Tikvah Economy and Jobs
የቲክቫህ ኢትዮጵያ ይፋዊ የኢኮኖሚና የስራ መረጃ ቻናል። The official channel for economy, finance, and verified job opportunities. ማስታወቂያ ለማስወጣት ፦ @tikvaheconomy_BOT
Ko'proq ko'rsatish📈 Telegram kanali Tikvah Economy and Jobs analitikasi
Tikvah Economy and Jobs (@tikvaheconomy) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 19 717 obunachidan iborat bo'lib, Iqtisodiyot & Moliya toifasida 6 306-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 1 751-o'rinni egallagan.
📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika
невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 19 717 obunachiga ega bo‘ldi.
25 Avgust, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 2 490 ga, so‘nggi 24 soatda esa -13 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.
- Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
- Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 86.12% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 40.81% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
- Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 16 986 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 8 049 ta ko‘rish yig‘iladi.
- Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 70 ta reaksiya keladi.
📝 Tavsif va kontent siyosati
Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“የቲክቫህ ኢትዮጵያ ይፋዊ የኢኮኖሚና የስራ መረጃ ቻናል። The official channel for economy, finance, and verified job opportunities.
ማስታወቂያ ለማስወጣት ፦ @tikvaheconomy_BOT”
Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 26 Avgust, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Iqtisodiyot & Moliya toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.
Ma'lumot yuklanmoqda...
| Sana | Obunachilarni jalb qilish | Esdaliklar | Kanallar | |
| 26 Avgust | 0 | |||
| 25 Avgust | +2 | |||
| 24 Avgust | +5 | |||
| 23 Avgust | 0 | |||
| 22 Avgust | +4 | |||
| 21 Avgust | 0 | |||
| 20 Avgust | 0 | |||
| 19 Avgust | 0 | |||
| 18 Avgust | +2 | |||
| 17 Avgust | +4 | |||
| 16 Avgust | 0 | |||
| 15 Avgust | 0 | |||
| 14 Avgust | +7 | |||
| 13 Avgust | 0 | |||
| 12 Avgust | +3 | |||
| 11 Avgust | +8 | |||
| 10 Avgust | +7 | |||
| 09 Avgust | +2 | |||
| 08 Avgust | +7 | |||
| 07 Avgust | +15 | |||
| 06 Avgust | +21 | |||
| 05 Avgust | +37 | |||
| 04 Avgust | +68 | |||
| 03 Avgust | +212 | |||
| 02 Avgust | +284 | |||
| 01 Avgust | +1 959 |
| 2 | Heleph Coffee
ሔሌፍ ቡና
ከሌሎች የቡና አፍቃሪዎች ጋር ዘና እያሉ ቅዳሜ ከሰዓቶን የሚያሳልፉበት ልዩ ዝግጅት።
በባለሞያ የተዘጋጀ ስፔሻሊቲ የሔሌፍ ቡና በተለያዩ አማራጮች ይቀርባል ይቀመሳል ፣ አዝናኝ የጥያቄና መልስ (Trivia) ውድድሮች፣ አዳዲስ ሰዎችን የሚተዋወቁበት፣ አስደሳች ጨዋታዎች ከበርካታ ሽልማቶሽ ጋር ይኖራሉ።
📅 ቀን እና ሰዓት
ቀን፡ ቅዳሜ፣ ነሐሴ 16 ቀን
ሰዓት፡ ከቀኑ 8:00 እስከ ምሽቱ 12:00 ሰዓት
ቦታ ፦ አዲስ አበባ፣ ቦሌ
📩 እንዴት ማመልከት ይቻላል?
@helephcoffee_bot ስም እና ስልክ ቁጥር
ምዝገባውን ከአንድ ተጨማሪ ጓደኛ ጋር ማድረግ ይቻላል።
ያለው ቦታ ውስን ስለሆነ ቀድመው ለሚመዘገቡት ቅድሚ ያስጣል። መግቢያ በነጻ !
Tikvah X Heleph
@tikvaheconomy | 9 298 |
| 3 | ክፍት የሥራ ቦታ
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ፦
- ለኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጽሕፍት አገልግሎት፣
- ለኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም፣
- ለኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ባሉ ክፍት የስራ መደቦች አመልካቾችን አወዳድሮ ፣በቋሚነት መቅጠር ይፈልጋል፡፡
ማመልከቻ ፦
1. ለኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጽሕፍት አገልግሎት ሊንከ👇
https://forms.gle/dxgeogAqveHXyyTV7
2. ለኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም 👇
https://forms.gle/Wip8f9qaPduHLvsX9
3. ለኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት 👇
https://forms.gle/rp6LqKDz6HrAikh48
ከወጡት የስራ ዘርፎች መካከል ከ0 ዓመት እስከ 10 ዓመት የስራ ልምድ የተጠየቀባቸው ናቸው።
@tikvaheconomy | 19 975 |
| 4 | ወደ ፍርድ ቤት ያመራው ዋጋ ጭማሪ
በአዲስ አበባ የሚገኘው British International School (BIS) ወላጆች፣ ትምህርት ቤቱ ለ2026/27 የትምህርት ዘመን ድንገተኛ የክፍያ ጭማሪ ማድረጉን ተከትሎ ጭማሪውን በመቃወም ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ወስደውታል።
ካፒታል ጋዜጣ እንደዘገበው፣ ወላጆቹ ጭማሪው እስከ 36 በመቶ የደረሰ መሆኑንና በቂ ቅድመ ማሳወቂያና ከወላጆች ጋር ተገቢው ምክክር ሳይደረግ እንደተጣለ ገልጸዋል።
ጉዳዩ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት እየታየ ነው።
አንድ ወላጅ እንደገለጹት፣ የአንድ ልጅ ዓመታዊ ክፍያ ከ2025/26 የትምህርት ዘመን 26 ሺህ ብር ከነበረበት በ2026/27 ከ60 ሺህ ብር በላይ ደርሷል።
ሌላ ሦስት ልጆች ያሏቸው ወላጅ እንደገለጹት፣ ጭማሪው እንደ ክፍል ደረጃው ከ25 እስከ 36 በመቶ ይደርሳል፤ ይህም በየሩብ ዓመቱ በአንድ ልጅ ከ11 ሺህ እስከ 12 ሺህ ብር ተጨማሪ ክፍያ እንዲጠየቅ አድርጓል።
በፍርድ ቤት ትዕዛዝ መሠረት 15 አባላት ያሉት የወላጆች ኮሚቴ ከትምህርት ቤቱ ጋር ድርድር ቢያደርግም ስምምነት ሳይደረስ ቀርቷል።
ወላጆቹ ጭማሪው በሁለት ዓመታት ተከፍሎ እንዲተገበር ሁለት አማራጮች አቅርበዋል፤ አንደኛው ጭማሪውን በድምሩ 20 በመቶ በማድረግ 10 በመቶ በ2026/27 እና 10 በመቶ በ2027/28 እንዲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ የጥሬ ክፍያ ጭማሪው 15 በመቶ ሆኖ በሁለት ዓመታት እንዲተገበር ነበር። ት/ቤቱ ግን ሁለቱንም ሀሳቦች እንደተቃወመ ወላጆቹ ገልጸዋል።
የት/ቤቱ አስተዳደር በበኩሉ የክፍያ ለውጡ የሥራ ማስኬጃ ወጪዎች መጨመራቸውንና የትምህርት ጥራቱን ለመጠበቅ አስፈላጊ መሆኑን ለወላጆች እንደገለጸ ተመላክቷል።
የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣኑ ጉዳዩን በጽሁፍ መመለሱን እና ት/ቤቱና ወላጆቹ በመግባባት መፍትሔ እንዲያገኙ መምከሩን ለካፒታል ጋዜጣ ገልጿል።
ወላጆቹ እንደሚሉት፣ የክፍያ ጭማሪው በትምህርት፣ በመጓጓዣ፣ በምግብና በሌሎች የትምህርት ወጪዎች ላይ እንዲሁም ከኑሮ ውድነት ጋር በተያያዘ የወላጆች/ቤተሰብ ወጪ ጫናን በእጅጉ የሚያከብድ ነው።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የካፒታል ጋዜጣ ነው።
ነሐሴ 3 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvaheconomy | 16 818 |
| 5 | አማራ ባንክ በተለያዩ የሥራ መደቦች ላይ ብቁ የሆኑ ተወዳዳሪዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
1. Branch Manager Grade-I
2. Senior Credit Risk Analyst
3. Junior Property Administration Officer
በባንኩ ኦፊሴላዊ ድረገጽ https://vacancy.amharabank.com.et/?csrt=6914453002451074544 ላይ ማመልከት ይቻላል።
⏰ የማመልከቻ ጊዜው እስከ ነሐሴ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. ነው።
አማራ ባንክ በማንኛውም የቅጥር ሂደት ክፍያ እንደማይጠይቅ ገልጿል። ስለሆነም ከሐሰተኛ የሥራ ማስታወቂያዎች ይጠንቀቁ።
@tikvaheconomy | 15 017 |
| 6 | ክፍት የስራ ቦታ
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ከላይ በምስሉ በተዘረዘሩት ክፍት የስራ መደቦች አመልካቾችን አወዳድሮ ፣በቋሚነት መቅጠር ይፈልጋል፡።
አዲስ አበባ ቦሌ መንገድ ፊላሚንጎ አካባቢ በሚገኘው የኮሚሽኑ ህንጻ 4ኛ ወለል ብቃትና ሰው ሀብት አስተዳደር ሥራ አስፈፃሚ በአካል በመቅረብ መመዝገብ ይቻላል ተብሏል።
የስራ ዕድል ማስታወቂያዎችን ለማስወጣት/ ሌሎች መልዕክቶችን ለማስተላለፍ 👉 @tikvaheconomy_BOT ይጠቀሙ።
@tikvahecocnomy | 26 006 |
| 7 | #የሥራ_ቅጥር_ዕድል_ጥቆማ
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሞዴል ኮሚኒቲ ትምህርት ቤት (AAU-MCS) ለተለያዩ የሥራ መደቦች ፍላጎት ያላቸውና ብቁ የሆኑ ባለሙያዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡
ትምህርት ቤቱ ከ2019 የትምህርት ዘመን ጀምሮ ለአንደኛ ደረጃ (ከ1ኛ እስከ 7ኛ ክፍል) ተማሪዎች ከፍተኛ ጥራት ያለው ትምህርት ለመስጠት አቅዷል፡፡
ዝርዝር የሥራ መደቦችና የማመልከቻ ሁኔታ ለማግኘት 👇
https://www.aau.edu.et/announcements/detail?title=Vacancy~Announcement~AAU-MCS
➤ የሥራ መደብ፦ በተለያዩ ሙያዎች
➤ ተፈላጊ ባለሙያዎች ብዛት፦ 70
➤ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፦ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ዲግሪ (ለተወሰኑ የሥራ መደቦች ዲፕሎማ፣10ኛ እና 12ኛ ክፍል ተጠይቋል፡፡)
➤ የሥራ ቦታ፦ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 5 ኪሎ
➤ የቅጥር ሁኔታ፦ በሙሉ ጊዜ
የተገለፁ መስፈርቶችን የምታሟሉ በሙሉ የማመልከቻ ደብዳቤ፣ CV፣ ሙሉ የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውና የማይመለስ ኮፒ እንዲሁም አስፈላጊ ሰርተፊኬቶችን በመያዝ እስከ ሐምሌ 29/2018 ዓ.ም ድረስ በሥራ ቀናት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ የሰው ሃብት ቢሮ በመገኘት ማመልከት ትችላላችሁ ተብሏል፡፡
(ዝርዝር የሥራ መደቦቹ እና መስፈርቶችን ከተያያዘው ፒዲኤፍ ይመልከቱ፡፡)
@tikvaheconomy | 27 476 |
| 8 | " በኢትዮጵያ የገበያ መር የውጭ ምንዛሪ ሥርዓት ድህነትን አባብሷል " - የዓለም ባንክ የፖሊሲ ሰነድ
የዓለም ባንክ በተያዘው ወር ባወጣው የፖሊሲ ሰነድ፣ በኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሪ ግብይት ሥርዓቱን ሙሉ በሙሉ በገበያ እንዲመራ መደረጉ ድህነትን ከመቀነስ ይልቅ ማባባሱን ገልጿል።
ሰነዱን ያዘጋጁት ከ2019 እስከ 2023 የዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት የነበሩት ዴቪድ ማልፔዝ ሲሆኑ፣ ኢትዮጵያ፣ ግብፅና ናይጄሪያ የተገበሩት ሙሉ በሙሉ ገበያ መር የምንዛሪ ሥርዓት የዝቅተኛ ገቢ ዜጎችን ይበልጥ እንደጎዳና ሀብት ዝቅተኛ ገቢ ካላቸው ዜጎች ወደ ልዩ ተጠቃሚ ቡድኖች እንዲሸጋገር እንዳደረገ ያብራራል።
በሰነዱ መሠረት፣ የውጭ ምንዛሪውን በአንድ ጊዜ ለገበያ ከመልቀቅ ይልቅ ብሔራዊ ባንክ ቀስ በቀስ እንዲመራውና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች እንዳይጎዱ ማድረግ ይቻል ነበር።
እንዲሁም የዲጂታል ክፍያ አገልግሎት ክፍያዎች እንዲቀንሱና የገንዘብ ዝውውር ፈጣንና ርካሽ እንዲሆን ቢደረግ በድህነት ላይ የሚፈጠረው ጫና ሊቀንስ እንደሚችል ያስረዳል።
ሰነዱ በቁጥር የሚያሳየው ለውጥም ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሷል። በግብፅ አንድ ዶላር በ2022 15 ፓውንድ ከነበረ በ2026 ወደ 50 ፓውንድ ከፍ ብሏል፤ በናይጄሪያ በ2023 461 ናይራ የነበረው በ2026 ወደ 1,350 ናይራ ደርሷል፤ በኢትዮጵያም በ2024 56 ብር የነበረው አንድ ዶላር በ2026 ወደ 160 ብር ከፍ ብሏል።
ከዚህ ጋር ተያይዞ የዓለም ባንክ ቀደም ሲል ባወጣው መረጃ መሠረት፣ በኢትዮጵያ የድህነት መጠን ከ33 በመቶ ወደ 43 በመቶ በ2025 ከፍ ማለቱን፣ የብር የመግዛት አቅም መዳከሙን፣ የውጭ የፋይናንስ ድጋፍ መቀነሱን እና የአገር ውስጥ የገንዘብ ሥርጭት መቀነሱን ጠቅሷል።
ዴቪድ ማልፔዝ በ2019 በኢትዮጵያ ባደረጉት ጉብኝት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር በመነጋገር የውጭ ምንዛሪው በሙሉ ለገበያ እንዳይለቀቅ ማሳሰባቸውን ገልጸው፣ "ነገር ግን ስኬታማ አልነበርንም፤ ምንዛሪው ሙሉ በሙሉ በገበያ እንዲመራ ተደረገ" ብለዋል።
በእሳቸው ገለጻ፣ የምንዛሪ ዋጋ መዳከም ጥቅሙ ለጥቂት ልዩ ተጠቃሚዎች ሲሆን፣ ኪሳራው ግን በብር ደመወዝ በሚከፈላቸውና በድህነት ውስጥ በሚኖሩ ዜጎች ላይ ይወድቃል።
በሌላ በኩል አይኤምኤፍ ግን በየጊዜው በሚያወጣቸው ሪፖርቶች የኢትዮጵያ የገበያ መር የውጭ ምንዛሪ ሪፎርም የውጭ ምንዛሪ ክምችትን እያሳደገ፣ ኢንቨስትመንትን እየሳበና የኢኮኖሚ ተወዳዳሪነትን እያሻሻለ መሆኑን በመግለጽ ከዚህ ግምገማ የተለየ አቋም ይዟል። #ሪፖርተር
@tikvahecocnomy | 27 557 |
| 9 | ክፍት የስራ ቦታ
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ባለው ክፍት የሥራ ቦታ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡
መስፈርቱን የምታሟሉ በኦንላይን ማመልከት ትችላላችሁ ፦ https://forms.gle/tFmB72pZ7XAGTJy76
@tikvaheconomy | 23 687 |
| 10 | ክፍት የስራ ቦታ
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ባለው ክፍት የሥራ ቦታ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡
መስፈርቱን የምታሟሉ በኦንላይን አመልክቱ https://forms.gle/mXg8SxMxbVCBN41X8
@tikvaheconomy | 20 753 |
| 11 | ክፍት የስራ ቦታ
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት ባለው ክፍት የሥራ ቦታ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡
መስፈርቱን የምታሟሉ በኦንላይን አመልክቱ https://forms.gle/PLeWEeRvo3tCUmco6
@tikvaheconomy | 22 123 |
| 12 | ክፍት የስራ ቦታ
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ባለው ክፍት የሥራ ቦታ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡
መስፈርቱን የምታሟሉ በኦንላይን አመልክቱ https://forms.gle/S1KwFgXJAChP7DDi8
@tikvaheconomy | 15 895 |
| 13 | ክፍት የስራ ቦታ
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት ባለው ክፍት የሥራ ቦታ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡
መስፈርቱን የምታሟሉ በኦንላይን አመልክቱ፦
https://forms.gle/SYemTA9r79pUxuY58
@tikvaheconomy | 14 011 |
| 14 | በመርካቶ ሸማተራ 180 የባህል ልብስ ሱቆች መታሸጋቸው 15 ሺህ ያህል ሰዎችን ተጎጂ አድርጓል።
እንደ ' አዲስ ፎርቹን ' ዘገባ፣ በአዲስ አበባ መርካቶ የሚገኘው የሸማተራ የባህል ጨርቅና ልብስ ገበያ በግብር አሰባሰብ ስርዓት ላይ በተነሳ አለመግባባት ምክንያት 180 የንግድ ሱቆች ከታሸጉ ሦስት ሳምንታት አልፈዋል።
ይህም በቀጥታና በተዘዋዋሪ 15 ሺህ ያህል ሰዎች የገቢ ምንጫቸውን እንዲያጡ አድርጓል።
ነጋዴዎቹ እንደሚናገሩት፣ የፌዴራል መንግሥት የገቢ ግብር ሕጉን ካሻሻለ በኋላ ከቋሚ የግብር ክፍያ ወደ ደረሰኝና ቫት (VAT) ስርዓት እንዲገቡ ተጠይቀዋል።
ነገር ግን ጨርቅ ከሸማኔዎች ያለ ደረሰኝ የሚገዙ በመሆናቸው ሥርዓቱን በቀላሉ መተግበር እንደማይችሉ ይከራከራሉ።
ባለሥልጣናት በበኩላቸው፣ ነጋዴዎቹ ከሕግ የሚጠይቀውን የገቢ መጠን እያገኙ በመሆኑ ደረሰኝ መስጠትና በVAT መመዝገብ እንዳለባቸው ገልጸዋል። ለዚህም ከስድስት ወራት በላይ ጊዜ መስጠታቸውንና ከተደጋጋሚ ማሳሰቢያ በኋላ ሕጉን ለማስፈጸም ሱቆቹን እንደታሸጉ አስታውቀዋል።
የሸማተራ ነጋዴዎች ግን ውይይቱ ሳይጠናቀቅ ሱቆቻቸው መታሸጋቸው ፍትሃዊ እንዳልሆነ ይገልጻሉ።
በሱቆቹ መዘጋት ምክንያት የባህል ጨርቅ ሸማኔዎች፣ ልብስ ሰፊዎች፣ ጥልፍ ሠራተኞች ፣ አጓጓዦችና ሌሎች በዘርፉ የተሰማሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ገቢያቸውን አጥተዋል።
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በበኩሉ ነጋዴዎቹ ወደ ሕጋዊ ስርዓቱ እንደገቡ ሱቆቹ እንደሚከፈቱ ገልጿል።
የግብር ባለሙያዎችም የVAT ምዝገባው በሕግ የሚጠየቅ ቢሆንም፣ በሸማኔዎችና በነጋዴዎች መካከል ያለውን የደረሰኝ ችግር በውይይትና በተለዋዋጭ መፍትሄ መፍታት እንደሚገባ ያሳስባሉ።
ይህ ጉዳይ መንግሥት የግብር ገቢን ለማሳደግ እየወሰደ ካለው ጠንካራ እርምጃ ጋር ተያይዞ የተነሳ ሲሆን፣ የሸማተራ ነጋዴዎች ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ለመውሰድ መዘጋጀታቸው ተገልጿል።
አዲስ ፎርቹን የመረጃው ባለቤት ነው።
@tikvaheconomy | 11 226 |
| 15 | በመርካቶ ሸማተራ 180 የባህል ልብስ ሱቆች መታሸጋቸው 15 ሺህ ያህል ሰዎችን ተጎጂ አድርጓል።
በአዲስ አበባ መርካቶ የሚገኘው የሸማተራ የባህል ጨርቅና ልብስ ገበያ በግብር አሰባሰብ ስርዓት ላይ በተነሳ አለመግባባት ምክንያት 180 የንግድ ሱቆች ከታሸጉ ሦስት ሳምንታት አልፈዋል። ይህም በቀጥታና በተዘዋዋሪ 15 ሺህ ያህል ሰዎች የኑሮ ምንጫቸውን እንዲያጡ አድርጓል።
ነጋዴዎቹ እንደሚናገሩት፣ የፌዴራል መንግሥት የገቢ ግብር ሕጉን ካሻሻለ በኋላ ከቋሚ የግብር ክፍያ ወደ ደረሰኝና ቫት (VAT) ስርዓት እንዲገቡ ተጠይቀዋል። ነገር ግን ጨርቅ ከሸማኔዎች ያለ ደረሰኝ የሚገዙ በመሆናቸው ሥርዓቱን በቀላሉ መተግበር እንደማይችሉ ይከራከራሉ።
ባለሥልጣናት በበኩላቸው፣ ነጋዴዎቹ ከሕግ የሚጠይቀውን የገቢ መጠን እያገኙ በመሆኑ ደረሰኝ መስጠትና በVAT መመዝገብ እንዳለባቸው ገልጸዋል። ለዚህም ከስድስት ወራት በላይ ጊዜ መስጠታቸውንና ከተደጋጋሚ ማሳሰቢያ በኋላ ሕጉን ለማስፈጸም ሱቆቹን እንደታሸጉ አስታውቀዋል።
የሸማተራ ነጋዴዎች ግን ውይይቱ ሳይጠናቀቅ ሱቆቻቸው መታሸጋቸው ፍትሃዊ እንዳልሆነ ይገልጻሉ። በሱቆቹ መዘጋት ምክንያት የባህል ጨርቅ ሸማኔዎች፣ ልብስ ሰፊዎች፣ ጥልፍ ሠራተኞች፣ ብረት ሠራተኞች፣ አጓጓዦችና ሌሎች በዘርፉ የተሰማሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ገቢያቸውን አጥተዋል።
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በበኩሉ ነጋዴዎቹ ወደ ሕጋዊ ስርዓቱ እንደገቡ ሱቆቹ እንደሚከፈቱ ገልጿል። የግብር ባለሙያዎችም የVAT ምዝገባው በሕግ የሚጠየቅ ቢሆንም፣ በሸማኔዎችና በነጋዴዎች መካከል ያለውን የደረሰኝ ችግር በውይይትና በተለዋዋጭ መፍትሄ መፍታት እንደሚገባ ያሳስባሉ።
ይህ ጉዳይ መንግሥት የግብር ገቢን ለማሳደግ እየወሰደ ካለው ጠንካራ እርምጃ ጋር ተያይዞ የተነሳ ሲሆን፣ የሸማተራ ነጋዴዎች ውሳኔውን በፍርድ ቤት ለመቃወም መዘጋጀታቸው ተገልጿል። | 1 |
| 16 | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ (GBE) የቀድሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተስፋዬ ቦሩን፣ በተደጋጋሚ የተፈጸሙ የቁጥጥር ደንብ ጥሰቶችን በመጥቀስ፣ በማንኛውም በኢትዮጵያ በሚሠራ የፋይናንስ ተቋም ውስጥ የቦርድ አባል፣ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወይም ከፍተኛ አመራር ኃላፊነት እንዳይይዙ ለ5 ዓመታት አግዷል።
ብሔራዊ ባንኩ ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በላከው ደብዳቤ፣ በግሎባል ባንክ ላይ ባደረገው ልዩ የቁጥጥር ምርመራ መሠረት አቶ ተስፋዬ ከሥራ መነሳታቸውን ገልጿል።
ምርመራው የባንኩን የኮርፖሬት አስተዳደር፣ የብድርና የክሬዲት አስተዳደር፣ የሰው ኃይል አመራር፣ የውጭ ምንዛሬ አሠራር እና አጠቃላይ የፋይናንስ አስተዳደርን መገምገሙን አመልክቷል።
እንደ ብሔራዊ ባንኩ ገለጻ፣ በምርመራው ወቅት በርካታ የቁጥጥር መመሪያዎችና የባንኩ የውስጥ አሠራር ደንቦች መጣሳቸው በመረጋገጡ የባንኩን ጤናማ አሠራር እንደጎዳ ተገልጿል። ግኝቶቹም ከባንኩ ቦርድና ከከፍተኛ አመራሮች ጋር ተወያይተው በተለዩት ችግሮች ላይ መግባባት መደረሱን ብሔራዊ ባንኩ ገልጿል።
ባንኩ በበኩሉ የማስተካከያ ዕቅድ ቢያቀርብም፣ የተገኙት ጥሰቶች ክብደት እና አቶ ተስፋዬ ከዚህ ቀደም በግንቦት 2013 እና በኅዳር 2017 ዓ.ም የተሰጧቸው የጽሑፍ ማስጠንቀቂያዎች በመኖራቸው፣ የበለጠ ጠንካራ እርምጃ መውሰድ አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን አስታውቋል።
በዚህም መሠረት፣ ከሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ከግሎባል ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚነት መነሳታቸውን እና ከዚያው ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 5 ዓመታት በማንኛውም የፋይናንስ ተቋም ውስጥ የቦርድ አባል፣ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወይም ከፍተኛ አመራር ኃላፊነት እንዳይይዙ ውሳኔ መተላለፉን ገልጿል።
ይህ የብሔራዊ ባንክ እርምጃ የግሎባል ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ አቶ ተስፋዬን ከሥራ ካሰናበተ በኋላ የተወሰደ መሆኑ ተገልጿል።
በጉዳዩ ላይ የአቶ ተስፋዬ ቦሩ፣ የግሎባል ባንክ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ዮሴፍ ጌታቸው እና የብሔራዊ ባንክ የባንክ ቁጥጥር ኃላፊ ፍሬዘር አያሌው አስተያየት ለማግኘት የተደረገው ጥረት ውጤታማ እንዳልሆነ ተገልጿል። #Capital
@tikvaheconomy | 12 364 |
| 17 | የሥራ እድል !
ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ ለሚገኙ የሥራ መደቦች ብቁ አመልካቾችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
የሥራ መደቦች ፦
- የሽያጭ ፕሮሞተር (Sales Promoter)
- ሲቪል ሥራ መሐንዲስ (Civil Work Engineer)
እንዴት ማመልከት ይቻላል ?
ወደ ኢትዮ ቴሌኮም ኦፊሴላዊ ድረ-ገጽ ይግቡ https://www.ethiotelecom.et
ከላይ በቀኝ ያለችውን ሶስት ሰረዝ ምልክት ይጫኑ።
በመቀጠል Company የሚለውን ይምረጡ።
በመቀጠል Vacancy የሚለውን በመክፈት የሥራ ዝርዝሩን ይመልከቱና ያመልክቱ።
@tikvahecocnomy | 15 563 |
| 18 | በርካታ የቁርጥ ግብር ከፋዮች ለ2018 ዓ.ም የተወሰነባቸው ግብር ከአቅማቸው በላይ መሆኑን ገልጸው ቅሬታ አቀረቡ።
ከፋዮቹ እንደሚሉት፣ ግብሩ ከአምናው ጋር ሲነጻጸር በእጅጉ ጨምሯል፤ ከ15 ሺህ ብር ወደ 180 ሺህ ብር፣ ከ10 ሺህ ብር ወደ 46 ሺህ ብር እና ከ12 ሺህ ብር ወደ 110 ሺህ ብር የደረሰባቸውም እንዳሉ ገልጸዋል።
ቅሬታ አቅራቢዎቹ የግብር ግምገማው በተጨባጭ የንግድ አቅምና የገቢ ሁኔታ ላይ ተመስርቶ ሳይሆን በዘፈቀደ የተወሰነ መሆኑን ተናግረዋል።
@tikvaheconomy | 14 756 |
| 19 | #ግብር : ከ2020 በጀት ዓመት ጀምሮ መንግሥት አዲስ የተሽከርካሪ ባለቤትነት ግብር ለመተግበር እየተዘጋጀ ሲሆን፣ ከግብሩ የሚሰበሰበው ገቢ በፌዴራል መንግሥትና በክልሎች መካከል የሚከፋፈልበትን የሕግ ማዕቀፍ ለማዘጋጀት እየሠራ መሆኑን ካፒታል ዘግቧል።
" ግብሩ የመንግሥትን የውስጥ ገቢ ለማሳደግ እና የግብር አሰባሰብን ለማጠናከር እንደሚያግዝ " ተገልጿል።
እቅዱ በፌዴራል እና በክልል መንግሥታት መካከል የገቢ መከፋፈል ሥርዓትን የሚያስቀምጥ ሲሆን በመጀመሪያ ዓመት 0.1% እና በሁለተኛው ዓመት 0.2% የአገሪቱን GDP የሚያህል ገቢ እንደሚያስገኝ ይጠበቃል።
ሆኖም ኢኮኖሚስቶች ግብሩ በመጓጓዣ ወጪ፣ በኑሮ ውድነት እና በዝቅተኛ ገቢ ተሽከርካሪ ባለቤቶች ላይ የሚያሳድረው ተፅዕኖ በጥንቃቄ ሊታይ እንደሚገባ ማስጠንቀቃቸውን ጋዜጣው አመልክቷል።
@tikvaheconomy | 22 677 |
| 20 | " ግብር "
የፕራግማ ካፒታል የተሰኘ ድርጅት፣ በደሞዝተኞች ላይ የሚጣለው የግብር መጠን ከኑሮ ውድነት ጋር ተዳምሮ ከባድ ጫና እየፈጠረ በመሆኑ መንግሥት ሊያሻሽለው እንደሚገባ ገልጿል።
ድርጅቱ እንዳለው፣ ኢትዮጵያ ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት መካከል በደሞዝተኞች ላይ ከፍተኛ ግብር ከምትጥሉ ሀገራት አንዷ ናት።
@tikvahecocnomy | 23 587 |
