uz
Feedback
የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር minister of labor and skills

የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር minister of labor and skills

Kanalga Telegram’da o‘tish

ብቁ ሰራተኛ . ብቁ ቀጣሪ . ብቁ ውሳኔ ሰጭ.

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር minister of labor and skills analitikasi

የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር minister of labor and skills (@bekuelmisgov0) kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 12 349 obunachidan iborat bo'lib, Marketing toifasida 854-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 729-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 12 349 obunachiga ega bo‘ldi.

23 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -380 ga, so‘nggi 24 soatda esa -8 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 1.13% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 0.75% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 140 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 93 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 0 ta reaksiya keladi.
  • Tematik yo‘nalishlar: Kontent barnoota, kana, chaanaalii, afaan, waver kabi asosiy mavzularga jamlangan.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
ብቁ ሰራተኛ . ብቁ ቀጣሪ . ብቁ ውሳኔ ሰጭ.

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 24 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Marketing toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

12 349
Obunachilar
-824 soatlar
-947 kunlar
-38030 kunlar
Postlar arxiv
ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን በማጠናከር የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ውጤታማ ተግባራት እየተከናወኑ ነው ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን በማጠናከር የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ውጤታማ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለጹ፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በለውጡ መንግሥት የተተገበሩ የሪፎርም ሥራዎች የወጣቶችን ኢኮኖሚና ማኅበራዊ ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ ተጨባጭ ውጤቶችን አስገኝተዋል። ባለፉት 4 ዓመታት በተከናወኑ ዘርፈ-ብዙ የሪፎርም ሥራዎች ለ19 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠራቸውን ጠቁመው፣ ከዚህም መካከል 75 በመቶ በላይ የሚሆኑት ወጣቶች መሆናቸውን ተናግረዋል። ለውጡ ካስገኛቸው ዋና ዋና ስኬቶች መካከል ወጣቶች ከተለመደው የቅጥር ሐሳብ ወጥተው ወደ ሥራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩና ለሌሎች የሥራ ዕድል እንዲፈጥሩ ምቹ ሁኔታዎችን መፈጠራቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡ በተጨማሪም የቤተሰብ የንግድ ሥራዎች እንዲስፋፉ በማድረግ ረገድ አበረታች ውጤቶች መገኘታቸውን አክለዋል፡፡ የዲጂታል ቴክኖሎጂዎች መስፋፋትና ለዘርፉ የተሰጠው ልዩ ትኩረት ለወጣቶች ዘመናዊ፣ ፈጣንና ምቹ የሥራ ዕድሎችን የፈጠረ ሲሆን፣ ይህም በዓለም አቀፍና በአህጉራዊ የዲጂታል የሥራ ገበያ ላይ የሀገሪቱንና የወጣቶቹን ተወዳዳሪነት ማሳደጉን አብራርተዋል። የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሙና አሕመድ በበኩላቸው፤ ከለውጡ በኋላ የወጣቶችን አቅም በማሳደግ ረገድ ሰፊ ስራዎች መሰራታቸውን ጠቅሰዋል፡፡ በዚህም ተስፋ ሰጪ፣ ዘላቂና ክህሎት መር የሥራ ዕድሎችን በተሻለ ሁኔታ ለመፍጠር ትልቅ አቅም መገንባቱን አብራርተዋል። በመዲናዋ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ከሆኑት መካከል ወጣት ጋሻው ዓለሙ የመኪና ጎማና ባትሪዎችን መልሶ ጥቅም ላይ የማዋል ሥራ ላይ መሰማራቱን ጠቅሷል፡፡ የምናመርታቸው ምርቶች የአካባቢ ብክለትን ከመቀነስና ቆሻሻን ወደ ሀብት ከመቀየር ባለፈ፣ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን የሚያሳድጉና ሰፊ የሥራ ዕድል የሚፈጥሩ ናቸው ብሏል። በማኅበር በመደራጀት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን የሚተኩ የቤትና የቢሮ መገልገያ ቁሳቁሶችን እያመረቱ መሆናቸውን የተናገረው ደግሞ ወጣት አስቻለው ጌትዬ ነው፡፡ በቀጣይም የምርቶቻቸውን የገበያ ተደራሽነትና የሥራ ዕድሎችን ይበልጥ ለማስፋፋት እየሠሩ መሆናቸውን ተናግሯል። መረጃው የኢዜአ ነው። ሰኔ 14/2018 ዓ.ም፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር

አካባቢያዊ ጸጋን መሰረት ያደረገው ቆላማ አካባቢዎች የሚገኙ ኢንተርፕራይዞችን ምርታማነትና ኑሮ የሚያሻሽል ሥራ ! ​በኢትዮጵያ ቆላማ አካባቢዎች የሚገኙ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን (MSMEs) ብቁና ተወዳዳሪ ለማድረግ እንዲሁም የኅብረተሰቡን የኑሮ ደረጃ በዘላቂነት ለማሻሻል ያለመ የክህሎት ሥልጠና በአዳማ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተሰጥቷል። በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አዘጋጅነትና በቆላማ አካባቢዎች የዘላቂ ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት (LLRP-II) ድጋፍ የተሰናዳው ይህ ሥልጠና፤ በወተት ሀብት ልማት፣ በዶሮ እርባታ እና በዕሴት ሰንሰለት (Value Chain) ላይ ያተኮረ የሥራ ዕድል ፈጠራን መሠረት ያደረገ ነው። ​በቆላማ አካባቢዎች ለሚገኙ የሥራ ዕድል ፈጠራ አስተባባሪዎች፣ ባለሙያዎችና ተጠቃሚ ኢንተርፕራይዞች የተሰጠው ይህ ሥልጠና ዋና ፋይዳው በቆላማ አካባቢዎች በስፋት የሚገኙትን የተፈጥሮና የእንስሳት ሀብት ጸጋዎች በዘፈቀደ ሳይሆን በእውቀትና በሳይንሳዊ መንገድ በማልማት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም መቀየር ነው ተብሏል። ​ በአካባቢው ያሉ ኢንተርፕራይዞች ከለመዱት ባህላዊ የእንስሳት አያያዝና እንክብካቤ አሠራር ተላቀው፣ ምርትና ምርታማነትን በሚያሳድጉ ዘመናዊ የቴክኖሎጂና የአመራረት ስልቶች እንዲተኩ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርም ተጠቁሟል ። በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የአቅም ግንባታ ዴስክ ኃላፊ አቶ መላኩ ወልደዮሐንስ እንደገለጹት፣ ይህ ስልጠና በቆላማ አካባቢዎች የሚገኙ ወጣቶችና ሴቶች በእንስሳት ሀብት ልማት ላይ በስፋት እንዲሳተፉ በማድረግ፣ የገቢ ምንጫቸውን እንዲያሳድጉና የኑሮ ደረጃቸውን በዘላቂነት እንዲያሻሽሉ ዕድል ይከፍታል። ​ አክለውም በተዘጋጁ ሞጁሎች የተሰጠው ይህ ስልጠና በቆላማ አካባቢዎች በወተት፣ በዶሮ እርባታና በማድለብ ዙሪያ ያሉ እንቅፋቶችን በመለየት ወደ መልካም አጋጣሚና ሰፊ የሥራ ዕድል መቀየር የሚያስችል መንገዶችን ማመላከቱን ገልፀዋል ። ​ በተጨማሪም በንድፈ-ሐሳብ ብቻ ሳይወሰን በተግባር የተደገፈ ስልጠና በመሆኑ፣ ሰልጣኞቹ ወደየክልሎቻቸው ሲመለሱ አዳዲስ ኢንተርፕራይዞችን በብቃት ለማደራጀት እንዲሁም ነባሮቹን ለመደገፍና ለማጠናከር የሚያስችል እውነተኛ አቅም እንደሚፈጥር ተናግረዋል። ሰኔ 12/2018 ዓ.ም፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር

የጀርመን የልማት ትብብር ድርጅት (KFW) ልዑካን ቡድን በገዋኔ ግብርና ኮሌጅ የሥራ ጉብኝት አደረገ በጉብኝቱም የኮሌጁን ሥልጠና በጥራትና በዲጂታላይዜሽን ለማገዝ የሚያስችል ከፍተኛ የድጋፍ ስምምነት ተደርሷል። በዚህ ስምምነት ኮሌጁን ሙሉ በሙሉ በዘመናዊ የሶላር ኃይል አቅርቦት ለመገንባት ከ800 እስከ 1000 ሜትር ካሬ የሚሸፍን የሶላር ፓወር ተከላ እና አነስተኛና መካከለኛ የሶላር ውኃ መሳቢያ ፓምፖች እንዲገጠሙለት ተወስኗል። በተጨማሪም ዘመናዊ ላብራቶሪዎች፣ ስማርት ክፍሎች፣ የዲጂታል ሥልጠና አቅሞች፣ የእርሻ ትራክተር  እንዲሁም ለተማሪዎች የመስክ ጉዞና ለተቋማዊ አገልግሎት የሚውሉ ተሽከርካሪዎች  የድጋፉ አካል መሆናቸው ተገልጿል። በኮሌጁ ውስጥ የወተትና የወተት ተዋፅኦ ማቀናበሪያ፣ የአትክልትና ፍራፍሬ ማቀናበሪያ፣ የእንስሳት መኖ ማቀናበሪያ  የአግሮ-ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪዎችን ለማቋቋም ስምምነት ላይ ተደርሷል። እነዚህ በኢንዱስትሪ ደረጃ የሚቋቋሙ ማዕከላት ለተማሪዎች የተግባር መማሪያ ከመሆናቸውም በላይ፤ ለአካባቢው አርብቶ አደር ማህበረሰብ ሰፊ የሥራ ዕድል የሚፈጥሩና የኮሌጁን የውስጥ ገቢ በከፍተኛ ደረጃ የሚያሳድጉ ናቸው ተብሏል። የKFW ያደረገው ይህ አዲስ ድጋፍ በገንዘብ ሲገመት ከ280 ሚሊዮን ብር በላይ ሲሆን፤ ቀደም ሲል ሚኒስቴሩ ባመቻቸው ዕድል  ከቻይና መንግስት  ያገኘውን የ90 ሚሊዮን ብር የዲጂታላይዜሽን ማጠናከሪያ ድጋፍ ጨምሮ፣ ኮሌጁ በአጠቃላይ ከ370 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የአጋር አካላት ድጋፍ  ተደርጎለታል፡፡ ሰኔ 14/2018 ዓ.ም፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር

የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ጉዟችን አካል እና የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ እመርታ ትልቅ ማሳያ የሆነው ሞጆ የተገነባው የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ተመርቆ አገልግሎት ጀምሯል። ቁልፍ ሀገራዊ ፋይዳ ያ
+6
የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ጉዟችን አካል እና የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ እመርታ ትልቅ ማሳያ የሆነው ሞጆ የተገነባው የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ተመርቆ አገልግሎት ጀምሯል። ቁልፍ ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸውን መሰል ፋብሪካዎች ግንባታ፣ ዓለም አቀፍ ኢንቨስትመንቶችን በመሳብ በመላ ሀገሪቱ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በተግባር ያረጋገጠ ነው። ‎ ‎​ፋብሪካው የዓለም ዓቀፍ ጥራትና ተወዳዳሪነት መስፈርቶችን የሚያሟሉ የሴራሚክ ምርቶችን የሚያቀርብ ሲሆን፣ ለምርቱ የሚያስፈልጉትን ጥሬ ዕቃዎች ከ80 በመቶ በላይ ከሀገር ውስጥ ዐቅም ያገኛል። ይህ ስኬት ኢትዮጵያ የራሷን የተፈጥሮ ሀብትና እምቅ ጸጋ የመጠቀም ብቃቷን ከመገንባቱ ባሻገር፣ ከውጭ ገቢ ምርቶች ላይ ያለንን ጥገኝነት በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሰዋል።

‘ፈልጉልኝ’፤ ብቁ ባለሙያዎችን ለአሠሪዎች፣ ፍትሃዊ የሥራ ዕድል ለሁሉም ዜጎች! የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት አካል የሆነና አሠሪና ሠራተኞችን በቀላሉ ማገናኘት የሚያስችል ‘ፈልጉልኝ’ የተሰ
+7
‘ፈልጉልኝ’፤ ብቁ ባለሙያዎችን ለአሠሪዎች፣ ፍትሃዊ የሥራ ዕድል ለሁሉም ዜጎች! የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት አካል የሆነና አሠሪና ሠራተኞችን በቀላሉ ማገናኘት የሚያስችል ‘ፈልጉልኝ’ የተሰኘ ሀገራዊ ዲጂታል መተግበሪያ ዛሬ በይፋ አስመርቀን ወደ ሥራ አስገብተናል። በመርሃ ግብሩ ‘ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030’ ስትራቴጂን መሠረት በማድረግ የመጪውን ዘመን የሥራ ገበያ መልክ እና የሰው ሠራሽ አስተውሎትን መሰረት ያደረጉ ዲጂታል መተግበሪያዎች በሀገራዊ ልማት ውስጥ ያለውን ሚና በጥልቀት ያየንበት ውጤታማ የፓናል ውይይትም አካሂደናል። ወደ ሥራ የገባው ይህ ዲጂታል መተግበሪያ፤ በሀገራችን ምጣኔ-ሀብት ውስጥ በሥራ ገበያው ውስጥ ያለውን የመረጃ ክፍተት በመቅረፍ ሥራ ፈላጊ ዜጎችንና አሠሪዎችን ካሉበት ሆነው በቀጥታ የሚያገናኝ ዘመናዊ የሥራ ሥነ-ምህዳር ነው። መተግበሪያው መደበኛ ያልሆነውን የሥራ ዘርፍ ወደ መደበኛ የኢኮኖሚ ሥርዓት ከማሸጋገሩም በላይ፣ በማስረጃ ላይ የተመሠረተ የፖሊሲ ቀረጻን በማገዝ እና አስተማማኝ የመረጃ ሉዓላዊነትን ከማረጋገጥ አኳያም ሚናው የላቀ ነው። ከሁሉ በላይ በቴክኖሎጂ አማካኝነት የሥራ ገበያውን ትክክለኛ ፍላጎት በማሳየት፣ የትምህርትና ሥልጠና ተቋማት የሥራ ገበያው የሚፈልገውን ብቁ የሰው ኃይል እንዲያፈሩ ስልታዊ አስተዋጽኦም ያበረክታል። ይህንን ዘመናዊ መተግበሪያ እውን በማድረግ ሂደት ሚና ለነበራችሁ አካላት በሙሉ ያለኝ ልባዊ ምስጋና የላቀ ነው። የሥራ ባለቤት እርስዎ ነዎት!

ኮሌጁ የሻይ ቅጠል እና የቅመማ ቅመም ምርት የልህቀት ማዕከል እንዲሆን እየተሠራ መሆኑ ተገለፀ ሚዛን ግብርና ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ሥልጠና ኮሌጅ የሻይ ቅጠል እና የቅመማ ቅመም ምርት የልህቀት ማዕ
+8
ኮሌጁ የሻይ ቅጠል እና የቅመማ ቅመም ምርት የልህቀት ማዕከል እንዲሆን እየተሠራ መሆኑ ተገለፀ ሚዛን ግብርና ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ሥልጠና ኮሌጅ የሻይ ቅጠል እና የቅመማ ቅመም ምርት የልህቀት ማዕከል ሆኖ እንዲያገለግል በትኩረት እየተከናወኑ መሆኑ ተነግሯል። ይህ ይፋ የተገለፀው ኮሌጁ የሀገሪቱን የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥና የግብርናውን ክፍለ-ኢኮኖሚ በዘመናዊ ክህሎት ለመደገፍ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 499 ባለሙያዎችን ባስመረቀበት ወቅት ነው። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የግብርና ቴክኒክና ሙያ መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ጌታቸው ደምሴ እንደገለጹት፤ ኮሌጁ በመካከለኛ ደረጃ ብቁና ተወዳዳሪ የሰው ኃይል በማፍራት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ሲያበረክት ቆይቷል። ኮሌጁ የነበረውን ታሪካዊ ሚና ይበልጥ በማጠናከር፣ አገራዊ ፍላጎትንና የአካባቢውን ዕምቅ የተፈጥሮ ጸጋ መሠረት በማድረግ፣ በቀጣይ የሻይ ቅጠል እና የቅመማ ቅመም ምርት የልህቀት ማዕከል ሆኖ እንዲያገለግል በትኩረት እየተሠራ ነው። ኮሌጁን ወደ ልህቀት ማዕከልነት እንዲሸጋገር የተጀመሩት ስትራቴጂካዊ ሥራዎች ለዘርፉ ዘመናዊነትና ለምርት ዕድገት ወሳኝ ሚና ይጫወታሉ ብለዋል። የኮሌጁ ዲን አቶ ካሳሁን ናይክ በበኩላቸው፤ ኮሌጁ ያስመረቃቸው ባለሙያዎች በንድፈ-ሀሳብና በተግባር የተደገፈ ጥራት ያለው ሥልጠና የወሰዱ ናቸው። በመሆኑም የአርሶ አደሩን ምርታማነት በቴክኖሎጂ ለማሳደግ የሚደረገውን አገራዊ ጥረት በግንባር ቀደምትነት የሚያግዙ ናቸው ብለዋል።

በኢትዮጵያ በልዩ የሕክምና ዘርፍ ሥልጠና ላይ ከሚገኙ እና ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ከመጡ 4ዐዐ በላይ የሕክምና ባለሙያዎች መካከል፤ ከሩዋንዳ ከመጡ 128 የሕክምና ባለሙያዎች ጋር በጋራ ማዕድ ቆር
+2
በኢትዮጵያ በልዩ የሕክምና ዘርፍ ሥልጠና ላይ ከሚገኙ እና ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ከመጡ 4ዐዐ በላይ የሕክምና ባለሙያዎች መካከል፤ ከሩዋንዳ ከመጡ 128  የሕክምና ባለሙያዎች ጋር በጋራ ማዕድ ቆርሰናል። ‎እነዚህ ባለሙያዎች የአኅጉራችን የጤና ዘርፍ የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚጠይቀውን ከፍተኛ ዕውቀትና የላቀ ብቃት ለማሟላት ታምነው እየተጉ ያሉ ሲሆን፤ ቀጣዩን አፍሪካዊ ትውልድ በሕክምና ዘርፍ የሚኖረውን የመሪነት ሚና በማረጋገጥ ላይ የሚገኙ ተቋማት አካል ናቸው። ‎በጋራ ዕውቀትና ዓላማ፣ ይበልጥ ጤናማ የሆነች አፍሪካን አብረን መገንባታችንን እንቀጥላለን።

የቡና ምርት ሂደትን ምቹ፣ ጤናማና ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችል ፕሮጀክት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ከዓለም አቀፍ ሥራ ድርጅት ጋር በመተባበር በጌዴኦ ዞን በቡና ሥራ ላይ የተሰማሩ የ
+2
የቡና ምርት ሂደትን ምቹ፣ ጤናማና ውጤታማ   ለማድረግ የሚያስችል ፕሮጀክት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ከዓለም አቀፍ ሥራ ድርጅት ጋር በመተባበር በጌዴኦ ዞን በቡና ሥራ ላይ የተሰማሩ የሕብረት ሥራ ማህበራትና የግል ድርጅቶች የሥራ እንቅስቃሴ በተመለከተ ድጋፍና ክትትል አድርገዋል። ድጋፍና ክትትሉ  የቡና ምርትን እሴት ሰንሰለት መሠረት ባደረገ  መልኩ የሥራ  ቦታዎችን ለማሻሻል  ‹‹ምቹ ሥራዬ››  በሚል  የተሰየመውን ፕሮጀክት ወደ ተግባር ለማስገባት  ያለመ እንደሆነ ተመላክቷል። የድጋፍና ክትትል ቡድኑ አባላት  ለማህበራቱ በቡና እሴት  ሰንሰለት አተገባበርና በቡና ምርት አዘገጃጀት እንዲሁም በሥራ ቦታ ደህንነትና ጤንነት ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰጥተዋል። በየትኛውም ማህበራትም ሆነ  በግል ድርጅት የሚቀጠሩ ጊዜያዊና ቋሚ ሠራተኞች የሥራ ሁኔታቸውን አስመልክቶ ቋሚ ክትትልና ድጋፍ ለማድረግ እንዲያስችል በሥራና ክህሎት ቢሮ በኩል እውቅና አግኝተው መሠማራት እንዳለባቸው  ተጠቁሟል፡፡ የፕሮጀክቱ ዋና ዓላማ  በቡና እሴት  ሰንሰለት ላይ ለተደራጁ ማህበራትና ለግል  ድርጅቶች በምርት ጥራት፣ በሥራ ላይ ደህንነትና ጤንነት እና በህፃናቶች ጉልበት ብዝበዛ ላይ ያሉ ችግሮችን በጥናት በመለየት የመፍትሔ አቅጣጫዎችን በማመላከት ላይ ያተኩራል፡፡

በሀገር ልጆች፤ በጥበበኛ እጆች! የኢትዮጵያ የዲጂታል ሉዓላዊነት አዲስ ምዕራፍ ! በአፍሪካ የመጀመሪያው AFIS - ABIS የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ወጣቶች ለ
በሀገር ልጆች፤ በጥበበኛ እጆች! የኢትዮጵያ የዲጂታል ሉዓላዊነት አዲስ ምዕራፍ ! በአፍሪካ የመጀመሪያው AFIS -  ABIS የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ወጣቶች ለምቶ  ሥራ ላይ የዋለ ትልቅ ሀገር በቀል የዲጂታል መሠረተ ልማት ነው። ይህ ሥርዓት የእጅ፣ የፊት እና የአይን አሻራ መረጃ ወስዶ ከማመሳከርና መንትዮችና ጨምሮ ከብዙ መረጃዎች መካከል ትክክለኛውን መረጃ በአጭር ሰከንዶች  ለይቶ ከማውጣት አኳያ ዓለም አቀፍ መመዘኛዎችንና ደረጃዎችን ስለማሟላቱ ተረጋግጧል። በዚህም በዓለም አቀፍ ደረጃ በዘርፉ ከፍተኛ ተቀባይነት ባለው የአሜሪካ ብሔራዊ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (NIST) የግምገማ ስርዓት ውስጥ እንዲያልፍ ተደርጓል። በዚህም በሳይንሳዊ መለኪያዎች መሰረት የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ABIS  ውጤታማነቱ ተረጋግጧል፡፡  ዓለም አቀፍ ምዘናን ማለፍ የቻለው ይህ ሀገር በቀል ሥርዓት፣ የመረጃ ሉዓላዊነታችንን ለማረጋገጥ እና በመስኩ ያለንን የውጭ ጥገኝነት በከፍተኛ ደረጃ ለመቀነስ የሚደረገውን ጥረት በእጅጉ ያግዛል። ስርዓቱ ራሱን በቻለ ሥነ-ምህዳራዊ መዋቅር ከተለያዩ ስርዓቶች ጋር የመቀናጀት የላቀ የቴክኖሎጂ አቅም ያለው በመሆኑ፣ ከብሔራዊ መታወቂያ፣ ከፓስፖርት፣ ከፍሮንሲክ ስርዓት፣ ከታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር እና ሌሎች ተዛማጅ ስርዓቶች ጋር በተቀናጀ መልኩ የመስራት አቅም አለው። ስርዓቱን እዚህ ደረጃ ላይ ለማድረስ ቀን ከሌት ለሠሩ ወጣት ቴክኖሎጂስቶች፣ ላስተባበሩ አመራሮች ልባዊ  ምስጋናዬ የላቀ ነው፡፡   የሥራ ባለቤት እርስዎ ነዎት!

የአካባቢ ጸጋዎችን መሰረት ያደረጉ የሥራ ዕድል ፈጠራ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገቡ ነው በየአካባቢው የሚገኙ የፈጠራና የተፈጥሮ ጸጋዎችን በመለየትና የሥራ ዕድሎችን በማስፋፋት ተጨባጭ ውጤቶች እ
+3
የአካባቢ ጸጋዎችን መሰረት ያደረጉ የሥራ ዕድል ፈጠራ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገቡ ነው በየአካባቢው የሚገኙ የፈጠራና የተፈጥሮ ጸጋዎችን በመለየትና የሥራ ዕድሎችን በማስፋፋት ተጨባጭ ውጤቶች እየተገኙ መሆኑን የተለያዩ ክልሎች የሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ኃላፊዎች ገለጹ። በኢትዮጵያ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማሳደግ፣ የግል ዘርፉን ለማበረታታትና የሥራ አጥነት ቁጥርን ለመቀነስ በርካታ መዋቅራዊና ሕጋዊ ሪፎርሞች ተከናውነዋል። ለአብነትም የአምራች ኢንዱስትሪዎችን ማስፋፋት፣ ለሥራ ዕድል ቅድሚያ የሚሰጥ ስትራቴጂ ትግበራ፣ ተቋማዊ ሪፎርም እንዲሁም የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪትን ማመቻቸት በዋናነት የሚጠቀሱ ተግባራት ናቸው። የተለያዩ ክልሎች የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊዎች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የአካባቢ ጸጋዎችን በጥናት በመለየት የሥራ ዕድልን ለማስፋፋት የተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶችን አስገኝተዋል። የአካባቢውን ጸጋ ተጠቅመው ዜጎች በማኅበረሰብና በቤተሰብ የንግድ ሥራዎች ላይ እንዲሰማሩ ምቹ ሁኔታዎች መፈጠራቸውን አመልክተው፤ የሥልጠና፣ የብድር እና የሌሎች ተያያዥ ድጋፎችን በማድረግ የዜጎች ውጤታማነት ይበልጥ እየጎለበተ መምጣቱን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት አማካኝነት የሥራ ፈላጊዎች ምዝገባና የሥራ ዕድል ፈጠራ መረጃዎችን በዘመናዊ መልኩ በማደራጀት፣ ቀልጣፋ፣ ግልጽና ተደራሽ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን ኃላፊዎቹ ጠቁመዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ተመስገን ኃይሌ፤ በክልሉ የሀገር ውስጥ የሥራ ዕድሎችን ለማሳደግ የአካባቢ ጸጋዎችን በመለየት ዜጎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ጉዟችን አካል እና የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ እመርታ ትልቅ ማሳያ የሆነው ሞጆ የተገነባው የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ተመርቆ አገልግሎት ጀምሯል። ቁልፍ ሀገራዊ ፋይዳ ያ
+8
የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ጉዟችን አካል እና የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ እመርታ ትልቅ ማሳያ የሆነው ሞጆ የተገነባው የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ተመርቆ አገልግሎት ጀምሯል። ቁልፍ ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸውን መሰል ፋብሪካዎች ግንባታ፣ ዓለም አቀፍ ኢንቨስትመንቶችን በመሳብ በመላ ሀገሪቱ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በተግባር ያረጋገጠ ነው። ‎ ‎​ፋብሪካው የዓለም ዓቀፍ ጥራትና ተወዳዳሪነት መስፈርቶችን የሚያሟሉ የሴራሚክ ምርቶችን የሚያቀርብ ሲሆን፣ ለምርቱ የሚያስፈልጉትን ጥሬ ዕቃዎች ከ80 በመቶ በላይ ከሀገር ውስጥ ዐቅም ያገኛል። ይህ ስኬት ኢትዮጵያ የራሷን የተፈጥሮ ሀብትና እምቅ ጸጋ የመጠቀም ብቃቷን ከመገንባቱ ባሻገር፣ ከውጭ ገቢ ምርቶች ላይ ያለንን ጥገኝነት በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሰዋል።

ለሥራ ዕድል ፈጠራና ለወጣቶች ተጠቃሚነት የተደረገ ድጋፍ የሲዳማ ክልል የሥራና ክህሎት ቢሮ ከእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ጋር በመቀናጀት፣ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠርና ግብርናን ለማዘመን በ
+4
ለሥራ ዕድል ፈጠራና ለወጣቶች ተጠቃሚነት የተደረገ ድጋፍ የሲዳማ ክልል የሥራና ክህሎት ቢሮ ከእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ጋር በመቀናጀት፣ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠርና ግብርናን ለማዘመን በግብርና ዘርፍ ለተደራጁ ወጣቶች ትራክተሮች አስረከበ። በISVCD ፕሮጀክት ድጋፍ በ32 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገዙ 10 ትራክተሮች፣ በተለያዩ ወረዳዎች በ10 ማህበራት ለተደራጁ 148 ወጣቶች ተላልፈዋል። የሲዳማ ክልል የሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትልና የሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ከፍያለው ከበደ ድጋፉ የሥራ አጥነት ችግርን ለመቀነስ የሚረዳ መሆኑንና ተጠቃሚ ወጣቶች በሙያዊ ሥልጠና ተደግፈው ወደ ሥራ እንደሚገቡ ገልጸዋል። ወጣቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመረው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ለተጠቃሚ የሆኑ ወጣቶች ወደፊትም የሙያ ሥልጠና እና የቴክኒክ ድጋፍ እንደሚሰጥ የተገለጸ ሲሆን፣ ይህም በክልሉ የዘላቂ ልማትና የሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትልቅ ለውጥ ያመጣል ተብሎ ይጠበቃል።

በድሬደዋ የወጣቶችን የስራ ዕድል ተጠቃሚነት ያሳደጉ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ -ከንቲባ ከድር ጁሃር በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር የወጣቶችን የስራ ዕድል ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባ
በድሬደዋ የወጣቶችን የስራ ዕድል ተጠቃሚነት ያሳደጉ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ -ከንቲባ ከድር ጁሃር በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር የወጣቶችን የስራ ዕድል ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ከንቲባ ከድር ጁሃር ገለጹ። የሀገር ውስጥና የውጭ አገራት የስራ ስምሪትን ለማመቻቸት ያለመ የአሰሪና ሰራተኞች አገናኝ ዐውደ ርዕይ ዛሬ በድሬደዋ ተካሂዷል። የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃር በወቅቱ እንዳሉት በድሬደዋ የወጣቶችን የስራ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በአገልግሎትና በሌሎችም ዘርፎች አማራጮችን በማስፋት ላይ ይገኛል። ተግባሩን ለማስቀጠልም ከአጋር አካላት ጋር በመቀናጀት በተለያዩ የሙያ መስኮች የሰለጠኑ 350 ወጣቶች በመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት የስራ እድል እንዲያገኙ መደረጋቸውን ገልጸው፤ ለዚህም የዛሬው መርሃ ግብር መዘጋጀቱን ጠቁመዋል። በተጨማሪም በሀገር ውስጥ የስራ ስምሪት ለሚሳተፉ ወጣቶችም በአሰሪና ሰራተኞች አገናኝ ድርጅቶች አማካኝነት 380 ለሚሆኑ ወጣቶች የስራ እድል መመቻቸቱን ገልጸዋል። የድሬደዋ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው ወጣቶች በዕውቀትና በክህሎት ተወዳዳሪ በመሆን የስራ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም ሴክተር መስሪያቤቶች እና ባለሃብቱ በቅንጅት እንዲሰሩ የተለያዩ መድረኮች መካሄዳቸውን ጠቁመው የአሁኑ ዐውደ ርዕይም የቅንጅታዊ ስራው ማሳያ ነው ብለዋል። ከሀገር ውስጥ የስራ ስምሪት ባለፈ ወደ ውጭ ሀገራት ለሚጓዙት ወጣቶች  የቋንቋ፣ የአካባቢዎቹ መረጃዎችና ሙያዊ ስነምግባር ላይ ተገቢውን ስልጠና በመውሰድ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ መሰራቱን አንስተዋል።

የ"ብቃት" የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ መሠረታዊ የሕይወት ክህሎት ሥልጠና ተጀመረ ‎የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከዓለም ባንክ ጋር በመተባበር የሚተገበረው የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም መሠረታዊ
+5
የ"ብቃት" የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ መሠረታዊ የሕይወት ክህሎት ሥልጠና ተጀመረ ‎የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከዓለም ባንክ ጋር በመተባበር  የሚተገበረው የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ  ፕሮግራም  መሠረታዊ የሕይወት ክህሎት ሥልጠና ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ፣  በአቃቂ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተጀምሯል። ‎ይህ ሥልጠና ወጣቶች በሥራ ቦታ የሚያጋጥሟቸውን ተግዳሮቶች በብቃት እንዲወጡ የሚያስችል ሲሆን፤ በተለይም የግንኙነት (Communication)፣ የቡድን ሥራ (Teamwork)፣ የችግር አፈታት እና የውሳኔ አሰጣጥ ክህሎቶችን ለማሳደግ ነው፡፡ ‎የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሁሉንም ዜጎች ያካተተ ምቹ የሥራ ዕድል ለመፍጠር ከሚሠራቸው ሥራዎች አንጻር፤ ሥልጠናው ሕጋዊ ፈቃድ ያላቸውንና በአዲስ አበባ የሚኖሩ የከተማ ስደተኞችን (Urban Refugees) ጭምር ያካተተ ነው። ‎የሥራ ላይ ልምምዱ እነዚህ ወጣቶች በተለያዩ ድርጅቶች ውስጥ በሚመርጧቸው የሥራ ዘርፎች ልምድ እንዲቀስሙና የሥራ ዕድል እንዲፈጠርላቸው የሚያስችል ነው፡፡

የሁለትዮሽ ትብብር ለላቀ የጋራ ተጠቃሚነት! በክህሎት ልማት እና በሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፉ ያለንን የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ በኢትዮጵያ የኦማን ሱልጣኔት ኤምባሲ ኃላፊ እና
+5
የሁለትዮሽ ትብብር ለላቀ የጋራ ተጠቃሚነት! በክህሎት ልማት እና በሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፉ ያለንን የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ በኢትዮጵያ የኦማን ሱልጣኔት ኤምባሲ ኃላፊ እና በአፍሪካ ኅብረት የኦማን ተወካይ ክቡር ዶ/ር አፍካር ናዚም አሊ አል-ፋርሲ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገናል፡፡ በውይይታችን የክህሎት ልማትና የሥራ ስምሪት ትስስርን ጨምሮ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ማሳደግ በሚቻልባቸው የትኩረት መስኮች ላይ በዝርዝር መክረናል። ይህ ትብብር በኢትዮጵያና ኦማን መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ከማሸጋገሩም ባለፈ፣ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቱን በማላቅ ለጋራ ተጠቃሚነት ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ነው፡፡ ክቡር ዶ/ር አፍካር ናዚም አሊ አል-ፋርሲ፤ የሁለቱን አገራት የክህሎትና የሥራ ዕድል ትስስር ለማጠናከር እንዲሁም የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ላሳዩት ቁርጠኝነት ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን ይድረስዎ፡፡ የሥራ ባለቤት እርስዎ ነዎት!

የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራውን ከዕቅድ በላይ ማሳካቱን ቢሮው አስታወቀ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የ10 ወራት ዕቅድ አፈፃፀሙን ከባለድርሻና አስፈፃሚ አካላት ጋር ገምግሟል። በዚህም ለ320,000
+3
የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራውን ከዕቅድ በላይ ማሳካቱን ቢሮው አስታወቀ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የ10 ወራት ዕቅድ አፈፃፀሙን ከባለድርሻና አስፈፃሚ አካላት ጋር ገምግሟል። በዚህም ለ320,000 በላይ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን አስታውቋል። ይህም ከዕቅዱ አኳያ 111 በመቶ እንደሆነ ነው የተገለፀው። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ  በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፣ ትልቁ ሪፎርም መዋቅር መቀየር ሳይሆን በአመራሩና በአስተግባሪው ዘንድ የሚፈጠር የአስተሳሰብ ለውጥ ነው ብለዋል። በሥራ ዕድል ፈጠራ ወቅት የሥራ ማማረጥ ችግር እንደ ዋነኛ ተግዳሮት የታየ መሆኑን አመላክተው ቢሮው ለወላጆችና ለሥራ ፈላጊዎች የአመለካከት ቀረጻ ንቅናቄ መደረጉ ትርግም ያለው ውጤት ማምጣቱን አመላክተዋል። ባለፉት 10 ወራት በቢሮው ለሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራው የ2.2 ቢሊዮን ብር የብድር አቅርቦትና የሥራ ቦታዎች ማመቻቸት መቻሉን ከቢሮው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ስልጠናው ለሴቶችና ለአካል ጉዳተኞች ምቹና ደህንነቱ የተጠበቀ የሥልጠና አካባቢ ለመፍጠር ያለመ ነው- የኢትዮጵያ ኢንትርፕረነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት የኢትዮጵያ ኢንትርፕረነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት የ
+4
ስልጠናው ለሴቶችና ለአካል ጉዳተኞች ምቹና ደህንነቱ የተጠበቀ የሥልጠና አካባቢ ለመፍጠር ያለመ ነው- የኢትዮጵያ ኢንትርፕረነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት የኢትዮጵያ ኢንትርፕረነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት የተቋማት ደህንነትና ጥበቃ ላይ ለቴክኒክና ሙያ አሰልጣኞች የአሰልጣኞች ስልጠና ሰጥቷል፡፡ ስልጠናው በቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት ውስጥ ምቹ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና ሁሉንም ዜጎች በፍትሃዊነት ለማሳተፍ ያለመ ነው፡፡ ከዚሁ ጋር ተያይዞ  በየተቋማቱ የደህንነትና የጥበቃ (Safeguarding) ሥራዎችን በባለቤትነት የሚመሩ ባለሙያዎችን ለማፍራት የሚያስችል ከመሆኑም ባሻገር ስልጠና የወሰዱ ባለሙያዎች የደህንነት መርሆዎችን በተቋማቱ የሥነ-ምግባር ደንብ ውስጥ እንዲያካትቱ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ነው ተብሏል፡፡ ይህም ለወጣቶች፣ በተለይም ለሴቶችና ለአካል ጉዳተኞች ምቹና ደህንነቱ የተጠበቀ የሥልጠና አካባቢ እንዲፈጠሩ የሚያስችል እንደሆነ ነው ኢንስቲትዩቱ የገለፀው፡፡ ስልጠናውን የኢትዮጵያ ኢንትርፕረነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት (EDI) ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን (SEED ፕሮግራም) እና "ላይት ፎር ዘ ወርልድ" (Light for the World) ጋር በመተባበር የተዘጋጀ መሆኑን ከኢንስቲትዩቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

በቦሌ አለምአቀፍ አየርመንገድ ዉስጥ የሰዉ ሃይል አቅም በማሳደግና በቴክኖሎጂ የታገዘ ዘመናዊ  አሰራር በመዘርጋት በቦታዉ የሚሰጡ የኢሚግሬሽን ስራዎችን ፍጥነትና ጥራት ማሻሻል ችለናል፡፡ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የኢሚግሬሽን ዘርፍ ሃላፊ አቶ ጎሳ ደምሴ

ታህሳስ 28፣ አዲስ አበባ.pdf2.67 MB

ታህሳስ 25፣ ድሬ ዳዋ.pdf6.89 KB