ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Kanalga Telegram’da o‘tish
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Ko'proq ko'rsatish669
Obunachilar
-124 soatlar
+37 kun
Ma'lumot yo'q30 kun
Postlar arxiv
✨✨✨🍁🍁✨✨✨🍁🍁✨✨✨🍁🍁
✨የንጉሥ ግብዣ አለ ተጠርተሃል እንዳትቀር✨
ወደ ቤተክርስቲያን አዘውትራችሁ የምትመጡ ይህን ልመናዬን ስሙ፤ ሰነፍ የኾኑትን ወደ ቤተ ክርስቲያን የመሄድን አስፈላጊነት አስተምሯቸው፡፡ የትምህርቷን ውበት ቀምሳችኋልና እናንተ ያወቃችሁትን ሳያውቁ እንዳይቀሩ፡፡
ቤተክርስቲያን ሀኪም ቤት እንጂ የነፍስ ፍርድ ቤት አይደለችም። የኃጢአትን ስርዬት ትሰጣለች እንጂ ኃጢአትን አትፈርድም፡፡
በቤተክርስቲያን ውስጥ እንደምናገኘው ምስጋና በሕይወታችን ውስጥ እንደዚህ ያለ አስደሳች ነገር የለም፡፡ በቤተክርስቲያን ውስጥ፣ ደስተኞች ደስታቸው ይበዛላቸዋል፡፡ የሚጨነቁት፤ ያዘኑት፣ ሰላምን ያገኛሉ፡፡ በቤተክርስቲያኑ ውስጥ፤ የተቸገሩ ሰዎች እፎይታ ያገኛሉ፤ ኹሉም ከተሸከሙት ያርፋሉ፡፡
ቤተክርስቲያን ኹሉን ታቅፋለች፡፡ ውስጥ ከሆንክ ተኩላው አይገባም፣ ብትሄድ ግን አራዊቶች ይይዙሃል፡፡ ከቤተክርስቲያን አትራቅ፣ ከቤተክርስቲያን የሚበልጥ ምንም ነገር የለም። ቤተክርስቲያን ተስፋህ ናት፡፡ ቤተክርስቲያን መዳንህ ናት፡፡ ቤተክርስቲያን ከሰማያት ከፍ ትላለች፡፡ ቤተክርስቲያን ከድንጋይ ትከብዳለች፡፡ ቤተክርስቲያን ከአለም ትስፋለች፡፡ ቤተ ክርስቲያን አታረጅም፣ ነገር ግን ሁልጊዜ እራሷን ታድሳለች፡፡
"እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበዳችሁ፤ በመከራና በኃጢአታችሁ የከበደ ኹሉ' ወደ እኔ ኑ" ይላል እግዚአብሔር፤ እኔም አሳርፋችኋለሁ፡፡" ማቴ ፲፩፥፳፰ይህንን ድምጽ ከመስማት የበለጠ ምን ደስታን ሊሰጠን ይችላል? ከዚህ ግብዣ የበለጠ ጣፋጭ ምንድነው? ጌታ ወደ ቤተክርስቲያን የሚጠራችሁ ለታላቅ ግብዣ ነው፡፡ ከትግል ወደ እረፍት፣ ከስቃይ ወደ እፎይታ ያሸጋግራችኋል፡፡ ከኃጢአታችሁ ሸክም ያገላግላችኋል፡፡ ጭንቀትን በምስጋና፣ ሀዘንንም በደስታ ይፈውሳል፡፡ ለክርስቶስ ከሚኖረው በቀር በእውነት ነጻ፣ በእውነት ደስተኛ የሆነ ማን ነው? እንዲህ ያለው ሰው ክፋትን ኹሉ ያሸንፋል ምንም አይፈራም! ቤተ ክርስቲያን ለኹሉም መጠጊያ ሆና ቆማለች፡፡ የአምላክን ትዕዛዝ የምትፈጽም መልካም ሰው ከሆንክ ቅድስናህን ለመጠበቅ ግባ፤ ኃጢአተኛ ከሆንህ መዳንን ለማግኘት እርምጃህን ፈጠን አድርገው:: የቤተክርስቲያንን ትምህርት ሳይሰሙስ እንዴት ነፍስን ወደ መልካም መንገድ መምራት ይቻላል? የእግዚአብሔር ቃል 'ብርሃን' በመባል ይጠራል፤ ፀሐይ ከምታፈልቀውና እኛም ከምናየው ብርሃን፣ እጅግ በጣም የከበረ ብርሃን፣ የነፍሳችንን ጥልቀት የሚያበራ ነው፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስ ስለዚህ እውነት እንዲህ ሲል መስክሯል፣ “በጨለማ የሄደ ሕዝብ ብርሃን አየ፤ በሞት ጥላ አገርም ለኖሩ ብርሃን ወጣላቸው::" ከእናንተ መካከል በታማኝነት ቤተ ክርስቲያን የምታገለግሉ፤ 'ስራ በዛብኝ፣ ልመጣ አልችልም' እንዳይሉ ሌሎቹን ምከሩ፡፡ ወደ ንጉሱ ግብዣ የተጋበዙ ግን መምጣት ያልቻሉትን እንደ ምሳሌ እንመልከት፡፡ አንደኛው አምስት ጥማድ በሬዎችን ሊገዛ እንደሄደ ተናገረ፣ ሌላው አዲስ መሬትን ሊገዛ እንደሄደ ሲናገር ሌላው ደግሞ ሚስት ማግባቱን ተናገረ፡፡ ምክንያታቸው ምንም ይሁን ምን፣ ንጉሡ ግብዣውን ንቀው ስለቀሩ የሚታገሳቸው ይመስልሃል? እናም ንጉሡን በሰበብ አስባቡ አታናዱት፡፡ ከጊዜህ ላይ አንድ ሰዓት ያህል እንኳን መቆጠብ ያቅትሃል? ቤተክርስቲያንን ከተሳለሙ በኋላ ወደ ሥራ መሄድ በእውነት ይህን ያህል ከባድ ነውን? አንድ ሰው ወርቅ፣ ብር፣ ማር ወይም ወይን በነጻ እየሰጠ ነው ቢባል፤ ማንም ሳይቀድማችሁ ለመድረስ አትቸኩልም? ነገር ግን፣ ከወርቅ የሚበልጥ፣ ከማርም ከወተትም የሚጣፍጠውን የእግዚአብሔርን ቃል ለማድመጥ ወደ ቤተክርስቲያን የምትመጡት አልፎ አልፎ ነው፡፡ ስለዚህም፣ ይህን ችላ ማለታችሁን አውግዣለሁ፤ ለእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ያላችሁን ግድየለሽነት እቃወማለሁ፡፡ ከመንፈሳዊ ትምህርቶቿ በመራቃችሁ፣ በውስጣችሁ የእግዚአብሔር ፍራቻ የለም፤ እግዚአብሔርን የማትፈራ ነፍስም ለኃጢአት የተገዛች ትሆናለችና ነፍሳችንን እንጠብቃት፡፡ 📚የነፍስ ምግብ 📝ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ✨✨✨🍁🍁✨✨✨🍁🍁✨✨✨🍁🍁
✨✨✨🌿
"ከፊትህ አንድ መመሪያ አስቀምጥ፤ ይህም በመንፈሳዊ ሕይወታህ ውስጥ የምትዋጋው ታላቁ ውጊያ፣ ከራስህ ጋር የምታደርገው ውጊያ ነው፤ ወደ ኅሊናህ የሚገባውን ማንኛውንም ዓይነት ክፉ ፍላጎት ተሸክመኸው አትዙር፤ ልትቆጠብ የማትችል ከኾነ ጉዳዩን ለጊዜው አራዝመው፤ ከዚህ በኋላ ጉዳዩን መላልሰህ ለማራዘም ራስህን አስገድደው፤ በማራዘም ውስጥ የእግዚአብሔር ጸጋ ስለሚጎበኝህ እርሱ ያጽናናሃል...
በመንፈሳዊ ትጋትህ ውስጥ ቸልተኝነትህን፣ ግዴለሽነትህን እና ቁም ነገር ማጣትህን የሚገልጹ የተለያዩ ነገሮችን ወደ አንተ እንዲመጡ አትፍቀድ።"
📚መንፈሳዊ መንገድ -
🖋ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ፤
🖋ትርጒም በአያሌው ዘኢየሱስ
✨✨✨🌿
በክብረ በዓሉ ያሬዳዊ ዜማ በአጫብር በሊቃውንት ቀርቧል።
የየረር ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምሕርት ቤት ዘማርያንም የአጫብር ወረብ አቅርበዋል። “ተቀጸል ጽጌ” (አበባን ተቀዳጀ) የሚለውን መዝሙር የዜማን የቅኔ መሥራች የሆነው ኢትዮጵያዊው ቅዱስ ያሬድ ነው፡፡ የተመሠረተውም በ፮ኛው መ/ክ/ዘ መጀመሪያ በዐፄ ገብረ መስቀል ዘመነ መንግሥት ነው፡፡
በዚሁ መሠረት የክረምቱና የልምላሜው ጊዜ አልፎ የአበባውና የፍሬው ጊዜ በሚተካበት በመስከረም ፳፭ ቀን ቅዱስ ያሬደ ውደ ንጉሡ ዙፋን ቀረቦ “ተቀጸል ጽጌ ገብረ መስቀል ዐጼጌ” በማለት ዘምሯል፡፡
ዐፄ ገብረ መስቀል ክረምቱ አልፎልሃልና አበባን ተቀዳጅ፣ አበባን ተላበስ እያለ ያወድሰው የነበረው በዓላዊ ትውፊት እየተቀባበለ እስከ ፲፭ኛው ምዕት ዓመት ደርሶ ነበር፡፡ በኋላም ዐፄ ዳዊት የጌታችን ግማደ መስቀል ከኢየሩሳሌም አስመጥቶ መስከረም ፲ ቀን ወደ ኢትዮጵያ በመድረሱ ግማዱም በንጉሡ ምክንያት በመምጣቱ “ዐፄ መስቀል” እየተባለ መከበር ሲጀምር፣ የ፳፭ኛው ቀን የአበባው በዓልም በ፲፭ ቀን ወደኋላ በማፈግፈግ በአንድነት የዐፄ መስቀልና ተቀጸል ጽጌ እንዲከበር ተወስኖ እስካሁን ድረስ በታላቅ ሥነ ሥርዐት በመከበር ላይ ይገኛል፡፡
©eotc tv
+3
“ተቀጸል ጽጌ”(አበባን ተቀዳጅ) በዓል ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በተገኙበት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በመከበር ላይ ይገኛል።
ስከረም 10 ቀን 2017 ዓ.ም ( ፍ.እ.ሚ. አዲስ አበባ)
በዐፄ ዳዊት ዘመን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ግማደ መስቀሉ ወደ ኢትዮጵያ የገባበት “ተቀጸል ጽጌ”(አበባን ተቀዳጅ) በዓል መስከረም ፲ ቀን በየዓመቱ ይከበራል፡፡
በዘንድሮው ዓመተት በዓሉ ሲከበር ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፤ የባሕር ዳር እና ሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ; ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስን ጨምሮ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ; የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነትና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ኃላፊዎች የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ካህናት ምእመናን የሰንበት ትምሕርት ቤት ዘማርያን ተገኝተዋል።
" ተቀጸል ጽጌ / አጼ መስቀል "
'ተቀጸል ጽጌ' ማለት 'መስቀል ሆይ! በአበባ አጊጥ' እንደ ማለት ሲሆን 'አጼ መስቀል' ደግሞ አጼ ገብረ መስቀልን: አንድም አፄ ዳዊት ቀዳማዊን ይመለከታል:: ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
በሃገራችን ኢትዮዽያ የነገረ መስቀሉ ትምሕርት ከመጣ ጀምሮ መስቀል ይከበራል:: በአደበባባይ ግን እንዲከበር ያደረጉት የቅዱስ ካሌብ ልጅ አፄ ገብረ መስቀል ናቸው:: በወቅቱ ንጉሡ: ሠራዊቱ: ዻዻሱና ሕዝቡ በተገኙበት ቅዱስ ያሬድ "መስቀል መልዕልተ ኩሉ ነገር: ያድኅነነ እምጸር-መስቀል ከሁሉ ነገር በላይ ነው: ከጠላትም ያድነናል" እያለ ይዘምር ነበር::
የአበባ ጉንጉንም ለመስቀሉና ለንጉሡ ይቀርብ ነበር:: ከ800 ዓመታት በሁዋላም አፄ ዳዊት ግማደ መስቀሉን ባስመጡ ጊዜ መስከረም ቀን ተተክሎ ታላቅ በዓልም ሆኖ ተከብሯል::
© ዝክረ ቅዱሳን
🌿🌿🌿✨✨🌿✨✨🌿✨✨🌿✨✨✨
"ፈተና ሲገጥመን ውስጣችን ሊረበሽ ወይም በቀቢጸ ተስፋ ሊያዝ አይገባውም፡፡ ወርቅን የሚያነጥር ሰው በእሳት ውስጥ የጨመራትን የወርቅ ቅንጣት እዚያ ውስጥ ምን ያህል ጊዜ መቆየት እንዳለባት ያውቃል፤ መቼ ከእሳቱ ሊያወጣት እንደሚገባውም ያውቃል፡፡ እንዲሁ እስከ መጨረሻው በእሳቱ ውስጥ ተጥላ እንድትቀርና በዚያ እንድትቃጠል አይፈቅድም፡፡
🌿✨✨🌿
እግዚአብሔር ደግሞ ይህን ከወርቅ አንጣሪው በላይ ያውቃል፡፡ መቼ ከርኩሰታችን እንደምንነጻ ያውቃል፡፡ በመኾኑም ራሳችንን በመጣልና ተስፋ በመቁረጥ በክፋት ላይ ክፋት እየጨመርን እንዳንኼድ ሽቶ መቼ ከዚያ ፈተና እንደሚያወጣን ያውቃል፡፡
🌿✨✨🌿
ስለዚህ ድንገት ያላሰብነው ነገር ቢገጥመን በፍጹም የምናማርር፣ ወይም ተስፋ የምንቆርጥ ልንኾን አይገባንም፡፡ ከዚህ ይልቅ የእነዚህ ነገሮች ምንነትን የሚያውቅ እግዚአብሔርን መጠበቅ፣ እርሱ እስከ ፈቀደው ጊዜ ድረስም ልቡናችንን በእሳት እንዲፈተን ማድረግ ይገባናል። ምክንያቱም ይህ ነገር በእኛ ላይ እንዲኾን (እንዲመጣ) የፈቀደው ለእኛ ጥቅምና በዚያ ውስጥ ኾነን በምናሳየው ጥረት ይበልጥ ሊያከብረን ስለሚወድ ነው፡፡"
📝ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
📚ወደ ኦሎምፒያስ መጽሐፍ በ ገብረ እግዚአብሔር ኪደ
🌿🌿🌿✨✨🌿✨✨🌿✨✨🌿✨✨✨
✨✨✨🍀✨🍀🍀✨🍀🍀✨🍀✨✨✨
ራሱን የማይነቅፍ ሰው እርሱ ትክክል እንደሆነና እንዳልተሳሳተ አድርጎ ስለ ሚያስብ ምንም አይነት ስህተች ቢሰራ እንኮን ይቅርታ አይጠይቅም ።
ከወንድሙ ጋ ሲጋጭ ከእርሱ ጋር ለመታረቅ ራሱን አያነሳሳም ። እርቁ እንዲመጣ የሚፈልገው ከሌላ ወገን ነውና ።
✨✨🍀✨
ግን ለምን? ይህን የሚያመጣው ማንነት ነው! ሌላው ቢቀር እኔነቱ ምንም አይነት ስህተት እንዳልሠራ አድር ስለ ሚያሳምነው ስህተቱንም በእግዚአብሔር ፊት እንኳን አይናዘዝም ።
ራስን መንቀፋ የሚመጣው ከትህትና ሲሆን ትህትና ደግሞ ራስን ወደ መካድ ይመራል ። ትኁት ያልሆነ ሰው ራሱን አይነቅፋም አይኮንንም ። ሁልጊዜ የሚነቅፈው ሆነ የሚኮንነው ሌሎችን ነው እንዲ አይነቱን ሰው ለምንድነው ሌሎችን የምትነቅፈው ብለህ ብጠይቀው እንዲ ብላችሁ በመጠየቃችሁ ብቻ ይቀየማል ይገስፃችሀል።
✨✨🍀✨
ራሱን በዚህ ዓለም ሳለ የሚወቅስ ሰው በወዲያኛው አለም ከመወቀስ ይድናል ።
ሰው ራሱን ከሚወቅስበት ምክንያት አንዱ ወደ ንሰሀ ለመቅረብ ነው ። ንሰሐ ከገባ ደግሞ እግዚብሔር ኃጢአተኛ ይቅር ይለዋል ። ራሱን ከማክበር አንፃር ራሱን የማይወቅስ ሰው ግን ሳይሻሻል በኃጢአት ውስጥ በመውቀስ ይኖራል ።
ቅዱስ እንጦስ "እኛ ራሳችን ከወቀስን ዳኛው በእኛ ይደሰታል ።" ብሎ የተናገረው ምንኛ እውነት ነው። ከዚ በመቀጠልም "እኛ ኃጢአታችን የምናስታውሳቸው ከሆነ እግዚአብሔር በንሰሐ ይረሳልናል : እኛ ኃጢአታችን የማናስብና ንሰሀ የማንገባ ከሆነ እግዚአብሔር ያሰበዋል " በማለት ተናግሮአል ።
✨✨🍀✨
ይህን አስመልክቶ ቅዱስ መቃርስ የተናገረው አባባል ምነኛ ድንቅ ነው!
"ወንድሜ ሆይ! ሌሎች ሳይወቅሱህ አንተ ራስህን ውቀስ!"📝አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ 📚መንፈሳዊ ውጊያወች ✨✨✨🍀✨🍀🍀✨🍀🍀✨🍀✨✨✨
🎲 Quiz 'ፍኖተ ወንጌል ልዩ መንፈሳዊ የጥያቄና መልስ መርሐ ግብር"start the quiz"የሚለውን ይጫኑ"i am ready"ሲጫኑ ጥያቄው ይጀምራል።መልካም ዕድል🛎🛎🛎'
🖊 7 questions · ⏱ 30 sec
ልዩ መንፈሳዊ በፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት እየተዘጋጀ የሚቀርብ የጥያቄ እና መልስ መርሐ ግብር።ዘወትር በየሳምንቱ አርብ ምሽት ከ2:00 ⏰ ጀምሮ እስከ 4:00 ⏰ ድረስ ወደ እናንተ ይደርሳል። ይሳተፋ! ለኦርቶዶክሳውያን ሼር በማድረግ ይጋብዙ! የአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475
✨✨✨🌼✨🍀✨✨✨🌼✨🍀✨✨✨🌼✨🍀
🌼✨🍀ዕቅድህ ምንድነው?🌼✨🍀
ባለፈው ዓመት መጨረሻ ለዚህ ዓመት ልትሠራው ያቀድኸውን ስንቱን ሠራህ ያቀድኸውን ለመፈጸም ትቸገራለህ? ያቀድኸውን ትተህ ያላቀድከውን አድርገህ ታውቃለህ? ዕቅድ ወደ ራዕይህ ፍጻሜ ለመድረስ የምትሳፈርበት መርከብ ነው። በሚገባ ካልሄደልህ የራእይህን ፍጻሜውን አታየውም ማለት ነው። የሚመጣውም ዓመት ያቀድኸው እንዲሳካ ራዕይህን መርምረው። የት መድረስ ነው ምትፈልገውን ምን ሲኖርህ ነው ዕቅዴ ተሳካ የምትለው?
✨✨🌼
እያንዳንዱ ዓመታት ቢያሻህ መልአክ ካልፈለግህም ሰይጣን መሆን የምትችልባቸውን ዕድሎች የያዙ ናቸው። ቅዱስ ሚካኤል የተሾመበት ዲያብሎስ የተሻረበት ቀኑ አንድ ነው። ይሁዳ ገሀነም የወረደበት ማትያስ በይሁዳ ፋንታ የመንግሥተ ሰማያትን ቁልፍ ከተቀበሉ ሐዋርያት እያንዳንዱ የሆነበት ቀንም አንድ ነው። አየኽ ወንድሜ በዚህ ዓመት ስንቶቹ በገነት ካሉ ነፍሳት ጋር ተቀላቀሉ ስንቶቹ ደሞ ከገነት ተባረሩ ብለን ብንመረምር ያልጠበቅነውን ውጤት እናገኛለን ::
✨✨✨🌼
ሰው ማንኛውንም ሥጋዊም ሆነ መንፈሳዊ ዕቅድ ሲያቅድ ከተፈጠረለት ዓላማ አንጻር ማቀድ ይገባዋል ። እግዚአብሔር አንተን ሲፈጥርህ ዓላማው መንግሥቱን ወርስህ ቅድስናውን ተካፍለህ ለዘለዓለም ሕያው ሁነህ እንድትኖር ነው። ያንተም ዕቅድ ከዚህ የራቀ ሊሆን አይገባውም ። ስታቅድ አስቀድመህ እግዚአብሔር ላንተ ያለውን ዕቅድ ማወቅ ይገባሃል። ክርስቲያን ሁነህ እንደ አሕዛብ እንዳታቅድ ተጠንቀቅ። ቤተክርስቲያን ሰውን ለዘለዓለም ሕይወት ለማብቃት ያቀደችውን ዕቅድ ሳታውቅ ታቅድና አንተና ቤተ ክርስቲያን አብራችሁ ሳትሠሩ ዓመቱ ያልፍባችኋል። ተቋማትና ሠራተኞቻቸው በሥራ ሚገናኙት ዕቅዳቸው ከተገናኘ አይደል? አንተና ቤተክርስቲያንም በሥራ ምትገናኙት ዕቅድህ ከቤተከርስቲያን ጋር አንድ ከሆነ ነው።
ሕይወት እንዲህ ናት እና ሌሎችም
📝ሊቀ ሊቃውንት ስምዓኮን
✨✨✨🌼✨🍀✨✨✨🌼✨🍀✨✨✨🌼✨🍀
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
+6
የ2017 ዓ.ም የአዲስ ዓመት የነድያን መግቦት
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27
Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475
ለደብራችን አስተዳደር፣ አባቶች ካህናት እና ዲያቆናት ፣ለሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት እና ለአካባቢው ምዕመናን እንዲሁም ለመላው ኢትዮጵያውያን በሙሉ
በጊዜ ሥጦታ ቀናት ተፈጥራዊ ዑደትን ተከትለውና ወራትን ተክተው ዘመንን ይፈጥራሉ፤ የዘመናት ለውጥም አዲስ ዓመትን ይተካሉ፤ ይህ ሁሉ ግን በእግዚአብሔር አምላክ ቅዱስ ፈቃድ ሆነ፤ እኛም ለአዲሱ ዓመት ዘመነ ማቴዎስ እንደ ቸርነቱ ደረስን፡፡ በዝናብ አብቅሎ፣ በፀሐይ አብስሎ፣ በነፋስ አሳድጎ ፍጥረቱን የሚመግብ እግዚአብሔር ዕድሜ ለንስሓ ዘመን ለፍስሐ የሰጠን መልካም እንድንሠራበት ነውና በመጪው ዘመን የትላንት ስሕተታችንን አርመን፣ የተጣላን ታርቀን፣ የበደልን ክሰን፣ ያለው ለሌለው እያካፈለ ለመኖር ልናቅድ ይገባናል፤ ለምድራዊ ኑሯችን የምንተገብራቸውን እንደምናቅድ ለመንፈሳዊ ሕይወታችንም ልናስብ ይገባል፤ የዘመናት ጌታ ብርሃንና ጨለማን፣ በጋና ክረምትን የሚያፈራርቅ ዘመንን፣ በዘመን የሚተካ የሠራዊት ጌታ የእስራኤል ቅዱስ ልዑል እግዚአብሔር ዘመነ ዮሐንስ (፳፻፲፮ ዓ.ምን አሳልፎ) ለዘመነ ማቴዎስ (፳፻፲፯ ዓ.ም) አድርሶናልና ክብርና ምስጋና ለእርሱ ይሁን!
ዝናመ ምሕረቱን፣ ጠለ በረከቱን ለምድር ለግሶ፣ አለስልሶ ባዶነቷን በሰብል፣ በልምላሜ፣ በጽጌአት ውበት አስጊጦ፣ እክለ በረከቱን ለእኛ የሚያድል ፈጣሪ ዘመኑን የፍቅር፣ የሰላም፣ የምሕረት ዘመን ያድርግልን! የተሰጠንን ዘመን መልካም ልንሠራበት ይገባል! በስንፍና ያሳለፍነው ጊዜ ይብቃን! በአዲስ ዘመን በአዲስ ዕቅድ፣ በአዲስ መንፈስ ለሥራ እንነሣ! ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በመልእክቱ እንዲህ ይለናልና ‹‹የአሕዛብን ፈቃድ ያደረጋችሁበት በመዳራትና በሥጋ ምኞትም፣ በስካርም፣ በዘፈንም፣ ያለ ልክም በመጠጣት፣ ነውርም ባለበት በጣዖት ማምለክ የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃልና፡፡››
ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ትምህርት ቤታችን በድጋሜ እንኳን አደረሳችሁ እያለ፤ አዲሱ ዓመት መልካም ሥራ የምንሰራበት፣ በኀጥያት፣ በተንኮል፣ በክፋት የቆሸሸው ሰውነታች በንስሓ ታጥቦ ለቅዱስ ሥጋው ወደሙ የምንበቃበት፣ በመልካም ተግባር የሚታደስበት እና ለስጋ ብቻ ሳይሆን ለነፍሳችንም የምንሰራበት እንዲሆን እንዲሁም አዲሱ ዓመት በሃይማኖት የምንፀናበት፣ በፍቅርና በመረዳዳት የምንኖርበት፣አንደነታችን የሚጠነክርበት፣ ሀገራችን ኢትዮጵያ ሰላም የምትሆንበት እንዲሆንልን መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን፡፡
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
መልካም በዓል!
የሰንበት ትምህርት ቤቱ ግንኙነት ክፍል
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት!
እኛ ኢትዮጵያውያን ለብዙ ዘመናት የታደሱ ያይደሉ በርካታ ዓመታት ተጭነውን አልፈዋል፤ ቀድሞ እንበልጣቸው ከነበሩ አህጉር በታች ሆነንም በርካታ ዓመታትን አስቈጥረናል፤ የእርስ በርስ ግጭት፣ ረኃብ፣ ጦርነት፣ ድህነት፣ ኋላ ቀርነት የመልካም አስተዳደር እጦት በዓለም ፊት ልዩ መለያችን ሆኖአል፤ ዛሬም ከዚህ አልተላቀቅንም ብቻ ሳይሆን እንዲያውም አጠናክረን ለማስቀጠል ውል የገባን እስክንመስል ድረስ እየቀጠልንበት እንገኛለን፤ በእውነቱ እንዲህ የመሰለ ልምድ ልናፍርበትና ንስሐ ልንገባበት እንጂ ልናስቀጥለው አይገባም፤
በተፈጥሮ የታደለች ሁሉንም አሟልታ የምትገኝ ኢትዮጵያን የመሰለች ሀገር ይዘን ከሰው በታች ሆነን ስንገኝ በስንፍናችሁ ከምንባል በቀር የሀብተ ጸጋ እጥረት አለባችሁ የሚለን አናገኝም፤
ስለዚህ አሁንም ለኢትዮጵያውያን ልጆቻችን በአጽንዖት የምናስተላልፈው መልእክት ኢትዮጵያ ለኢትዮጵያውን አይደለም ለዓለም የሚተርፍ ሀብተ ጸጋ አላትና ለኔ ለኔ በመባባል የሕዝባችንን ሰቆቃው አናስረዝም፤
ኢትዮጵያ የሁሉም ኢትዮጵያውያን ናት የሚለውን ጥሬ ሓቅ በደምብ አላምጠን መዋጥ አለብን፣ ከዚያም በእኩልነትና በአንድነት ሀገራችንን እናድስ፤ ከሌሎች በደባል የሚመጡ ነገሮችን ሳይሆን የሀገሪቱ በሆኑ ዕሤቶች እንመራ፤ ለበርካታ ዓመታት የተሸከምነው ደባል የአስተዳደር ስልት ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር የሚጣጣም ሆኖ አልተገኘም፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከምንም ከማንም በላይ በፈጣሪው እንደሚመካ እሱንም አጥብቆ እንደሚያምን ልኂቃኖቻችን ተገንዘቡልን፤
እኛ ኢትዮጵያውያን ከሦስት ሺሕ ዓመታት በላይ ባስቆጠረ ታሪካችን ከእግዚአብሔር ተለይተን አናውቅም፤ በዚህም ተጠቃሚዎች እንጂ ተጐጂዎች የሆንበት ጊዜ የለም፤ በለመደው እምነት ባህልና ዕሤት ሕዝቡን ብንመራው ሁሉም ነገር ቀላል ይሆንልናል፤ ከዚህ ውጭ እንምራህ ብንለው ግን ያጋጠመንን ችግር ማስቀጠል ነው የሚሆነው፤ ስለዚህ የሁሉም መነሻ ማለትም የክፋትም ሆነ የደግነት መነሻ ውሳጣዊ አእምሮአችን ነውና እሱን በማደስ በአዲሱ ዓመት አገራችንን እንድናድስ በዚህ አጋጣሚ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
በመጨረሻም
አዲሱ ዘመን በሃይማኖት መንፈስ ግጭትን በውይይት፤ መለያየትን በአንድነት፤ አለመግባባትን በዕርቅ ፈትተን በመታደስ ማማ ላይ የቆመ ማኅበረ ሰብን ለመገንባት ሁላችንም ጥረት እንድናደርግ በእግዚአብሔር ስም መልእክታችንን እናስተላልፋለን፡፡
አዲሱ ዓመት የሰላም የዕርቅ የእኩልነትና የአንድነት ያድርግልን፡፡
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
አሜን::
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
መስከረም 1 ቀን 2017 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
✨🌼✨🌼✨🌼✨🌼✨🌼✨🌼✨🌼
✨🌼✨🌼✨🌼✨🌼✨🌼✨🌼
ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ዘተናገረ በበዓለ ርእሰ ዐውደ ዓመት ዘዕሥራ ምእት ዐሠርቱ ወሰብዓቱ ዓመተ ምሕረት
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፤ ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፤ የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፤ በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፤ እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤት የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ፡፡
ሁለመናችንን በሐዲስ ምግብና እየመገበ የሚጠብቀን አምላካችን እግዚአብሔር እንኳን ከዘመነ ዮሐንስ 2016 ዓ.ም. ወደ ዘመነ ማቴዎስ 2017 ዓ.ም. በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!!
‹‹ሐድሱ መንፈሰ ልብክሙ፤ የልባችሁን መንፈሳዊ አእምሮ አድሱ›› (ኤፌ. ፬÷፳፫)፤በገሃዱ ዓለም በግልጽ እንደምናስተውለው ከሞላ ጎደል የማያረጅ የለም የማይታደስም የለም፤ መታደስ ባይኖር ኖሮ ሕይወታውያን ፍጡራን በሕይወት መቀጠል አይችሉም ነበር፤ የዘመን መታደስም የሥነ ፍጥረት አንዱ አካል ነው፤ እኛ ሰዎችም የሕዳሴው መሪዎች ሆነን የተሾምንባትን ምድር በየጊዜው በልማት እንድናድሳት እግዚብሔር አዞናል፤ የሃይማኖት ትልቁ ተስፋም መታደስ ላይ የተመሠረተ ነው፤ ዘመንም እንደ ሌላው ያረጃል፤ ይታደሳልም፤ “ወናሁ እገብር ኵሎ ሐዲሰ እነሆ ሁሉን አዲስ አደርጋለሁ” የሚለው የእግዚአብሔር ቃልም የዚህ አስረጅ ነው፤ በዚህ ሕገ እግዚአብሔር መሠረት እነሆ አሮጌውን ዘመን የምንሸኝበት አዲሱን ዘመን ደግሞ የምንቀበልበት ምዕራፍ ላይ ነን፤ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት፡- ፍጥረታትን በማደስ ሕይወትን የማስቀጠል ሥልጣን በዋናነት የእግዚአብሔር ብቻ መሆኑ ለጥያቄ የሚቀርብ አይደለም፤ ይሁን እንጂ ሰውም ሥነ ፍጥረትን በማደስና በማጐስቈል ረገድ ያለው ሚና ቀላል አይደለም፤ ይህም ሰው በምድር ላይ እንዲሠለጥን ወይም ፍጥረትን እንዲገዛና እንዲመራ በፈጣሪ ከተሰጠው ሥልጣን የሚመነጭ ነው፤ ዛሬም ዓለማችን በመታደስ ያይደለ በማርጀት ላይ የምትገኘው ከሰዎች ድርጊት የተነሣ እንደሆነ እንገነዘባለን፤ የአየሩ መለወጥ፣ የበረዶው መቅለጥ፣ የሙቀቱ ማሻቀብ፣ የዝናሙ ማጥለቅለቅ፣ የባሕሩ መናወጥ ወዘተ. እየተፈጠረ ያለው ኃላፊነት ከጐደለው የሰው አጠቃቀም የተነሣ እንደሆነም ተደጋግሞ እየተነገረን ነው፤ እኛም በዓይናችን እያየን ነው፤ ከዚህ በተለየ ደግሞ በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ሰው ምድረ በዳውን ወደ ሐመልማለ ገነት ሲቀይር የሚስተዋልበት ሌላ ገጽታ አለ፤ ይህ የሚያሳየው ሰው በሥነ ፍጥረት ላይ የማደስና የማጐስቈል ብሎም የማጥፋት ሚና ያለው መሆኑን ነው፤ ሰውም እንደሌላው ሥነ ፍጥረት የሚያረጅም የሚታደስም ነው፤ ይህም በብዙ አቅጣጫ ሊከሠት ይችላል፤ ሰዎች በተናጠልም ሆነ በጋራ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ሁለቱንም ማለትም ማርጀትና መታደስን ሊያስተናግዱ ይችላሉ፤ ሰዎች በመንፈሳዊ፣ በኢኮኖሚያዊ በማኅበራዊና በመልካም አስተዳደር ወዘተ. የላቀ ዕድገትን ሲያስመዘግቡ በመታደስ ላይ እንደሆኑ ይታወቃል፤ የዚህ ተቃራኒ የሆነውን ይዘው እየተጓዙ ከሆነ ደግሞ ተቃራኒውን ወይም ማርጀትን እያስተናገዱ እንደሆነ ይታወቃል፤ ነገር ግን የእግዚአብሔር ፈቃድ ሰዎች በመንፈሳቸውም ሆነ በአእምሮአቸው፣ በነፍሳቸውም ሆነ በአካላቸው በመታደስ እንዲኖሩ እንጂ እርጅና እንዲጫጫናቸው አይፈልግምና “የልባችሁን መንፈስ አድሱ” በማለት ያስተምረናል፤ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት! የክርስትና ሃይማኖት የመጨረሻው ግብ የፍጥረት መታደስ ነው፤ ይህም ማለት የሃይማኖቱ አስተምህሮ መዳረሻ ከሞት በኋላ ትንሣኤ ከዚያም ፍጻሜና እንከን የሌለው ጣዕመ ሕይወት አለ ብሎ ሰውን ለዘላለማዊ ሕዳሴ ማብቃት ነው ማለት ነው፤ ከዚህ አንጻር የሰው የመጨረሻ ዕድሉ ማርጀት ሳይሆን መታደስ እንደሆነ እንገነዘባለን፤ እግዚአብሔር የሰውንና የፍጥረታትን መታደስ የሚሻው በሰማያዊው ዓለም ብቻ ሳይሆን በምድራዊው ዓለምም ጭምር ነው፤ ለዚህም ነው በየወቅቱ የሥነ ፍጥረትን ውበት እያደሰ የሚመግበን፤ አሁን ትልቁ ጥያቄ የሚሆነው እኛስ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ለመታደስ ተዘጋጅተናል ወይ? የሚለው ነው፤ ዛሬ እያንዳንዳችን ይህንን ጥያቄ አንሥተን ኅሊናችንን በጥልቀት መጠየቅ አለብን፤ በዚህም ሳናበቃ መልሱን በትክክል ማግኘት አለብን፤ በሁለንተናችን ለመታደስም ቈራጥ ውሳኔ በራሳችን ላይ ማሳለፍ አለብን፤ አዲሱ ዘመን አዲስና ብሩህ የሆነ የደስታ ሕይወት ሊያጐናጽፈን የሚችለው በዚህ መንፈስ ተቀብለን ስንጠቀምበት ነው፤
#በዓለ_ርዕሰ_ዐውደ_ዓመት_ዮሐንስ_ወቅዱስ_ራጉኤል
#እንኳን_አደረሳቹ
#ዐዲስ_ዓመት
ዘመን አልፎ ዘመን ሲተካ የመሸጋገሪያው ዕለት በየዓመቱ ቅዱስ ዮሐንስ እየተባለ ይጠራል፡፡ የዘመን መለወጫ፣ እንቁጣጣሽ፣ ሌላም መጠሪያ ስሞቹ ናቸው፡፡ በግእዝ ርእሰ ዐውደ ዓመትም ይባላል፡፡ ይህ በዓል የዓመት መጀመሪያ እንደመሆኑ መጠን በየዓመቱ ወሮች በመጀመሪያ ቀን ይከበራል፡፡ ያን ጊዜ ሌሊቱ ከቀኑ ጋር እኩል 12 ሰዓት ይሆናል፡፡ ዓመቱን ጠንቅቀው ሲቆጥሩ 364 ቀናት ይሆናል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ “ለዘመን መታወቂያው ይሆን ዘንድ ፀሐይና ጨረቃ ከዋክብትንም ፈጠረ” ይላልና /ሔኖክ. 21፥49/፡፡ በሌላ በኩልም በዘመነ ኖኅ በፍል ውኃ አጥለቅልቆ በኃጢአት ሕይወት ይኖሩ የነበሩት የኖኅ ዘመን ሰዎች ቀጥቶ ካጠፋ በኋላ ከንፍር ውኃ ምድር የተገለጠችበት ወር ነው /ኩፋሌ. 7፥1/፡፡ “በመጀመሪያው ወር ምድር ታየች የንፍር ውኃም ከምድር ደረቀ” የሚለውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቃል መሠረት አድርገው የአቡሻኸር ሊቃውንት የዘመን መለወጫን ታሪካዊ አመጣጥ ያስቀምጣሉ፡፡
✞
የቤተ ክርስቲያኒቱን ቀኖናዊ ሥርዐት ያጠኑ ሊቃውንት ደግሞ አዲስ ዓመት መስከረም አንድ ቀን መሆኑን አስመልክተው በክታባቸው እንዳስቀመጡት በአራቱ ወንጌላውያን ዘመኑን ይከፍሉታል፡፡ ምክንያቱም በዘመነ ዮሐንስ ተፀንሶ በዘመነ ማቴዎስ ተወልዶአል፡፡ በዘመነ ማርቆስ ተጠምቋል፡፡ በዘመነ ሉቃስ ተሰቅሎ ዓለምን ከፍዳና ከመርገም ነጻ አውጥቷል፤ እያሉ ታሪካዊ ሐረጋቸውን ጠብቆ አራቱ ወንጌላውያን ተከትለው ያለ እንቅፋት እንደሚጓዙ ያስረዳሉ::
#እንቁጣጣሽ
ኢትዮጵያዊቷ ንግሥት ሳባ የጠቢቡ ሰሎሞንን ዝና ሰምታ ኢየሩሳሌም ተጉዛ ስትመለስ “እንቁ ለጣትሽ /ለጣትሽ እንቁ/ በማለት ከእንቁ የተሠራ የጣት ቀለበት ንጉሥ ሰሎሞን እጅ መንሻ እንዲሆናት አበርክቶላት ነበርና ይህን ታሪክ መነሻ አድርገው “እንቁጣጣሽ” የሚለው ስያሜ ከዚያ እንደመጣ የታሪክ ድርሳናት ያስረዱናል ፡፡ በኢትዮጵያ የዘመን መለወጫ ዕለት ምድሪቱ በክረምቱ ዝናብ ረስርሳ ድርቀቷ ተወግዶ በአርንጓዴ እጸዋት ተውባ ሜዳው፣ ሸለቆውና ተራራው በአደይ አበባ ተንቆጥቁጠው የሚታዩበት ወቅት በመሆኑ ዕለቱ “እንቁጣጣሽ” የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡
በዚህ ወቅት ሕፃናትና ልጃገረዶች ነጭ ባሕላዊ ልብስ በመልበስ ለምለም ቄጤማና አደይ አበባ በመያዝ በአካባቢያቸው በመዞር አዲስ ዘመን መበሠሩን “እንኳን አደረሳችሁ” በማለት በቸርነቱ ዓመታትን የሚያፈራርቀውን እግዚአብሔርን በዝማሬ ያመሰግናሉ፡፡
መልካም_አዲስ_ዓመት
#ራጉኤል ሊቀ መላእክት:-
ራጉኤል ማለት የብርሃናት አለቃ ማለት ነው። የብርሃናት አለቃ ሲባል ፀሐይን፣ ጨረቃን እና ከዋክብትን በማመላለስና ለሰው ልጆች፣ ለአዝርዕት፣ ለእንስሳት፣ ለአራዊት ሁሉ ብርሃንን የሚመግብ ነው ማለት ነው። አንድም ራጉኤል ማለት የሚበቀል ማለት ነው። የሚበቀል ነው ማለት በቀል የሚገባው ለጠላት ነው የሰው ልጅ ጠላት ደግሞ ዲያብሎስ ነው፤ ስለሆነም ቅዱስ ራጉኤል እግዚአብሔርን አምነው ሕገ እግዚአብሔርን ጠብቀው በፍርሐተ እግዚአብሔር አምልኮቱን ለሚፈጽሙ ሁሉ ጠላት ዲያብሎስን የሚያርቅላቸው ወደ እነርሱም ፈጥኖ በመድረስ የሚታደጋቸው ነው ማለት ነው። ሔኖክ 6:4፡፡ አንድም ራጉኤል ማለት የኃያላን ኃያል እግዚአብሔር ማለት ነው። የኃያላን ኃያል ያለው የእግዚአብሔርን ኃያልነት ከምድር ፍጥረታት ዘንድ ኃያል ከሚባሉት ሁሉ ሊገለጽ የማይችል ኃያልነቱን ለመግለጽ ኃያልነቱም ከ እስከ የሌለው መሆኑን ለመግለጽ የተቀመጠ ነው። ስለዚህ እግዚአብሔር ኃያል የኃያላን ኃያል መሆኑን የሚገልጽ ትርጉም አለው።
አንድም ራጉኤል ማለት ጽኑ እግዚአብሔር ማለት ነው። የእግዚአብሔር አምላክን ጽኑነት ለማጉላት ሲል ጽኑ አለው። እግዚአብሔር የማይወላውል የማይዋዥቅ የማይከዳ ነው ለማለትም ሲል ይህ ስያሜ ተሰጠው። የእግዚአብሔርን ጽናት የሚያሳይ ትርጉም ያለው ስያሜ ነው። የሊቀ መላእክት የቅዱስ ራጉኤል አገልግሎት እና ስልጣን፡- እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከዚህ ዓለም በ64 ዓመቷ ካረፈች በኋላ ሥጋዋ ወደ ዕፀ ሕይወት ሲነጠቅ (ሲያርፍ) አብሮ ለሔደው እና ስጋዋን በእጣን ሲያጥን ለነበረው ለፍቁረ እግዚ ለቅዱስ ዮሐንስ ኅብስትን የመገበ መልአክ ነው። በብርሃናት ሁሉ ላይ የሰለጠነ መልአክ ነው። ከአዳም ሰባተኛ ትውልድ የሆነ በእግዚአብሔር ፊት ግሩም ያማረ ሥራው የሰመረ እስከዛሬ የሞት ወጥመድ ያልያዘው የሞት ጥላ ያላረፈበት ነብዩ ሔኖክ "ከቅዱሳን መላእክት አንዱ የሆነ ጸላዒ ዲያብሎስን የሚበቀለው ራጉኤል በብርሃናት ላይ የሰለጠነ ነው" ሲል ስለ እርሱ ተናግሯል፡፡
እግዚአብሔር ዓለምን ይቆጣጠር ዘንድ የሾመው ታላቅና ቅዱስ መልአክ ነው። (ድርሳነ ራጉኤል ዘ ጥቅምት ገጽ 23) አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር ለመተካት ዓለምን የመለወጥ ሥልጣን የተሰጠው ቅዱስ መልአክ ነው። ከእግዚአብሔር የጌትነቱ አዳራሽ ይገባና ይወጣ ዘንድ ስልጣን ያለው ከኪሩቤልና ከሱራፌል ጋር ከፈጣሪ የጌትነት ዙፋን ፊት የሚቆም ነው። ሎጥን ሚስቱንና ልጆቹን ከእሳተ ጎመራ ያዳነ የበለአምን እርግማን ወደ በረከት የለወጠ እርሱ ነው። በቅዱስ ራጉኤል ስነ ሥዕል ላይ የምናየው ይህ ባለ አራት እራስ ንስር ከአርባእቱ ኪሩቤል አንዱ ገጸ ንስር ነው። የሥላሴን የጌትነት ዙፋን የሚሸከሙ አርባዕቱ እንስሳት ናቸው። የሚሸከሙት ሲባል ጫማ የሰውን ልጅ እንደሚሸከመው እንጂ ችለውትስ አይደለም። እነርሱም የሰው ገጽ፣ የእንስሳ ገጽ፣ የንስር ገጽ እና የአንበሳ ገጽ ያላቸው ናቸው። ይህንንም ነብዩ ሕዝቅኤል "ለእያንዳንዱ እንስሳትም የተለያዩ አራት ገጾች ነበሩት። ይህውም በስተቀኝ በኩል የእንስሳ መልክ፣ በስተ ግራ የላም ገጽ፣ በበስተ ኋላም የንስር ገጽ የሚመስሉ ነበሩ" ብሏል ሕዝ 1፡6-13፡፡ ከዚህ የምንገነዘበው ነገር ቢኖር አራት ገጽ ካላቸው ኪሩቤል መካከል አንዱ ንስር መሆኑን ነው። ቅዱስ ራጉኤል ደግሞ የእነዚህ ኪሩቤል አለቃቸው (የጌትነቱ ዙፋን ጠባቂ) በመሆኑ በዚህ ምክንያት ማለትም እነርሱ ዙፋኑን ተሸካሚ እርሱ ደግሞ አጠገባቸው መቆሙ መንበሩን ጠባቂ በመሆኑ በዚህ አይነት የአገልግሎት ድርሻ አብረው ሊሳሉ ችለዋል። ቅዱስ ያሬድም በድጓው "አርባእቱ እንስሳ አልቄንጥሩ እንደሚባለው ንስር ፊት ለፊት አይታዩም አንዱም በመራቸው ይሔዳሉ እነርሱም እያንዳንዳቸው አራት ገጽ ሲኖራቸው ሳያርፉና ሳይደክሙ የሚያመሰግኑ ናቸው" በማለት ጽፏል።
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
ሩፋኤል ሆይ ከላይ ከሰማይ ወርደህ የጻድቃንና የሰማዕታትን ጸሎት የምታሣርግላቸው አንተ ነህ ፡ ሩፉኤል ሆይ የድኩማን ኃይላቸው አንተ ነህና፡፡ ምስጋናዬን ጸሎቴን ወደላይ ታሣርግልኝ ዘንድ በእግዚአብሔር ወልድና በእናቱ በድንግል ማርያም ስም እማልድሃለሁ፡፡"
[ መልክአ ሩፋኤል ]
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27
Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475
+2
ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ የእንኳን ደህና መጡ አቀባበል በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ተከናወነ።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ሐምሌ 6/2016 ዓ/ም ወደ አሜሪካ ያቀኑ ሲሆን በዛሬው ዕለት ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል።
ቅዱስነታቸው ወደ ኢትዮጵያ መመለሳቸውን ተከትሎ ክብረ አበውን አሠረ ሐዋርያትን መሠረት በማድረግ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ጀምሮ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የእንኳን ደህና መጡ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
በመንበረ ፓትርያርክ ቅዱስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በተደረገው ባለው የቅዱስነታቸው አቀባበል መርሐ ግብር ላይ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የባሕርዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ በርካታ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉኃን ቀሲስ ታጋይ፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያውና የየድርጅቱ ሥራ ሐላፊዎች፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ ፣ የሀገረ ስብከቱ የሥራ ሐላፊዎች የክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጆች የገዳማትና የአድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ ሰንበተ ተማሪዎች እና ምዕመናን ተገኝተዋል።
የብፁዕ ወቅዱስ አባታችን ቡራኬ አይለየን።
