ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Kanalga Telegram’da o‘tish
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Ko'proq ko'rsatish669
Obunachilar
+124 soatlar
+37 kun
-330 kun
Postlar arxiv
"ልጆቼ ሆይ በፊቱ ትቆሙና ታገለግሉት ዘንድ አገልጋዮቹም ትሆኑ ዘንድ ታጥኑለትም ዘንድ እግዚአብሔር መርጦአችኋልና ቸል አትበሉ" 2ኛ ዜና 29፥11
።።።።።።።።።።። ጾም መድኃኒት ናት።።።።።።።።።።።
አወሳሰድዋን በትክክል ላላወቁ ግን ጥቅም የላትም፡፡
ይህችን መድኃኒት የሚወስድ ሰው በየስንት ሰዓቱና በምን ያህል መጠን እንደምትወሰድ፣ ለምን ዓይነት በሽታ እንደምትጠቅም፣ በየትኛው አከባቢና የአየር ኹናቴ እንደምትወሰድ፣ ከእርሷ ጋር የሚኼዱና የማይኼዱ ምግቦችን እንዲሁም ከእርሷ ጋር የማይስማሙ ሌሎች ነገሮችን ለይቶ ማወቅ አለበት፡፡
እነዚህን ግምት ውስጥ አስገብቶ የማይወስዳት ሰው ግን ከጥቅሟ ይልቅ ጉዳቷ ታመዝንበታለች፡፡አንድ በሐኪም የታዘዘልንን የደዌ ዘሥጋ መድኃኒት እንዲያሽለን ስንፈልግ በጥንቃቄ ልንወስደው ያስፈልጋል፤ የነፍሳችንን ደዌና በአእምሮአችን ውስጥ ያሉ ቁስሎችን ለመፈወስ ብለን በምንወስደው መድኃኒት ደግሞ ከዚህ የበለጠ መጠንቀቅ ይገባናል፡፡ ።።።።። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ።።።።።።።
"ለእግዚአብሔር ተገዙ ስሙንም ጥሩ ሥራውን ለአሕዛብ ንገሯቸው ለስሙ ምስጋናን ስጡ ሰንበትን አክብሩ ጽድቅን ሥሩ ሌባ በማያገኘው ብል በማያጠፋው በሰማያት መዝገብን አከማቹ ክርስቶስ ባለበት ለመሆን በላይ ያለውን እያሰባችሁ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ።"
መዝሙር ዘቅድስት
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
ብዙዎች በእኔ ላይ ቆሙ፡፡ ብዙዎች ሰውነቴን አምላክሽ አያድንሽም አሏት፡፡ አንተ ግን አቤቱ መጠጊያዬ ነህ፡፡ ክብሬንና ራሴንም ከፍ ከፍ የምታደርገው አንተ ነህ (መዝ. 3፡1)ነቢዩ ዳዊት ክፉ ቀን ቢገጥመው የጸለየው ጸሎት ነው፡፡ መራራ ቀናት ሀገር ያስለቅቃሉ፡፡ ከዙፋን ያወርዳሉ፡፡ ማቅ ያስለብሳሉ፡፡ ለብቻ ያነጋግራሉ፡፡ መራራ ቀናት እንደ ጣፋጮቹ ቀናት ፈጥነው አያልፉም፡፡ ያስቸግራሉ፡፡ ዳዊት መራራ ለቅሶን እያለቀሰ ይህንን መዝሙር የዘመረው ሳኦል ሲያሳድደው ፣ ጎልያድ ሰይፉን መዝዞ ሲመጣበት በነበረ ጊዜ አይደለም፡፡ ዳዊት አቤቱ የሚያስጨንቁኝ ምንኛ በዙ ብሎ መራራ ቃላትን የተናገረው ወደ ዙፋን ከወጣ በኋላ ነው፡፡ ዳዊት አደገ ፤ በሳኦል ፈንታ ተሾመ ፣ ሚስት አገባ ፤ ልጆች ወለደ፡፡ ነገር ግን ከዚህ ሁሉ በኋላ አስጨናቂ ቀን በዳዊት ላይ መጣ፡፡ ልጁ አቤሴሎም በጠላትነት ተነሣበት፡፡ ኤሎፍላውያን ቢሆኑ ይዘምትባቸዋል፡፡ እነ ሳኦል ቢሆኑ ተከታትሎ ያጠፋቸዋል፡፡ የገዛ ልጁ ፣ የአብራኩ ክፋይ ሕዝቡን አሳምጾ አባቱን ሀገር አስጥሎ አሳደደው፡፡ የእኛም ሕዝብ ዛሬ ላይ እንደ ዳዊት ያለ መከራ ነው የገጠመው፡፡ የሚያሰቃዩት በዙ፡፡ ብዙዎች በራሱ ላይ ቆሙ፡፡ አምላክሽ አያድንሽም እያሉ የገነባውን መቅደስ አፈረሱ፡፡ የሚያሳድዱት ኤሎፍላውያን ቢሆኑ በዘመተ ፣ ፣ እነ ጎልያድም ቢሆኑ ወንጭፉን ይዞ በተጋደለ ፣ እነ ሳኦልም ቢሆኑ ቁርጡን አውቆ ጫካ ገብቶ በታገለ ነበር፡፡ ግን እነ አቤሴሎም ናቸው፡፡ ከአብራኩ የተከፈሉ ፤ ከማዕዱ እየበሉ ያደጉ ፣ አብረውት ሀገር ፣ ቤት የተጋሩ፡፡ እነዚህን ምን ማድረግ ይሻላል? ዳዊት ያልተዋጋው ‘አቤሴሎም ልጅ ነው እውቀት ቢጎድለው ነው’ ብሎ ነው እንጂ ስለማይችል አልነበረም፡፡ ዳዊት አርበኛ ነው፡፡ ነብር በጡጫ ፣ አንበሳ በእርግጫ መስበር የሚችል ፤ የጦር መላ ያለው ጀግና ነው፡፡ ሳይዋጋ ዝም ያለው መልስ ከእግዚአብሔር ነው ብሎ አስቦ ነው፡፡ የሸሸ ሁሉ የተሸነፈ አይደለም፡፡ ዝም ያለ ሁሉ ኃይል በውስጡ የሌለው አይደለም፡፡ በመጨረሻ አሸናፊው ዳዊት ነው፡፡ አቤሴሎሞች የሸሸላቸው ሁሉ የተሸነፈ ፣ የማይመለስ ፣ የማይችል ፣ ከዚህ በኋላ አከርካሪው የተሰበረ ስለሚመስላቸው ሚስቱን ፣ ርስቱን ፣ ቤቱን ሀብቱን ሁሉ ይወርሳሉ፡፡ ዳዊት የተመለሰ ቀን ግን ሬሳቸውም አይመለስም፡፡ አቤሴሎም ዳዊትን ባሳደደው ቀን ያደረገው ይህንኑ ነው፡፡ የዳዊትን የአባቱን አልጋ አረከሰ፡፡ ሚስቱን ዙፋኑን ወረሰ፡፡ ዳዊት ሲመለስ ግን አልተገኘም፡፡ ነፍሱ በምድረ በዳ እንደወደቀች ቀረች፡፡ መጨረሻው አያምርም፡፡ እነ አቤሴሎምን ሥልጣን ሲይዙ አለማያውቁበት ግፉን አታብዙ በሏቸው፡፡ ዳዊትም
‘ተነሥ አቤቱ አምላኬ አድነኝ ፤ የጠላቶቼን መንጋጋ መትተሃልና የክፉዎችንም ጥርስ ሰብረሃልና’ እያለ ይመለሳል፡፡ መዝ. 3፡7ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ 🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
ስለዚህ፥ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፦እውነት እውነት እላችኋለሁ፥የሰውን ልጅ ሥጋ ካልበላችኹ ደሙንም ካልጠጣችኹ በራሳችሁ ሕይወት የላችኹም። ዮሀ 6÷53የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት ህጻናት እና አዳግያን ክፍል(ማህበረ ቂርቆስ) የጋራ የቅዱስ ቁርባን ቀን ❤️🙏 ( የካቲት 15/2018 ዓ.ም) የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
ስለዚህ፥ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፦እውነት እውነት እላችኋለሁ፥የሰውን ልጅ ሥጋ ካልበላችኹ ደሙንም ካልጠጣችኹ በራሳችሁ ሕይወት የላችኹም። ዮሀ 6÷53የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት ህጻናት እና አዳግያን ክፍል(ማህበረ ቂርቆስ) የጋራ የቅዱስ ቁርባን ቀን ❤️🙏 ( የካቲት 15/2018 ዓ.ም) የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
🔔ዐቢይ ጾም 🔔
🔔ሁለተኛ ሳምንት🔔
🔔ቅድስት🔔
የካቲት 15
የዕለቱ ምንባባት
1ኛ ተሰ 4÷1-13
1ኛ ጴጥ 1÷13-ፍ
ሐዋ 10÷17-30
የዕለቱ ምስባክ
እግዚአብሔር ሰማያት ገብረ አሚን ወሠናይት ቅድሜሁ ቅድሳት ወዕበየ ስብሕት ውስተ መቅደሱ። መዝ 95÷5
ትርጉም
እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ፈጠረ
እምነትን እና በጎነት በፊቱ ናቸው
ቅድስና እና የክብር ገናንነት በመቅደሱ ውስጥ ናቸው።
የዕለቱ ወንጌል ማቴ 6÷17
ቅዳሴ ዘኤጲፋንዮስ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🤲🤲🤲🕯🕯🕯🕯🕯
ዕለተ ሰንበት በማስቀድስ እናሳልፍ
እምነት በሁሉም ቀናት
እምነት የሚገነባው በተአምራት ብቻ ሳይሆን በታዛዥነትም ጭምርነው። ዝም ማለት ቀላል ሆኖልን ሳለ ደግነትን በማሳየት፣ ለመጥላት ምክንያት ኖሮን ሳለ ይቅር በማለት፣ ባዶነት ተሰምቶን ሳለ ከልብ በመጸለይ እምነትን በውስጣችን መገንባት እንችላለን፡፡
ልብ እንበል… እያንዳንዱ ትንሽ የእምነት ተግባር ወደፊት ፍሬ አፍርቶ የምናየው ዘር ነው!'
ጌታችን በአንድ ወቅት እንዲህ ብሏል፡- “ስለ እምነታችሁ ማነስ ነው ! እውነት እላችኋለሁ, የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ ይህን ተራራ፦ ከዚህ ወደዚያ እለፍ ብትሉት ያልፋል፤ የሚሳናችሁም ነገር የለም::' (ማቴ. 17፥20)
እዚህ ጋር መርሳት የሌለብን ነገር ተራራውን የሚያንቀሳቅሰው የእምነታችን መጠን ሳይሆን በውስጣችን የእምነት መኖር ነው፡፡ ድቅድቅ ባለ ጨለማ ውስጥ ትንሽዬ የእሳት ነበልባል እንዳትበራ የሚያግዳት ምንም ዓይነት ነገር የለም፡፡
ስለዚህ ክርስቲያን ሆይ ሰውነታችንን ስንመግብ መንፈሳችንም እምነት መጉረሱን መርሳት የለብንም፤ የእግዚአብሔርን ቃል በውስጣችን አትሞ ለማኖር ሁሌም መጣር፤ ፍርሃት ሲሰማን የእግዚአብሔርን ተስፋዎች ለማስታወስ መሞከር፣ ዓይኖቻችን ለማየት የተቸገሩትን ልባችን እንዲመረምረው መፍቀድን መማር አለብን፡፡
ምክንያቱም እምነት የነፍስ አፍ ነው! የተዘጋ አፍ ደግሞ መብላት አይችልም!
📝አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
“ራስህን ዝቅ ስታደርግ በዙሪያህ ያሉትን ሁሉ ቅዱሳን እንደሆኑይሰማሃል፡፡ ትዕቢተኛ ግን ከሆንክ ሁሉም በዙሪያህ ያለ ሰው አድካሚ እና መጥፎእንደሆነ ይሰማሃል፡፡”
አባ ዮሴፍ ገዳማዊ
ካህናትን አክብር!
ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ "ካህናትን በሚገባ አክብር። ለመዓርጋቸውም ክብር ስጥ፤ ሥራቸውን አትመርምር። በመዓርጉ ካህን መልአክ ነውና። በሥራው ግን ሰው ነው። በእግዚአብሔር ቸርነት ቄሱ በሰው ልጆችና በእግዚአብሔር መካከል ያለ አማላጅ ነው። የሰዎችን ስሕተት አትፈልግ። የወዳጅህን ኃጢአት አትግለጥ። የጎረቤትህን መጥፎ ጎን በንግግርህ አውጥተህ አትድገመው። በፍጥረት ላይ ፈራጅ አልኾንክምና። በምድር ላይ ገዥ አይደለህምና። ጽድቅን ካፈቀርክ ራስህን ገሥጽ። ለራስህ ኃጢአቶች ፈራጅ ለመተላለፍህ ብቻ ተነሳሒ ኹን። የሰዎችን መጥፎ ምግባር በተንኮል አትመርምር። ... በወዳጅህ ላይ ከተቆጣህ በእግዚአብሔር ላይ መቆጣትህ ነው። በልብህ ቍጣን ከተሸከምክ በጌታ ላይ መነሣትህ ነው። ድፍረትህም ከፍ ይላል። በክፉ ቅናት ከገሠጽክም ግሣጼው ኹሉ የክፋት ነው። በጎነት በውስጥ ከኖረ ምንም ጠላት በምድር ላይ አይኖርህም። እውነተኛ የሰላም ልጅ ከኾንክ በማንም ሰው ላይ ቍጣን አትቆሰቁስም። መቆጣትን የምታፈቅር ከኾነ በክፉው ነገር ተቆጣ ከዚያን ያንተ ኾኖ ታገኘዋለህ። የምትፈልገው ጦርነትን ለማወጅ ከኾነ ሰይጣን አማካሪ ኾኗል። ለመቆጣት ብትመኝ በአጋንንት ላይ ተቆጣ። በአርአያ ሥላሴ የተፈጠረውን ሰው የምትሳደብ ከኾነ የነፍሰ ገዳይ ቅጣት ይገባሃል። ሰውን ሙልጭ አድርጎ መሳደብ የእግዚአብሔርን አርአያ መሳደብ ነው" እንዲል። (Nicene and post Nicene Fathers second series V 13)።
Namni armaan olitti ilaaltan kun, Mana Kiristaanaa keessatti kutaa Lallaba Arsii keessatti walitti bu’iinsa fi jibba facaasa kan jiru, nama safuu hin qabne dha. Waggoota muraasa darban irraa kaasee tajaajiltoota Mana Kiristaanaa kabajamoo ta’an suuraa isaanii miidiyaa hawaasaa irratti maxxansuun arrabsuu fi maqaa balleessuu irratti bobba’ee argama.
Afaan Oromoo kan hin beekne ta’ee osoo jiruu, akka nama Oromootaaf cinqamu fakkaachuun obboloota Afaan Oromoottin tajaajilan birati maxxanfame ajandaa jibbaa isaa Mana Kiristaanaa keessatti facaasa jira. Magaalaa keenya Asallaa keessatti hojii misoomaa Mana Kiristaanaa akka hin hojjetamneef bulchitoota mana kiristaanaa kenya irratti maqaa balleessuu hojjechuun misoomni akka gufatu taasisuuf wanti hin sochoone hin jiru.
Kabaja abbootii gadi buusuun maqaa jibbaa gara garaa itti moggaasa; akkasumas “iddoo hin turre ture” jechuun mirga lammummaa isaanii sarbuun suuraa isaanii maxxansuun arrabsaa kan jirruu samu isaas sirnaan hojjeta jira jechuunis kan shakkisiisudha.
Kanaafis jibba inni facaasa jiru arginee osoo hin argin fakkaannee, “magaalaan seera qabdi; qaamni nageenyaa ni jira; isaan ni dhaabu” jechuun obsa fi callisaan taa’uun keenya ture. Amma garuu hojii badaa isaa babal’achaa jira; magaalaa keessatti tajaajiltoota jiran maqaa balleessuun itti fufeera. Kanaaf qaamni dhimmi ilaallatu akka dhaabu gaafanna.
Yoo akkas hin taane, ijoolleen Mana Kiristaanaa warri yeroo hunda eeggumsa dhaabbatan osoo jiranii, abbootiin arrabsamanii, maqaan manneen barnoota Dilbataa balleessamaa akka itti fufu hin eeyyamnu. Akkasumas hojii badaa isaa, daa’imman walitti qabuun maal akka hojjetu, keessumaa daa’imman dubartootaa irratti maal akka raawwate fi akka hojjete ragaa ifa ta’een ni saaxilna.
+2
ይህ ከላይ የምትመለከቱት ግለሰብ በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተክርስቲያን ውሰጥ ጸብን፤ ጥላቻን የሚዘራ ሀይ ባይ ያጣ ግለሰብ ነው። ከቅርብ አመታት ወዲህ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንቁ አገልጋዮችዋን ፎቶ በየማህበራዊ ሚዲያው በመለጠፍ በመሳደብ እና ስም በማጥፋት ስራ ተጠምዶ ይገኛል።
የኦሮምኛ ቋንቋ ሳያውቅ ለኦሮሞ ተቆርቋሪ በመምሰል በኦሮምኛ ቋንቋ የሚያገለግሉ ወንድሞች ስር በመለጠፍ የራሱን የጥላቻ አጀንዳ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እየዘራም ይገኛል። በከተማችን በአሰላ ባሉ የቤተ ክርስቲያን የልማት ስራዎች እንዳይሰሩ በደብራት አስተዳዳሪዎች ላይ ስም የማጥፋት ስራን በመስራት ልማት እንዲስተጓጎል ለማድረግ የማይፈነቅለው ድንጋይም የለም።
የአባቶች ክብር በማዋረድ የተለያየ የጥላቻ ስም በመስጠት የሚጠራ እናም ባልዋሉበት ዋሉ እያለ የዜግነት መብታቸውን በሚጥስ መልኩ ፎቶ እየለጠፈ የሚሳደብ አይምሮ በስርዓት መስራቱ የሚያጠራጥር ግለሰብ ነው። እናም ይህ ሰውዬ እየዘራው ያለውን ጥላቻ አይተን እንዳላየ ከተማው ህግ አለ ፤ የጸጥታ አካላት አሉ በማለት ያስቆሙታል ብለን በትዕግስት በዝምታ ተቀምጠናል። የዚህ ሰውዬ የብልግና ስራው አሁን ላይ እየሰፋ እና በከተማው ያሉ አገልጋዮችን ስም የማጥፋት ስራው የቀጠለ በመሆኑ ይመለከተኛል የሚል አካል እንዲያስቆመው ስንል እንጠይቃለን። ካልሆነ ግን የቤተ ክርስቲያን ሁሌም ዘብ የሚቆሙ ዕንቁ የቤተክርስቲያን ልጆች እያሉ አባቶች እየተሰደቡ ፤ የሰንበት ት/ቤቶችን ስም እያጠፋ እንዲቀጥል አንፈቅድም። የሱን ብልግና ህጻናትን ሰብስቦ ምን እንደሚሰራ በተለይ በሴቶች ህጻናት ላይ ምን እንዳደረገ እና እንደሰራ በመረጃ የምናጋልጥ ይሆናል።
