አል–ዒምራን (CMC) የቁርኣንና ኢስላማዊ ት/ት ተቋም
➡️ ይህ የአል–ዒምራን(cmc) የቁርአንና ኢስላማዊ ትምህርት ተቋም official ቻናል ሲሆን፣በዚህ ቻናል ➲ ስለ ተቋሙና በስሩ ስላሉ ቅርንጫፎች የተለያዩ መረጃዎች ይለቀቃሉ ➲ እለታዊና ወቅታዊ ምክሮች ➲ ሳምንታዊና ወርሓዊ የዳዕዋ ፕሮግራሞች የሚለቀቁበት ይሆናል። ቻናሉ ተደራሽነት እንዲኖረው ለሌሎች በማጋራት የበኩሎን ይወጡ። https://t.me/alimranislamic
Ko'proq ko'rsatish5 618
Obunachilar
+724 soatlar
+787 kunlar
+29030 kunlar
- Kanalning o'sishi
- Post qamrovi
- ER - jalb qilish nisbati
Ma'lumot yuklanmoqda...
Obunachilar o'sish tezligi
Ma'lumot yuklanmoqda...
Hammasini ko'rsatish...
❤ 25🥰 4
የዒድ ሶላት በአል ዒምራን የቁርአን እና ኢስላማዊ ትምህርት ተቋም
❤ 53👍 5🥰 4
Photo unavailableShow in Telegram
ከዐረፋህ ቀን ትሩፋት
👇👇👇
عن عائشة -رضي الله عنها- أن رسول الله صلى الله عليه وسلم قال: "ما من يوم أكثر أن يعتق الله فيه عبدا من النار من يوم عرفة، رواه مسلم
ከእናታችን ዓዒሻህ (ረዲየሏሁ ዐንሀ ) በተላለፈ ሐዲስ ነብዩ ( ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል ፡
" አላህ ባርያን ከእሳት ነፃ ከሚያደርግባቸው ቀናቶች መሀከል የዐረፋን ያህል የበዛ ነፃነትን የሚለግስበት ቀን የለም "
ሙስሊም ዘግበውታል
❤ 22👍 4
Photo unavailableShow in Telegram
የዐረፋህ ቀን ትሩፋቶች
****
➡️ የዐረፋ ቀን በዒድ አል–አድሐ ዋዜማ ማለትም በዙል ሒጃህ ዘጠነኛ ቀን ላይ የሚውል ቀን ነው ።
▶️ የዐረፋ ቀን ከዓመቱ ቀናቶች ሁሉ በላጭ እንደሆነ በኢብኑ ሒባን በኹዘይማህ እና በበዛር የሐዲስ ጥራዝ ውስጥ በሰፈረው የጃቢር (ረዲየሏሁ ዐንሁ) ሐዲስ ነብዩ (ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ማለታቸው ተወስቷል ...
" ما من يوم أفضل عند الله من يوم عرفه "
" ከዐረፋ ቀን በተሻለ በአሏህ ዘንድ በላጭ የሆነ ቀን የለም "
➡️ የዐረፋህ ቀን ሑጃጆች ወሳኝ የሚባለውን የሐጅ መሠረት ለመፈፀም በዐረፋህ ሜዳ ላይ የሚቆሙበት ቀን ሲሆን በሐጅ ኑሱክ ላይ ያልሆነ ሰው ቀኑን በመጾም እና የተለያዩ ዒባዳዎችን በማብዛት ማሳለፍ ይወደድለታል
▶️ ሰዪዱና አቡ ቀታዳህ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) ባስተላለፉት’ና ሙስሊም ውስጥ በተዘገበ ሐዲስ ነብዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) በዐረፋ ቀን ስለመፆም ተጠይቀው ...
"يكفر السنة الماضيه والسنة القابلة "
" ያለፈውን እና የመጭውን ዓመት ወንጀል ያስምራል "
በማለት መልሰዋል ።
👍 21❤ 11
ስለ ኡድሂያ ማብራርያ ( በመዝሀብ ሻፊዒይ)
ሰይዳችን ﷺ ስለ እርድ እንዲህ ብለውናል :-
« የአደም ልጅ የአረፋ ቀን ከማረድ የበለጠ አላህ የሚወደውን ስራ አልሰራም ፤ የታረደችዋም የቂያማ ቀን ከቀንዶቿ ከጥፍሮቿም ጭምር ትቀርባለች፤ ደሙ መሬት ላይ ከመድረሱ በፊት አላህ ጋር አጅሩ ይደርሳል፤ ተደስታቹ ስሯት »
📗 ኢብኑ ማጀ'ህ (3124)
፡==================
• ኡድሂያ የተባለበት ምክንያት ወቅት ዱሀ (ረፋዱ) ሰዓት ላይ የሚታረድ በመሆኑ ነው ይላሉ ዑለማዎች።
• ኡድሂያ ማረድ በዒዱ ቀናቶች ከሚያስፈልገው ነገር ተጨማሪ ማረድ የሚያስችል ሀብት ላለው ሰው የጠበቀ ሱና ነው።
ኢማሙ ቲርሚዚ'ይ በዘገቡት ሀዲስ ሰይዳችን ﷺ :- « እንዳርድ ታዝዣለው ፤ ለእናንተ ደሞ ሱና ነው » ብለዋል
ነዝር ካደረገው ግን ( ስለት ከገባ) ዋጂብ ይሆናል።
• ለኡድሂያ የሚቀርቡት
1- ግመል (5 አመት የሞላው)
2- በሬ/ላም/ፍየል (2 አመት የሞላው)
3- በግ (1 አመት የሞላው)
• የሚታረደው ከብት ስጋውን ከሚቀንስ ወይም ከሚያነውር ጉድለት መጥራት አለበት ( በጣም የከሳ ፤ ያበደ ፤ እውር ውይም አንድ አይኑ የጠፋ፤ በሽታ ያለበት ፤ ጆሮው ወይ ምላሱ የተቆረጠ ወይ ሙሉ ጥርሱ የሌለና የመሳሰሉት ነውሮች የሌለበት መሆን አለበት )
• አንድ ቤተሰብ ውስጥ አንዱ ካረደ ይበቃል። ሁሉም ከቻሉና አጅር ለማግኘት ሁሉም ቢያርዱ የተወደደ ነው።
• ግመል ወይም ከብት ለሰባት ሰዎች መሻረክ ይቻላል።
• የሚታረድበት ሰዓት የሚጀምረው የዒዱ ጠዋት ፀሀይ ከወጣችና አጠር ያሉ የሁለት ረክዐ ሰላትና ኹጥባ ጊዜ ካለፈ ቡሀላ ነው። ከዛች ሰዓት ጀምሮ እስከ ሶስተኛው አያም ተሽሪቅ (13 ዙል ሂጃ) መግሪብ ድረስ ይቻላል።
• ቡኻሪና ሙስሊም ከሰይዳችን ﷺ በዘገቡት ሀዲስ :- « በዚህ ቀናችን (የአረፋ ቀን) መጀመርያ የምንጀምርበት ስራ ሰላት እንሰግዳለን ፤ ከዛ ተመልሰን እናርዳለን። ይሄን ያደረገ መንገዳችንን በእርግጥ አግኝቷል ፤ ከዛ በፊት ግን ያረደ ለቤተሰቡ እንደማንኛው ግዜ እንደሚያቀርብላቸው ስጋ ነው ከኢባዳ ( ኡድሂያ) አይቆጠርም..»
• ሱና ከሆነው ኡድሂያ ትንሽም ቢሆን ሰደቃ መስጠት ግዴታ ነው። ትንሽም ቢሆን ሰደቃውን ካወጣ ሙሉ አጅሩን ያገኛል።
- የበለጠው ደሞ አንድ ሶስተኛውን በልቶ ሌላውን ሰደቃ ማውጣት ነው።
- ከዚህም የበለጠ ደሞ ከኡድሂያው ጉበት ትንሽ በልቶ ስጋውን በሙሉ ሰደቃ ማውጣት ነው።
- የኡድሂያን ስጋም ሆነ ቆዳ ሰደቃ መስጠት እንጂ ምንም ነገር መሸጥ ክልክል ነው። ለገፋፊውም ቢሆን ክፍያ ተደርጎ አይሰጥም።
• ኡድሂያ ለማድረግ ነዝር ያደረገ ( ስለት የገባ ) ኡድሂያው ዋጂብ ይሆናል። ዋጂብ ኡድሂያን ደሞ ስጋውን በሙሉ ሰደቃ ማውጣት ግዴታ ይሆንበታል።
• የኡድሂያን ሙሉ አጅር ለማግኘት ከማረዱ በፊት ወይም ሲያርድ ኒያ ማድረግ ይኖርበታል ።
- እራሱ የማያርድ ከሆነ ኡድሂያው ሲታረድ መመልከት ይወደድለታል።
አላህ ይወፍቀን ፣ አላህ ይቀበለን
፡==================
❤ 23👍 17
▶️ የዙል ሒጃህ መልዕክት
****
❤️ በአሏህ ስጦታዎች እንጠቀም! !
➡️ የተለያዩ በጎ ስራዎች በተለየ መልኩ እጥፍ ድርብ ምንዳ የሚያገኙበት ፣ ወንጀሎች የሚሰረዩበት’ና ብዙ ስጦታዎችን ያጨቁ የተለያዩ ቀናት ፣ ሳምንታት እና ወራት መኖራቸው ከጌታችን አሏህ እዝነት እና ስጦታ መገለጫዎች መሀከል ይመደባሉ ።
እኚህ ቅዱስ ወቅቶች በተለያዩ ጊዜያት እየተፈራረቁ መምጣታቸው ባሮች በጥቂት ስራ እጥፍ ድርብ ምንዳ የሚያገኙበትን እድል ከመፍጠርም ባሻገር በመልካም ተግባሮች ላይ ያላቸውን ተነሳሽነት ከፍ ማድረግ ይችላሉ ።
➡️ ከሳምንቱ ቀናቶች ውስጥ በላጭ የሆችው የጁሙዐ ቀን ስትመጣ ሶሏቷ የሳምንት ወንጀልን ማስማሯ ፣ የባርያው ልመና ተቀባይነትን የማይነፈግበት ድብቅ ሰዓት መያዟ’ና ሌሎችንም መልካም ነገሮች መያዟ ባርያው ከሌሎች ቀናት በተሻለ ለዒባዳ እንዲነሳሳ ያደርገዋል ። ነገረ ግን ቀኑን ከበጎ ተግባራት ተዘናግቶ የዋለ ባሪያ የአሏህን የሳምንት ስጦታ ሳይቀበል’ና ሳይጠቀምበት እንዳሳለፈ ይቆጠራል ።
➡️ ከወራቶች ሁሉ በላጭ የሆነው የረመዳን ወር ሲመጣም ሙስሊሙ ከሌላው ጊዜ በተሻለ ለዒባዳ እንዲነሳሳ የሚያደርጉ አያሌ መልካም ነገሮችን እንደመያዙ’ና ከለሊቶቹ አንዱ የ 83 ዓመት ዒባዳን ማስገኘት የሚችል እንደመሆኑ የአሏህ ባሮች ከሌላው ወራት በተሻለ በበጎ ተግባራት ላይ ይበራታሉ ። ነገር ግን ይህን መልካም እድል ችላ ብሎ የተገኘ ባሪያ የአሏህን ውድ ስጣታ ሳይቀበል’ና ሳይጠቀምበት እንዳሳለፈ ይቆጠራል ።
➡️ ከዐመቱ ቀናቶች ሁሉ በላጭ የሆኑት አስሩ የዙል ሒጃህ ቀናት ሲመጡም መልካም ስራዎች ሁሉ (ከጁሐድም በበለጠ) ከሌሎች ጊዜያት በተሻለ አላህ ዘንድ ይበልጥ ተወዳጅ የሚሆኑበት እንደመሆኑ የአሏህ ባሮች በጾም ፣ በዚክር ፣ በቁርአን ንባብ እና በመሳሰሉት በጎ ተግባሮች በመበራታት በዐመታዊው ልዩ የአሏህ ስጦታ ተጠቃሚ ለመሆን ይሽቀዳደማሉ ፣ እኚህን ውድ ቀናቶች ችላ ያለ ግን የአሏህን ስጦታ መጠቀም ባለመቻል ትልቅ ኪሳራ ውስጥ ይወድቃል ።
በአሏህ ስጣታዎች ተጠቃሚ እንሁን ! !
❤ 16👍 6