cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

Dave ( ባለ በገና)🍎🍇🎸🪗

I looked, and rose up,Nehemiah 4:14 ☞በዚህ ቴሌግራም ቻናል የተለያዩ መሰናዶች ይቀርባሉ! ➩ #አዳዲስ_መዝሙሮች ➩ #ቆየት_ያሉ_ዝማሬዎች #መንፈሳዊ ስነ ፅሁፎች ➩ #Live_WORSHIP_እና_studio_live_worship ➩ #ቅዱሱ የእግዚአብሔር ቃል እና የተለያዩ ትምሕርት ነክ ዝግጅቶች ይቀርባሉ። ለሃሣብ እና አስተያየት ደግሞ @Dave_one_Bot አለላችሁ።

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
1 105
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-177 kunlar
+55130 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

ብላቴናዉ ዘማሪ አላዛር ስንታየሁ original song hanna tekle 5 minutes 57 seconds, 5.6 MB, sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ @Heavenly_Grace_1 @Heavenly_Grace_1         👇JOIN OUR GROUP👇 @Dave_group_chat                 △Join us △ Title: ብላቴናዉ ዘማሪ አላዛር ስንታየሁ original song hanna tekle
Hammasini ko'rsatish...
👍 1
ሰላሜ ሆነሃል ዘማሪት ህሊና ዳዊት 🕐-7:46Min || 💾-7.6MB sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ @Heavenly_Grace_1 @Heavenly_Grace_1         👇JOIN OUR GROUP👇 @Dave_group_chat                 △Join us △ Title: ሰላሜ ሆነሃል || ህሊና ዳዊት
Hammasini ko'rsatish...
2
የአስደናቂዋ ሴት ማስታወሻ እዉነተኛ ታሪክ! በDave ባለ በገና የተሰናዳ. ክፍል 26. ሁሉም በተቀመጡበት ሳሉ አንድ አባት ተነስተው ‹‹እስኪ ሁላችን ስለአንድርያና ለትንሽ ጊዜ እንፀልይ›› አሉ፡፡ ሁሉም ድምፅ አውጥተው መፀለይ ጀመሩ፡፡ አንድርያናም በሰማችው ነገር እየተደነቀች በእንባ ባህር ትዋኛለች፡፡ ‹‹ጌታ ሆይ አንድርያናን በነፍሳችን ቀይራት፣ እኛ ሞተን እስዋ ትዳንልን፣ ነፍስዋን በነፍሳችን ተካ›› በማለት ይፀልያሉ፡፡ መላው እስረኛው የአንድርያናን ክፋትና ኃይለኝነት እያሰበ ያለቅሳል። ፡ አንድርያና አንጀቷ ተንሰፈሰፈእንባዋ እንደ ጎርፍ ይፈሳል። ብድግ አለች ነገር ግን ማልቀስዋ በዝቶ መናገር አቃታት፡፡ እርስዋም እዚህ ሳይቤሪያ ከገባች አስራአምስት ዓመት ሆኗታል፡፡ አንድርያናም ‹‹ለጌታ በሆነ እንደ እናንተ ስሰቃይ እኔም በአንድ ቦታ የወጣቶች መረጃ ቢሮ አባል ነበርኩ፡፡›› በማለት ንግግርዋን ጀመረች በእምነት መከራ የከፈለችውን ትነግራቸው ጀመር የቀኝ ጡቷ መቆረጥ የደረቷ ስድስት አጥንት ተሰብሮ እንደ እንጨት ተገትሮ ከጡቷ ስር የሚወጣውን እያሳየች፤ በጀርባዋ ያለ የተቦደሰ ስጋ በታፋዋና በጉልበቷ አከባቢ ያለው የቁስል እባጭ ለማሳየት እየሞከረች ሳለች በዚያች ቅፅበት ያለችበትን አካባቢ እስከምትረሳ ፈፅሞ ተለዋወጠባት፡፡ በሳይቤሪያ ስላሳለፉት ታላቅ መከራ እየተነጋገሩ ሳለ አዲስነገር ተከሰተ በደቂቃዎች መሃል ማንነቷ ተለውጦ ያገኘችው አንድርያና የስጋ አይኗ ተለውጦ በመንፈስ ውስጥ ገባች፡፡ ሰማያዊ ቀለም የለበሰው ሰማይ (ሕዋ) መግለፅ በማይቻል ልዩ ቀለም ተውቦና ከዳር እስከ ዳር ከሰሜን እስከ ደቡብ ከምዕራብ እስከ ምስራቅ ተዘርግቶ ወለል ብሎ አየች፡፡ በዚህ ልዩና ህብረ ቀለሙ መግለፅ በማይቻል ጠፈር (ጋላክሲ) በማለዳ ፀሃይ በሰፊ ባህር ላይ ብርሃን ሲያርፍበት የሚያብረቀርቅ ብልጭ ድርግም የሚል ነገር እንደሚታየው ብልጭታ የሚመስል ነገርን ታያለች ያ ሲያብረቀርቅ ያየችው አረፋ መሰል ብርሃን ቀስ በቀስ እየሰፋ እየቀረበና እየተጠጋ መምጣት ጀመረ፡፡ በተገለጠው ራዕይ ውስጥ ቁጥር ስፍር የሌላቸው አዕላፋት መላዕክት ፀጉራቸው የተጠቀለለ ከአንገታቸው እምብዛም ያልወረደ ስስና የሚያብረቀርቅ ልብስ የለበሱ ዙሪያቸው የልዩ ብርሃን የተከበቡ ዓይኖቻቸው ነጫጭና ሽፋሽፍቶቻቸው ችፍግ ብሎ የበቀሉ ውብ መላዕክት ሲያሸበሽቡ ሲዘምሩ ተመለከተች፡፡ ክንፎቻቸው አንዱ የሌላውን ሳይነካ በስርዓት ተሰልፈው ይሰግዳሉ ሳያቋርጡ ያዜማሉ፡፡ አንድርያና በምታየው ራዕይ ውስጥ ሆና መናገር አቅቷት ዝም ብትልም ዓይኖቿ እንባን ማፍሰሳቸውን አላቆሙም ነበር፡፡ አጠገቧ የነበሩ በሳይቤሪያ እስር ቤት መከራ የደረሰባቸው ቅዱሳን በሰማችው ታሪክ አዝና የምታለቅስ መስሏቸው አንዳንዱ በእንባ ያግዛታል ገሚሱ ዝም ብሎ ይመለከታታል ወደ ሳይቤሪያ እንዴት ልትመጣ እንደቻለች ታሪኳን ለመስማት እየጓጉ፡፡ በዚህ ሁሉ መሃል በነዚያ እልፍ ጊዜ እልፍ ሺህ ጊዜ ሺህ በሆኑ መላዕክት መሃል ዘለግ ያለ ውበቱ ልዩ የሆነ ከዓይኑ የእሳት ነፀብራቅ የሚያቃጥል ንዳድ ይፈልቃል፣ በወገቡ ዙሪያ የወርቅ መታጠቂያን አጥልቋል፣ ከእግሩ ስር የሚፈልቀው የወርቅ እንቁ ፈሳሽ ወንዝ ይመስላል፤ ሲፈስ ትመለከተዋለች ወርዶ ወርዶ የት እንደሄደ ባታይም እሳት ሆኖ በእሳት መካከል ሲቀመጥ ታየዋለች፡፡ በዚህ መሃል ከዓይኑ በዙሪያው ከከበበው የብርሃን ነፀብራቅ ጨረር ወደ እያንዳንዳቸው እንደዘንግ እየተወረወረ ሲመጣ ትመለከታለች፡፡ ይህ የተገለጠው የጌቶቹ ጌታ የነገስታት ንጉስ የዓለማት ገዢና ፈጣሪ ተቆጣጣሪ ጌታ ኢየሱስ ያለመከልከል በእነዚያ ከአእላፋት መላዕክት መሃል ሲመላለስ ዙሪያውን በከበበው ሰማያዊ ዝማሬ እየታጀበ ከወዲህ ወዲያ ሲራመድ ታያለች፡፡ ውብ አይኖቹ በሳይቤሪያ ያሉትን ቅዱሳን እንደሚመለከቱ ያስተዋለችው አንድርያና በዚህ መሃል ነበር ልዑል ዓምላክ ጌታዋ ከእይታዋ የተሰወረባት፡፡ ብዙ ፈለገችው በዓይኗ ልታገኘው አልቻለችም፡፡ ‹ኦ ጌታዬ ምንኛ መልካም ነው! ውብ ነው! በእይታዬ መሃል ከነፍሴ ሰላምና ደስታ እረፍትና እፎይታ የተነሳ ያለኹበትን የመከራ ስፍራ አስረሳኝ፡፡ ስለ አንተ የተጎዳሁልህ መከራና ስቃይ የተቀበልኩልህ ጌታዬ ሆይ ወዴት ነህ?›› ብላ ድምፅዋን ጮክ አድርጋ ተጣራች፡፡ ያን ጊዜ ነበር አብረዋት የነበሩት ራዕይ እያየች እንደሆነ የተረዱት፡፡ እናም ‹‹ተዉዋት ዝም በልዋት ታሪኳን በኋላ ትነግረናለች አኹን ራዕይ እያየች ነው›› መባባል ጀመሩ በዚህ መሃል ከመላዕክት አንዱ በደረጃ እንደሚወርድ ዓይነት እየተራመደ ወደ አንድርያና በመምጣት አጠገቧ ቆሞ ‹‹ማንን ትፈልጊያለሽ?›› ብሎ ጠየቃት፡፡ ዓይኗን ከሰቀለችበት ሳትነቅል ‹‹ጌታዬ ሆይ ስለርሱ የተጎዳሁለትን ነፍሴ የወደደችውን የውስጤ ጥማት የሆነውን ኢየሱስ ወዴት ሄደብኝ? እሱን ብቻ ነው የምፈልገው!አለች ጮክ ብላ፡፡ እንባዋ ግድቡ እንደፈረሰበት ወንዝ በጉንጮቿ እየፈሰሰ በልቅሶ መለሰችለት፡፡ ክፍል 27 ይቀጥላል. ቻናላችንን ለመቀላቀል https://t.me/Heavenly_Grace_1 በምለዉ ልንክ በኩል ገብተው ጆይን ይበሉ። ለሃሳብ እና አስተያየት ደግሞ፣ @Dave_one_Bot የምለዉን ይጠቀሙ። ሼርም እንዳይረሳ!
Hammasini ko'rsatish...
Dave ( ባለ በገና)🍎🍇🎸🪗

I looked, and rose up,Nehemiah 4:14 ☞በዚህ ቴሌግራም ቻናል የተለያዩ መሰናዶች ይቀርባሉ! ➩ #አዳዲስ_መዝሙሮች ➩ #ቆየት_ያሉ_ዝማሬዎች #መንፈሳዊ ስነ ፅሁፎች ➩ #Live_WORSHIP_እና_studio_live_worship ➩ #ቅዱሱ የእግዚአብሔር ቃል እና የተለያዩ ትምሕርት ነክ ዝግጅቶች ይቀርባሉ። ለሃሣብ እና አስተያየት ደግሞ @Dave_one_Bot አለላችሁ።

👍 3
አንለያይም ዘማሪት በረከት መገርሳ|Live Worship ⌚️9:00 ደቂቃ | 💾 8.4 MB sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ @Heavenly_Grace_1 @Heavenly_Grace_1         👇JOIN OUR GROUP👇 @Dave_group_chat                 △Join us △ Title: አንለያይም ዘማሪት በረከት መገርሳ|Live Worship
Hammasini ko'rsatish...
👍 2🥰 2 1
እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና። ወደ ዕብራውያን 12:2
Hammasini ko'rsatish...
4
እግዚአብሔር አለ| ዘማሪ ቢኒያም መላኩ|Live Worship watch ️11:30 ደቂቃ | floppy disk 10.7 MB sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ @Heavenly_Grace_1 @Heavenly_Grace_1                 △Join us △ Title: እግዚአብሔር አለ| ዘማሪ ቢኒያም መላኩ|Live Worship
Hammasini ko'rsatish...
👍 4 1
በመገኘትህ!! EBENEZER TAGESSE New Song Duration, 12 minutes and 31seconds, sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ @Heavenly_Grace_1 @Heavenly_Grace_1                 △Join us △ Title:በመገኘትህ!! EBENEZER TAGESSE New Song
Hammasini ko'rsatish...
👍 3 2
የአስደናቂዋ ሴት ማስታወሻ እዉነተኛ ታሪክ! በDave ባለ በገና የተሰናዳ. ክፍል 25. በዓለም የመጨረሻው ቦታ ሰሜናዊ ንፍቀ ክበብ፣ እልም ያለ በርሃ ሰው የማይኖርበት የበረዶ ስፍራ፣ ሳይቤሪያ ነው። ፡ ማንም በዚህ የግዞት ስፍራ ቢጣል ሮጦ ወይም ተጉዞ የትም አይደርስም፡፡ ሰፊ የበረዶ በረሃ ቀዝቃዛና አስቸጋሪ ቦታ ነው፡፡ በሳይቤሪያ በሌላው ዓለም እንደሚታየው አስራ ሁለት ሰዓት ፀሃይ አስራ ሁለት ሰዓት ጨለማ የሚባል ነገር የለም፡፡ ለስድስት ወር ጨለማ ሲሆን ለስድስት ወር ደግሞ ብርሃን አለ፡፡ ብርሃን ማለት የሚያቃጥል ጃንጥላ የሚያዘረጋ የፀሃይ ብርሃን ሳይሆን ለወጉ ያህል የሚታይ ብርሃን እንጂ፡፡ እነ አንድርያና በዚህ ስፍራ ነበር ለአስራዎቹ አመታት የሚሰቃዩት፡፡ ሳይበሪያ የምድር ሲዖል፡፡ መርዝ ጠጥተው ሆድቃቸውን ዘርግፎ እንዲገደሉ በታሰበበት ቀን ያልጠበቁት ነገር የገጠማቸው እስረኞች በሆነው እየተደነቁና እየተገረሙ እርስበእርስ መተያየት ሆነ ስራቸው፡፡ የሚተዋወቀውም ሆነ የማይተዋወቀው ሁሉ በግልፅ መተያየት ጀመረ፡፡ አንዱ የራሱን ቁስል ጉዳትና አካለሰንካላነት ረስቶ በሌላው ወገኑ ላይ በሚያየው ጉዳት ማልቀስና ማዘን ጀመረ፡፡ ምን ያህል እንደተጎዱ እንኳን ለማወቅ እድል የማይሰጥ እስርቤት መታጎር እጅግ አስከፊ ነው፡፡ በሳይቤሪያ የሆነውም ይህ ነው፡፡ ሁሉም የመርዶ ያህል እያለቀሰ መሬት እየደበደበ አንተንም እንዲህ አደረጉህ? አንቺንም እንዲህ አደረጉሽ? ጌታ ይመስገን!!፡፡ ስንት አመት ታሰርክ? አንተስ? አንቺስ? በሚል ጥያቄ ጨዋታው ደርቶ ለቅሶና ሳቅ ተቀላቅሎ አዲስ ትኩስ ሬሳ የወጣበት ቤት መሰለ፡፡ ‹‹እኔ እገሌ ነኝ እኔ ደግሞ እገሊት እባላለሁ፡፡ ጀኔራል እገሌ፣ መከላከያ ሚኒስትርና የባህር ኃይል ልዩ ኮማንዶ አዛዥ እገሌ ነኝ፤ የኮሚኒስት ተማሪዎች አባል ነኝ፤ እኔ ደግሞ ለአምስትደቂቃ የሰማሁትን ኢየሱስ አማኝ ነህ ተብዬ ተያዝኩ ያንጊዜ ሲይዙኝ አማኝ እንዳልሆንኩ ለማስረዳት ብዙ ጣርኩኝ ይሁን እንጂ የሚሰማኝ አጥቼ ታፍሼ ወደዚህ ገባሁ፡፡ እዚህ ከገባሁ በኋላ ግን ጣፋጩን ኢየሱስን አገኘሁት፡፡›› ይላል፡፡ በዚህ መሃል ነበር ሌሊት ዘጠኝ ሰዓት አከባቢአስደንጋጭ ትረካ የተሰማው፡፡ እንዴት ወደ ሳይቤሪያ እንደመጣ አንድ ፀጉሩ የተጨፈረረ የቀኝ ዓይኑ በግርፋት የፈሰሰ ወገቡ በኃይለኛ ምት ተሰብሮ መቀመጥ ያልቻለ ሰው እየሳቀ ከፊቱ የደስታ ፈገግታ የድል ስሜት እየታየበት ተንበርክኮ መናገር ጀመረ፡፡ ያሳለፈው የእስር ዘመኑ እንዴት እንደተያዘ ከመያዙ በፊት ከነበረው ህይወት ይልቅ ተይዞ ወደዚህ የምድር ሲኦል ሳይቤሪያ ስለ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በተቀበለው መከራ ደስተኛ እንደሆነ ይመሰክራል፡፡ እርሱ ሲመሰክር እስረኞቹ በሙሉ እንባ በእንባ ሆነው ያደምጡታል፡፡ የኮሚኒዝምን ክብረ በዓል ለማክበር ከሰልፍ ተመልሰን ወደ መሰብሰቢያ አዳራሽ ስንገባ እህታችን እንበላትና አንድርያና ያ የተለመደው ኃይለኛ አነጋገርዋን ስትናገር አምላኬን ስትሳለቅበት ሰምቼ ማለፍ አቃተኝ፡፡ ሃሳባውያን አላችሁ? ከሌንን ወዲያ መሪ ከኮሚኒስት ወዲያ ፓርቲ በዓለም ላይ የለም ስትል ጊዜ ጌታዬ ከሁሉ በላይ መሆኑን መግለፅ እንዳለብኝ ልቤ መሰከረልኝ! ለመጣልኝ ሀሳብ እምቢ ማለት ስላልቻልኩ ወጥቼ ራሴን ገለጥኩ፡፡ ሌሎችም እንደዛው፡፡ ያን ጊዜ አንድርያና ጀርባዬንና ወገቤን በዚያ ጫማዋ ስትረግጠኝ እንደምንም ብዬ ‹‹እንወድሻለን›› ብያት እኛ እያለቀስን እስዋ እየሳቀች ተለያየን እዚህ ቦታ ከመጣሁ እነሆ አስራ ስድስት ዓመት አልፎኝ አስራ ሰባተኛዬን ልይዝ ነው፡፡ ጌታ ይመስገን፡፡›› አለ ሌላውም መናገር ጀመረ ‹‹አጠቃላይ ስብሰባ መሃል ሳለን ለብዙ ጊዜ ያስቸገረን ጉዳይ በድንገት ተሳካልኝና ሳላስበው በዚያ በቆምኩበት ስፍራ ‹ሃሌ ሉያ! ጌታ ይመስገን› ብዬ ተናገርኩ፡፡ ጉባዔው ለብዙ ጊዜ የተቸገረበትን የክዋክብት የብርሃን ዓመትና በጨረቃ ላይ ያለው ጉም ነገር ምንነት በምርምር በማግኘቴ ልዩ ነገር ሊሸልመኝ መንግስት ተዘጋጅቶ ሳለ ‹ሃሌሉያ በማለቴ ተደናግጠው ታላቁ ሰው የማይገባውን ነገር አመነ ተብዬ ሽልማቴ ቀርቶ ሳይቤሪያ ገባሁ፡፡ እዚህ ከመጣ ሃያ ዓመት ሞላኝ፡፡›› አለ ሁሉም በሳይበሪያ ያሉት ቅዱሳን በሚሰሙት ነገር እንባቸው በጉንጫቸው መሃል ይፈሳል፡፡ ይሁን እንጂ የሌሎቹ ለቅሶ ሌላ ነው የአንድርያና ለቅሶ ግን ሌላ ነበር፡፡ ** ሌላዋ ተነሳች እኔ በትምህርት ቤታችን የተማሪዎች ህብረት ሰብሳቢ ነበርኩ የሁለት ዓመት ቦይ ፍሬንዴ ለካ እኔ ሳላውቅ ጌታን ያመልክ ነበር፡፡ የመጨረሻ ስድስት ወራት ሁሉ ጠባዩ ፈፅሞ ተለወጠብኝ፡፡ መዝናናት መውጣት ሁሉ አቆመ፡፡ አንድ ቀን ስለኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ስለመሞቱ ታሪክ ሲነግረኝ በጣም ሳቅሁኝ፡፡ ያንን ታሪክ ስሰማ ከመገረሜ የተነሳ ስለ ሰው ኃጢአት ሲል ራሱን ለስቃይ ለስቅላት አሳልፎ የሚሰጥ እሱ ሞኝ መሆን አለበት ብዬ አሾፍኩኝ፡፡ ምናለ የአንተ ኢየሱስ ህይወት ያህል ነገር ለማይረባ ዓላማና ተከታይ ለማያገኝበት ፓርቲ ራሱን በከንቱ አሳልፎ ከሚሰጥ ቢቀርበት? ያሳዝናል አልኩት፡፡ ቢያንስ ዘመድ አዝማድ የለውም? መክሮ የሚያስተወው? ብዬ አስባለሁ፡፡ እሱ ግን ተስፋ ሳይቆርጥ ለኔ መመስከሩን ቀጠለ፡፡ በመጨረሻም እሱ ጠፋብኝ ምናልባት በወጣበት ተይዞ አልያም ተገድሎ ይሆናል ብዬ አስባለሁ፡፡ እሱ ይጥፋ እንጂ ያ የተናገረኝ ቃል ግን ሁል ጊዜ በልቤ ያቃጭላል፡፡ ሞቱ ስቅላቱ ኮ ስላንቺ ሀጢአት ብሎ ነው ያለኝ ቃል እረፍት ነሳኝ ፡ እኔን ሳያውቀኝ ስለኔ ሀጢአት ሲል የሚሞት ማነው? በሚል ጥያቄ ስላለስ ቀናት አለፉብኝ፡፡ በመጨረሻም ጌታን ባገኘሁ በዓመቴ በአንድርያና ልዩ ትዕዛዝ ወደ ዚህ ወደ ጌታ ቤት የህይወት ማጣሪያ ወንፊት ስንዴና እንክርዳድ መለያ ሳይቤሪያ መጣሁ፡፡ ዛሬ አስራ ስድስት ዓመት ከአራት ወር ሆኖኛል፡፡ጌታ ይመስገን፡፡ አንድርያና ባለችበት ቦታ ጌታ ይባርካት ስለእርስዋ መፀለይን አናቋርጥም ወገኖቼ ሳዖልን የለወጠ እሱዋንም ይለውጣታል፡፡ ደግሞም ውደድዋት፡፡›› በማለት ስትጨርስ ሌሎችም ቀጠሉ በታሪካቸው መጨረሻ ላይ ንግግራቸውን የሚቋጩት ‹‹አንድርያና ልካኝ አንድርያና ይዛኝ .... አንድርያና ገርፋኝ፡፡›› በማለት ነበር፡፡ ክፍል 26 ይቀጥላል. ቻናላችንን ለመቀላቀል https://t.me/Heavenly_Grace_1 በምለዉ ልንክ በኩል ገብተው ጆይን ይበሉ። ለሃሳብ እና አስተያየት ደግሞ፣ @Dave_one_Bot የምለዉን ይጠቀሙ። ሼርም እንዳይረሳ!
Hammasini ko'rsatish...
Dave ( ባለ በገና)🍎🍇🎸🪗

I looked, and rose up,Nehemiah 4:14 ☞በዚህ ቴሌግራም ቻናል የተለያዩ መሰናዶች ይቀርባሉ! ➩ #አዳዲስ_መዝሙሮች ➩ #ቆየት_ያሉ_ዝማሬዎች #መንፈሳዊ ስነ ፅሁፎች ➩ #Live_WORSHIP_እና_studio_live_worship ➩ #ቅዱሱ የእግዚአብሔር ቃል እና የተለያዩ ትምሕርት ነክ ዝግጅቶች ይቀርባሉ። ለሃሣብ እና አስተያየት ደግሞ @Dave_one_Bot አለላችሁ።