cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

ተንቢሀት ለአማኝ ሴቶች

ማወቅ ያለብንን መሠረታዊ የሆኑ ዲናዊ ትምህርቶችን የምንማርበት ቻናል ነዉ። ስተት ካያቹብን አርሙን 🌺🌺🌺🌺 For any comments ➾ @Tenbihatleamnhsetoch_bot

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
1 223
Obunachilar
-224 soatlar
+527 kunlar
+15130 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

In shaa Allah 🥀 ከደስታ ብዛት የተነሳ እየጮህክ ጌታዬ ሆይ! ለብቻዬ እንደማትተወኝ አውቅ ነበር የምትልበት ቀን ይመጣል።
Hammasini ko'rsatish...
🥰 5 2
ما من أيام أفضل عند الله ولا العمل فيهن أحب إلى الله من هذه الأيام العشر، فأكثروا فيهن من التهليل والتكبير وذكر الله، وإن صيام يوم منها يعدل بصيام سنة، والعمل فيهن يضاعف سبعمائة ضعف “በደረጃቸውም ሆነ በውስጣቸው በሚሠራ ሥራ ከነኚህ አሥር ቀናት የሚበልጥ በአላህ ዘንድ አንድም የለም። በነሱ ውስጥ ላኢላሀ ኢለላህ፣ አላሁ አክበር ማለትንና አላህን ማውሣት አብዙ። ከነሱ ውስጥ አንድ ቀን መፆም የአመት ፆምን ይስተካከላል። በነሱ ውስጥ የሚሠራ ሥራ እስከ ሰባት መቶ ድረስ እጥፍ ድርብ ይሆናል።” (በይሀቂና ኢማም አህመድ ዘግበውታል) 4. በነሱ ውስጥ ተክቢራ ማብዛት ዐብዱላህ ኢብኑ ዑመር እና አቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) በአሥርቱ ቀናት ውስጥ “አላሁ አክበር!” እያሉ ወደ ገበያ ይወጣሉ። ሰዎችም የነሱን ተክቢራ እየተቀበሉ “አላሁ አክበር!” ይሉ ነበር። እንዲህም ብለዋል። “ዑመር በሚና በሚገኘው ቁባቸው ውስጥ ተክቢራ ያደርጉ የነበረ ሲሆን በመስጅድ ውስጥ ያሉ ሰዎችም እርሣቸውን ይሰሙና ‘አላሁ አክበር!’ ይሉ ነበር። ገበያ ውስጥ ያሉ ሰዎችም ሚና በተክቢራ እስክትናወጥ ድረስ ‘አሏሁ አክበር!’ ይሉ ነበር።” ብለዋል። (ፈትሁል ገፋር ቀጽ 5፣ ገጽ 379) 5. ሀጅ ሥራ ውስጥ ላልተሠማራ ሰው የመጀመሪያዎቹን ዘጠኝ ቀናት መፆም ይህንንም ሀሠን፣ ኢብኑ ሲሪን እና ቀታዳህን የመሣሰሉ ታቢዒዮችን ጨምሮ በርካታ ሰሃቦች ሰርተውታል። ኢማም ነወዊ እንዲህ ብለዋል፡- ليس في صوم هذه التسعة كراهة بل هي مستحبة استحبابًا شديدًا، لا سيما التاسع منها، وهو يوم عرفة “አነኚህ ዘጠኝ ቀናት መፆማቸው የሚጠላ አይደለም። ባይሆን እጅግ ተወዳጅ ነገር ነው። በተለይም ዘጠነኛው ቀን። እሱም የዐረፋ ቀን ነው።” (ሸርሁል ሙስሊም ቀጽ 3፣ ገጽ 245) ከአቢ ቀታዳህ እንደተዘገበው ደግሞ የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ስለ ዐረፋ ቀን ፆም ተጠየቁ። እንዲህም አሉ፡- يكفِّر السنة الماضية والباقية “ያለፈውንና የሚመጣውን አመት ወንጀል ያብሳል።” (ኢማም ሙስሊም እና አህመድ ዘግበውታል) 6. ቁርዓንን ማንበብ ከኢብኑ መስዑድ (ረ.ዐ) እንደተዘገበው የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- من قرأ حرفًا من كتاب الله فله به حسنة، والحسنة بعشر أمثالها، لا أقول الم حرف، ولكن ألف حرف، ولام حرف، وميم حرف “ከአላህ ኪታብ አንድ ፊደል ያነበበ ሰው የመልካም ምንዳ አለው። አንዱ መልካም ምንዳ አሥር ተመሣሣይ እጥፍ ይባዛል። አንድ ሰው ‘አሊፍ-ላም-ሚም’ ያለ እንደሆነ አንድ ፊደል አይደለም። ነገርግን ‘አሊፍ’ አንድ ፊደል ነው፣ ‘ላምም’ አንድ ፊደል ነው፣ ‘ሚምም’ አንድ ፊደል ነው።” (ቡኻሪና ቱርሙዚ ዘግበውታል) 7. ኡድሂያ ማዘጋጀት አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ አለ فَصَلِّ لِرَبِّكَ وَانْحَرْ [١٠٨:٢] “ስለዚህ ለጌታህ ስገድ፤ (በስሙ) ሰዋም።” (አል-ከውሰር 108፤ 3) ከዓኢሻ (ረ.ዐ) እንደተዘገበው የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ፡- ما عمل آدمي من عمل يوم النحر أحب إلى الله من إهراق الدم، وإنها لتأتي يوم القيامة بقرونها وأشعارها وأظلافها، وإن الدم ليقع من الله بمكان قبل أن يقع على الأرض فطيبوا بها نفسًا “ከነህር /እርድ/ ቀን ሥራዎች ውስጥ የአደም ልጅ ደምን ከማፍሠስ በላይ ወደ አላህ ተወዳጅ የሆነ አንድም ሥራ አልሠራም። እርዷም የቂያማ ቀን ከነፀጉሯና ጥፍሯ ትመጣለች። ደሙም መሬት ላይ ከማረፉ በፊት ከአላህ ዘንድ ቦታ ይይዛል። በዚህም ነፍሣችሁን አስደስቱ (ደስ ይባላችሁ)።” (ቱርሙዚ፣ ሃኪም እና ኢብኑ ማጀህ ዘግበውታል) ኡድሂያ ማረድ የተዘጋጀ ሰው ኡድሂያውን እስኪያርድ ድረስ ፀጉሩንም ሆነ ጥፍሩን የሰውነቱን መንካት የለበትም። ከኡሙ ሰለማ (ረ.ዓ) በተላለፈው ሀዲስም ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ)፡- إِذَا دَخَلَتِ الْعَشْرُ وَأَرَادَ أَحَدُكُمْ أَنْ يُضَحِّيَ فَلا يَمَسَّ مِنْ شَعَرِهِ وَبَشَرِهِ شَيْئًا “አንዳችሁ ኡድሂያ ለማረድ አስቦ አሥርቱ ቀናት የገቡ እንደሆነ ከፀጉሩም ሆነ ከሰውነቱ አንዳቸም ነገር አይንካ።” ብለዋል። (ሙስሊም እና ነሣኢ ዘግበውታል።) አላህ እነዚህን ውድ ቀናቶች ከሚጠቀሙት ያድርገን።» منقول
Hammasini ko'rsatish...
«አሥሩ የዚልሂጃ ቀናት- ከዱኒያ ቀናቶች ሁሉ በላጮች ከዱኒያ ቀናቶች ሁሉ እጅግ በላጮች የሆኑት የመጀመሪያዎቹ አሥሩ የዚልሂጃ ወር ቀናት ናቸው። እነሆ እነኚህ ምርጥ ቀናት ከፊት ለፊታችን ተደቅነዋል። ለዚህም ይመስላል ሙስሊሙ የአላህን ቤት ከዕባን ለመጎብኘት ያለው ጉጉቱ ድንበር አልፏል፤ በከዕባ ዙሪያ ጠዋፍ ለማድረግ፣ በሶፋና መርዋ መካከል ለመሮጥ እና ዐረፋ ላይ ቆሞ አላህን ለመለመን ያለው ስሜት ጣሪያ ነክቷል። የታላቁን ነቢይ መስጅድ መስጅደ-ነበዊን ለመጎብኘትና በመስጅዱ ውስጥ በተከበረው ቦታ ረውደቱ ሸሪፋ ላይ ለመስገድ ያለው መነሣሣት ውስጥን ይነቀንቃል፤ በሀሣብ ያምሣል፣ ክንፍ ቢኖር “ምነዋ ወደዚያ ወደተቀደሰው ምድር በበረርኩ!” ያስብላል። ወዳጆቼ! እኛስ እነኚህ እጅግ የተባረኩና የተከበሩ ቀናቶች ከያዙት ምንዳ ለመቋደስ ምን ማድረግ እንችል ይሆን? አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ ዘወትር በትእዛዙ በመገኘት ለቋሚው ሀገራቸው ለሚሰንቁ መልካም ባሮቹ በነኚህ በተባረኩ ቀናት ውስጥ ምን ዓይነት ትልቅ ምንዳ ይሆን ያዘጋጀላቸው? የዚልሂጃ ወር የመጀመሪያዎቹ አሥር ቀናት ታላቅነት 1. አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ የማለባቸው ቀናት መሆናቸው አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ አለ وَالْفَجْرِ ﴿١﴾ وَلَيَالٍ عَشْرٍ ﴿٢﴾ وَالشَّفْعِ وَالْوَتْرِ ﴿٣﴾ “በጎህ እምላለሁ። በዐሥር ሌሊቶችም። በጥንዱም በነጠላውም።” (አል-ፈጅር 89፤ 1-3) ከጃቢር ኢብኑ ዐብዱላህ (ረ.ዐ) እንደተዘገበው የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እነኚህ አሥር ቀናቶች የትኞቹ እንደሆኑ በሚያመላክተው ሀዲሣቸው ውስጥ እንዲህ ብለዋል፡- العشر عشر الأضحى، والوتر يوم عرفة، والشفع يوم النحر “አሥሩ ማለት አሥሩ የአድሃ ቀናት ናቸው። ‘ወትር’ /ጥንዱ/ የተባለው የዐረፋ ቀን ሲሆን ‘ሸፍዕ’ /ነጠላው/ ማለት ደግሞ የነህር /የእርዱ/ ቀናት ናቸው።” ብለዋል። ሀዲሱን ኢማም ነሣኢ እና ሃኪም በሙስሊም መስፈርት መሠረት ሰሂህ ትክከለኛ ሀዲስ ነው ብለውታል። ኢማም በይሀቂ ከዐብዱላህ ኢብኑ ዙበይር እንደዘገቡት ደግሞ:- ليالٍ عشر، العشر الثماني، وعرفة، والنحر “አሥርቱ ሌሊቶች የመጀመሪያዎቹ ስምንቶቹ፣ የዐረፋ ቀን እና የእርድ ቀን ናቸው።” ብለዋል። 2. እነኚህ ቀናት “አያም መዕሉማት” /የታወቁ ቀናት/ም ይባላሉ ይህም በሚከተለው የቁርዓን አንቀፅ ውስጥ የተጠቀሠ ነው። وَيَذْكُرُوا اسْمَ اللَّهِ فِي أَيَّامٍ مَّعْلُومَاتٍ [٢٢:٢٨] “በታወቁ ቀኖችም ውስጥ የአላህን ስም ያወሱ ዘንድ” (አል-ሀጅ 22፤ 27) “የቁርዓን ተርጓሚ” በመባል የሚታወቁት ታላቁ ሰሃባ ዐብዱላህ ኢብኑ ዐባስ እነኚህ ቀናት “አሥርቱ ቀናት” ናቸው ያሉ ሲሆን በነኚህ ቀናት ውስጥ ታላቁን ጌታ አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላን በብዛት ማውሳት የተወደደ ነው። 3. ከዱኒያ ቀናቶች ሁሉ በላጮቹ ይህም በሚከተለው ሀዲስ ውስጥ ተነግሯል። ከጃቢር (ረ.ዐ) እንደተዘገበው የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- أفضل أيام الدنيا أيام العشر، يعني: عشر ذي الحجة، قيل: ولا مثلهن في سبيل الله؟، قال ولا مثلهن في سبيل الله إلا رجل عفر وجهه في التراب، وذُكر عرفة، فقال يوم مباهاة ينزل الله تبارك وتعالى إلى سماء الدنيا، فيقول: عبادي شعثًا غبرًا ضاحين، جاءوا من كل فجٍّ عميق يسألون رحمتي، ويستعيذون من عذابي ولم يروا، فلم نر يومًا أكثر عتيقًا وعتيقة من النار “ከዱኒያ ቀናቶች ሁሉ በላጮቹ አስሩ ቀናት ናቸው። ማለትም አሥሩ የዚልሂጃ ቀናት። በአላህ መንገድ ላይ መውጣትም ቢሆን የነሱ አምሣያ የለምን? ተብለው ተጠየቁ። እርሳቸውም ‘በአላህ መንገድ ላይም ቢሆንም እነሱን የሚመስል የለም። ፊቱ ከአፈር የተገናኘ ሰው (በአላህ መንገድ ላይ የሞተ) ሲቀር።’ አሉ። ስለ ዐረፋም ተወሳና መልእክተኛው (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ ‘እሱ የሙባሃት /አላህ በባሮቹ የሚኩራራበት/ ቀን ነው። አላህ ወደ ቅርቢቱ ዓለም ይወርድና ባሮቼ ተንጨፋረው፣ አቧራ የለበሱ ሆነውና ተጎሣቁለው እሩቅ ከሆነ አቅጣጫ ሁሉ እዝነቴን ሊጠይቁ እሷን ያላዩ ሲሆን ከእሣቴም በኔ ሊጠበቁ መጡ። ወንድም ሆነ ሴት በብዛት ከእሣት ነፃ የሚወጡበት እንዲዚህ ቀን አላየንም’።” (በዛር ሀዲሱን ዘግበውታል) 4. በርካታ የሀጅ ሥራዎች የሚሠሩት በነኚህ ቀናት ውስጥ ነው ከነኚህም መካከል የዚልሂጃ ስምንተኛ ቀን በሙዝደሊፋ ይታደራል፤ በዘጠነኛው ቀን በዐረፋ ላይ ይቆማል፤ ከዚህም በተጨማሪ ለመስዋእት የሚሆን እንሠሳት መንዳት፣ ጠጠር መወርወር፣ ፀጉር መላጨት አሊያም ማሣጠር፣ በዚልሂጃ አሥረኛው ቀን ጠዋፍ ማድረግንና የመሳሰሉትን ያጠቃልላል። 5. የአምልኮ ዘርፍ የሆኑት ዋና ዋናዎቹ የሚሰበሰቡባቸው ቀናቶች ናቸው ኢማም ሃፍዝ ኢብኑ ሀጀር ፈትሁልባሪ በተሠኘው ታዋቂ ኪታባቸው ውስጥ እንዲህ ይላሉ والذي يظهر أن السبب في امتياز عشر ذي الحجة لمكان اجتماع أمهات العبادة فيه، وهي الصلاة والصيام والصدقة والحج، ولا يتأتى ذلك في غيره “የዚልሂጃ አሥርቱ ቀናትን ለየት ከሚያደርጉ ነገሮች መካከል ቦታው ከአምልኮ ተግባራት ዋና ዋና የሚባሉት በአንድ ላይ ተሰባስበው የሚሠሩበት መሆኑ ነው። ይሀውም ሰላትን፣ ፆምን፣ ሰደቃን (ምጽዋትን) እና ሀጅን ያጠቃልላል። ከነኚህ ቀናት ውጭ እነኚህ ሁሉ ነገሮች አንድ ላይ የሚሰባሰቡበትን አጋጣሚ አናገኝም።” (ፈትሁልባሪ ቅጽ 2፣ ገጽ 462) በነኚህ ቀናት ውስጥ ከሚወደዱ ሥራዎች መካከል 1. ሐጅና ዑምራ ማድረግ በነኚህ ቀናት ውስጥ የሚሠሩ ምርጥ የአምልኮ ሥራዎች ናቸው። ምክኒያቱም የነኚህ አምልኮ ሥራዎች ትክክለኛ ወቅቱ ይህ ነውና። ከአቢሁረይራ (ረ.ዐ) እንደተዘገበው የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ)እንዲህ አሉ:- العمرة إلى العمرة كفارة لما بينهما، والحج المبرور ليس له جزاء إلا الجنة “አንደኛው ዑምራ እስከ ሌላኛው ዑምራ በመካከላቸው የተሰራ ወንጀልን ያብሣል፤ መብሩር /የተሟላ/ የሆነ ሀጅ ምንዳው ጀነት ብቻ እንጂ ሌላ አይደለም።” (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል) 2. በበጎ ሥራዎች ላይ መበርታት ከዐብዱላህ ኢበብኑ ዐባስ (ረ.ዐ) እንደተዘገበው የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ፡- ما مِن عمل أفضل من عمل فى هذه الأيام العشر، قالوا: ولا الجهاد؟ قال ولا الجهاد إلا رجل خرج بماله ونفسه فلم يرجع منه بشيء “በነኚህ አሥር ቀናት ውስጥ የሚሠራ ሥራን የሚበልጥ ምንም የለም። ‘ጅሃድም ቢሆን?’ አሏቸው። እርሣቸውም ‘አዎን ጅሃድም ቢሆን ገንዘቡንና ነፍሱን ይዞ ወጥቶ ያልተመለሰ ሰው ብቻ ሲቀር።’ አሉ።” (ኢማም አህመድና ቱርሙዚ ዘግበውታል) እንዲሁ በሌላ ዘገባም:- لا تطفئوا سرجكم ليالي العشر “በአሥርቱ ቀናት ለሊቶች ውስጥ መብራታችሁን አታጥፉ።” የሚል ዘገባ የመጣ ሲሆን ይህም ትርጉሙ “በነኚህ ቀናት ውስጥ ቁርዓን ቅሩ፣ በሰላትም በርትታችሁ ቁሙ ለማለት ነው” ተብሏል። 3. ዚክር ማብዛት ከኢብኑ ዑመር (ረ.ዐ) እንደተዘገበው የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ:-
Hammasini ko'rsatish...
✅ ከጁመዓ ቀን ሱናዎች ➠➻➠➻➠➻➠➻➠➧ ↩️‏ #سنن_يوم_الجمعة ➊ الغسل ➋ الطيب ➌ السواك ➍ لبس الجميل ➎ قراءة سورة الكهف ➏ التبكير لصلاة الجمعة ➐ الإكثار من الدعاء والصلاة على النبي ﷺ 🔹ገላን መታጠብ 🔹ሽቶ መቀባት 🔹ሲዋክ መጠቀም 🔹ጥሩ ልብስ መልበስ 🔹ሱረቱ ከህፍን መቅራት 🔹በጧት ለጁመዓ ሶላት መጣድ 🔹በነብዩ ﷺ ላይ ዱዓና ሰለዋት  ማብዛት اللَّهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ، وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ كَمَا صَلَّيْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ، اللَّهُمَّ بَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ، وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا بَارَكْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ، وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيد        الَّلهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبَيِّنَا مُحَمَّد ٍﷺ  اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبَيِّنَا مُحَمَّدٍ ﷺ اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبَيِّنَا مُحَمَّدٍ ﷺ 🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺
Hammasini ko'rsatish...
018.mp319.63 MB
ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላቸው አስርቱ የዙል-ሒጃ ቀናት ✍ ዝግጅት፦ አቡ ጁነይድ ሳላሕ አሕመድ ህዳር 2004 E.C.
Hammasini ko'rsatish...
10ቱ የዙልሒጃ ቀናት.pdf3.33 KB
የዙል ሂጃ አስቱ ቀናት በላጭነት አሏህ ይዘንላቸው ኢብኑ ኡሠይሚን እንዲህ ይላሉ፦"ሰዎች በነዚህ በአስርቱ ቀናት ላይ ዝንጉ ናቸው ፣እውቀትን ፈላጊዎች ደግሞ ለህዝቡ በላጭነቷን ማብራራት አለባቸው ፤ህዝቡ ደግሞ ኸይርን ይወዳል ፤ነገር ግን እውቀትን ፈላጊዋች በርግጥም ከማመላከት ተዘናግተዋል ።" [መጅሙአል ፈተዋ እና ረሳኢሉ ሸይኽ ኢብኑ ኡሠይሚን አሏህ ይዘንላቸው የተወሠደ]
Hammasini ko'rsatish...
👍 5
00:48
Video unavailableShow in Telegram
የወርሽ አቀራር ነው። በሀገረ ሞሪታንያ። #ቁርኣን ውበቱን በቃል መግለፅ የሚዳግት ድንቅ መፅሐፍ!
Hammasini ko'rsatish...
1.13 MB
3
"የአደም ልጆች ሆይ! ሰይጣንን አትገዙ፤ እርሱ ለእናንተ ግልጽ ጠላት ነውና በማለት ወደእናንተ አላዘዝኩምን?"   Surah Yasin; 60
Hammasini ko'rsatish...
"ፍጹም ምእምናን እነዚያ አላህ በተወሳ ጊዜ ልቦቻቸው የሚፈሩት፣ በነሱም ላይ አንቀጾቹ በተነበቡ ጊዜ እምነትን የሚጨምሩላቸው፣ በጌታቸውም ላይ ብቻ የሚመኩት ናቸው፡፡" Surah Al-Anfal; 2 
Hammasini ko'rsatish...