uz
Feedback
Ajeba Emmanuel united church

Ajeba Emmanuel united church

Kanalga Telegram’da o‘tish

እውነት እላችኋለሁ፤ ቃሌን የሚሰማ፣ በላከኝም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ ከሞት ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም።” — ዮሐንስ 5፥24 (አዲሱ መ.ት)

Ko'proq ko'rsatish
259
Obunachilar
-224 soatlar
-27 kunlar
-430 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Taglar buluti
Ma'lumot yo'q
Muammo bormi? Iltimos, sahifani yangilang yoki bizning qo'llab-quvvatlash boshqaruvchimizga murojaat qiling>.
Kirish va chiqish esdaliklari
---
---
---
---
---
---
Obunachilarni jalb qilish
Dekabr '24
Dekabr '24
+3
0 kanalda
Noyabr '24
+4
0 kanalda
Get PRO
Oktabr '24
+12
0 kanalda
Get PRO
Sentabr '24
+8
0 kanalda
Get PRO
Avgust '24
+20
0 kanalda
Get PRO
Iyul '24
+191
0 kanalda
Get PRO
Iyun '240
0 kanalda
Get PRO
May '240
0 kanalda
Get PRO
Aprel '240
0 kanalda
Get PRO
Mart '24
+70
0 kanalda
Sana
Obunachilarni jalb qilish
Esdaliklar
Kanallar
21 Dekabr0
20 Dekabr+1
19 Dekabr0
18 Dekabr0
17 Dekabr0
16 Dekabr0
15 Dekabr0
14 Dekabr+1
13 Dekabr0
12 Dekabr0
11 Dekabr0
10 Dekabr0
09 Dekabr0
08 Dekabr+1
07 Dekabr0
06 Dekabr0
05 Dekabr0
04 Dekabr0
03 Dekabr0
02 Dekabr0
01 Dekabr0
Kanal postlari
2
+8
Matn yo'q...
116
3
🎯 የመጥራት ዋጋ እግዚአብሔር የመጥራት አምላክ ነው ። እግዚአብሔር ያለ ዋጋ አልጠራንም ። ዋጋውንም ተምኖ ጠርቶናል ። እግዚአብሔር የሰውን ልጅ መጥራት የጀመረው በኤደን ገነት መሆኑ ደግሞ የእግዚአብሔርን የሰውን ልጅ ለክብር ና ለትልቅ ዋጋ ላለው ነገር መጥራቱን ያስረዳናል ። ይህም ድንቅ ነው ። 📌እግዚአብሔር አንድን አዲስ ትውልድ ለመቅረጽና ያሳበውን ይፈጽምበት ዘንድ አብርሃምን ጠርቶታል ። በእርሱም አዲስ ፣የራሱ የሆነ ፣ ቅዱስ ሕዝብ ፣ የተመረጠ ትውልድን ፈጥሯል ። 📌እግዚአብሔርም ከተፈጠረው አዲሱ ትውልድ(እስራኤል )በጀመረው ጉዞ ውስጥ በግልም (ለተለየ ዓላማ)፣በሕዝብም ደረጃ ደጋግሞ ተጣርቷል ። 📌የጥላውም ዘመን አልፎ በአዲሱ ኪዳንም ምስረታ ግለሰቦችን እየጠራ ወደ አካሉ በመጨመር ሂደት ላይ ነው ። ⭐️ ለምን ዓላማ እግዚአብሔር ጠርቶናል ?ይጠራናል? 1) ለድኅነት (ለድነት) ጠርቶናል ለእግዚአብሔር ዓላማ የተጠራ ሰው አስቀድሞ መዳን አለበትና እንድንድን ጠራን ። ከኃጢአት ፣ ከሞት ፣ ከጨለማ ሕይወት ፣ከዲያብሎስ እስረኝነት ፣ከፍርድ ድነን ለፈቃዱ እንውል ዘንድ ጠርቶናል ። የሚያስደንቀው እግዚአብሔር በልጁ ለመዳን ብቻ አልጠራንም ፣ ከዳንን ቀጥሎ ለክብር በልጁ ጠርቶናል ። 2)ለደቀመዝሙርነት ጠርቶናል ደቀመዛሙር ማለት ተከታይ ፣መሳይ ፣ ረድዕ ፣ተማሪ ማለት ነው ። ጌታ ኢየሱስ በፍጹም ልብ የተከተሉትን በሙሉ ያደረጋቸው ደቀመዛሙርት ነው ።ደቀመዛሙር ተከታይነት ብቻ ሳይሆን ጠንቅቆ ከተማረ መምህሩንም የሚመስል ነውና ። የተከቱሉትን በሙሉ በመንፈስ ቅዱስ ማህተምነት እርሱን እንዲመስሉ ሆነዋል ። የእርሱ ኮፒ(copy) ሆነውታል ። ይህም አስቀድሞ የተወሰነ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው። ጳውሎስ ለሮሜ ሰዎች የእግዚአብሔር የዘላለም ፕሮግራም ሲነግራቸው ፥ ወንድሞች ሁሉ የበኩሩን (የልጁን)መልክ እዲመስሉ ወስኗል ፥ ይላቸዋል። የልጁ መልክ በደቀመዛሙርት ሁሉ እንዲሳል የአብብ ፈቃድ ና ግብ ነው። ጌታ ኢየሱስ ክርሰቶስ በመጨመረሻው ቃሉ ለተከተሉት የእርሱ ደቀመዛሙርት ያላቸው ምንድነው ስንል ? አሕዛብን እያጠመቃችኹ ፣እያስተማራችኹ ደቀመዛሙርት አድርጉ ነው ያለው ። 3)ለቅድስና ጠርቶናል የጠራን እግዚአብሔር ቅዱስ (የተለየ)ነው ። ቅልቅል የሌለው ነው። ልዩ ነው ። እርሱ እንዲህ ነውና የጠራንም እኛ የተለየን (የተቀደስን )እንድንሆን ጠራን ። ቅድስና (መለየት)የእግዚአብሔር የምናይበት ዓይን ነውና ። እግዚብሔርን የምናስደስትበት ሕይወት ነውና። ርኩሱን ሳንነካ ፣ሳንቀላቀል በልዩነት እርሱን እያሳየን እንድንኖር ተጠርናል ። 4)ለምስክርነት ጠርቶናል ምስክር ማለት ያየውን ፣የሰማውን ፣ልምዱ ያደረገውን የሚናገር ማለት ነው። ጌታችን ካዳነን ፣ ከእርሱ ጋር ካዋለን ካሳደረን ፣ሕይወቱን ካሳየን በኋላ በጎነቱን የመናገር ኃላፊነት አለብን ። ጌታ የጠራቸውን በመጨረሻ ያላቸው ፥ ያያችሁትን የምነትመሰክሩ "ምስክሮቼ" ናችሁ ብሏቸዋል ። በሌላም ክፍል ሐዋርየረው "በጎነቱን የምትነግሩ የተመረጠ ትውልድ ናችሁ" ብሏል። 5)ለሽልማት ጠርቶናል እግዚአብሔር በዚህ ሁሉ ያለ ዋጋ አልጠራንም። በመጨረሻው ሽልማት አለ ። የተጠራንበት ዋጋ የልጅነት ክብር ነው ።ይኸ ክብር በእኛ ሲገለጥ ድል ከነሳው የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ፣ በዙንፋንም የተቀመጠው ድል የምነሳውን ለእኛ ከእርሱ ጋር እንቀመጥ ዘንድ ይሰጠናል ። ራዕ 3፥21 በዚህም (የድል አክሊል ፣ የደስታ አክሊል፣ የጽድቅ አክሊል፣ የሕይወት አክሊል እና የክብር አክሊል።) ያቀዳጀናል ። ተወዳጆች ሆይ እግዚአብሔር ለዚህ ሁሉ ክብር ከጠራን ይህ ደግሞ ከእኛ የሆነ የኛ የጽድቅ ሥራችን ውጤት ሳይሆን የእግዚአብሔር መልካምነት ና ፍቅር በመሆኑ ዘወትር ለዚህ ላበቃን ጌታ ክብርም ፣ ምስጋናም በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይሁንለት እንላለን ። አሜን ። ተባረኩ ። መ/ር አብርሃም ይገዙ ነሐሴ 26/2016 ዓመተ ምሕረት
144
4
#ክብር_ለእግዚአብሔር_ብቻ! ➘የምናደርገውንም ሁሉ ለእግዚአብሔር ክብር ብቻ ማድረግ አለብን! ➘ መኖርም ቢሆን ለእግዚአብሔር ክብር ብቻ መኖር አለብን! ♦ ምስጋና ለእግዚአብሔር ብቻ! ♦ ስግደት ለእግዚአብሔር ብቻ! ♦ አክብሮት ለእግዚአብሔር ብቻ! ➘ ክብሩን ሌላ ነገር ማንም ቢሆን ከእኛ መቀበል የለበትም። የምናደርገውንም ነገር ሁሉ ለእግዚአብሔር ክብር ማድረግ አለብን! ለማንም ክብር ብለን ምንም ማድረግ የለብንም የምናወራው ነገር የምናደርገው ነገር እግዚአብሔር ያከብራል ወይ ብለን መሳብ አለብን... እግዚአብሔርን የማያከብር ከሆነ የትኛውንም ነገር ከማድረግ ፣ከመናገር መመለስ አለብን። ➘ እንግዲህ የምትበሉ ወይም የምትጠጡ ብትሆኑ ወይም ማናቸውን ነገር ብታደርጉ ሁሉን ለእግዚአብሔር ክብር አድርጉት። — 1ኛ ቆሮንቶስ 10፥31 እግዚአብሔር ለማንም የማይሰጠው ነገር ክብሩን ነው! ➘ ስለ እኔ፥ ስለ ራሴ አደርገዋለሁ ስሜ ተነቅፎአልና፤ ክብሬንም ለሌላ አልሰጥም። ኢሳይያስ 48፥11 ኤፌሶን 1 ⁶ በውድ ልጁም እንዲያው የሰጠን የጸጋው ክብር ይመሰገን ዘንድ ይህን አደረገ። ➘ ሰማያት የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፥ የሰማይም ጠፈር የእጁን ሥራ ያወራል። — መዝሙር 19፥1 #ክብር አብ ለከበረው ለኢየሱስ ብቻ! #ዮሐንስ 17 ⁴ እኔ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር አከበርሁህ፤ ⁵ አሁንም፥ አባት ሆይ፥ ዓለም ሳይፈጠር በአንተ ዘንድ በነበረኝ ክብር አንተ በራስህ ዘንድ አክብረኝ። #በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ።እንግዲህ የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች የራሳችሁ ፡ለራሳችሁም አይደላችሁምና በሥጋችሁ እግዚአብሔር አክብሩ፡ እናክብር! ➘ከእግዚአብሔር ውጭ ክብር ምስጋና ስግደት ለማንም ለምንም አይሁን! ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ! ➘ ወይስ ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን? በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ። — 1ኛ ቆሮንቶስ 6፥19-20 ♦ የሚናወራውን ለእግዚአብሔር ክብር እናውራ ♦ የሚናደርገውን ለእግዚአብሔር ክብር እናድርግ ♦ የምናስበውን ለእግዚአብሔር ክብር ይሰጣል ወይ እያለን እናስብ! ♦ የምናገለግለው ክብር ፈለገን ሳይሆን ለእግዚአብሔር ክብር ብቻ ይሆን! #ለታረደው_በግ_ለኢየሱስ_ክብር_ይሁን! ዶ/ር መንግስቱ ለማ
111
5
Matn yo'q...
85
6
እሁድ ድንቅ የቃል እና የአምልኮ ጊዜ👇 በቃል ፦ዶ/ር መንግስቱ ለማ በመዝሙር፦ የቤተክርስቲያኒቱ አምልኮ ህብረት ጋር ድንቅ ጊዜ ጌታ ሰጥቶናል። እንዲሁም ልጆችን ለእግዚአብሔር የመስጠት ጊዜ ነበረን! #ክብር_ለእግዚአብሔር_ብቻ!👇
88
7
https://www.facebook.com/100072210318428/posts/535912122159127/?mibextid=rS40aB7S9Ucbxw6v
83
8
ኢየሱስ ይበልጣል.... 🙋
90
9
አቤት ክርስቲና ውበቱ . . . . ጉዞ ወደ ክብር ነው🙋
94
10
Matn yo'q...
111
11
ያ መሲህ ዝቅ ብሎ መጣ አነሰ ስለኛ ክፋት እንዳረገ ወንበዴ ፍርደኛ የሰው ልጅ እርቃኑን በመስቀል ላይ ታየ በዚያ በጎለጎታ በቀራንዮ ቆየ ያ መሲህ ዝቅ አለ ያ ንጉስ ዝቅ አለ ከአብርሀም በፊት የነበረው እርሱ ሰው ሆነ የአለም ፈጣሪ ሰው ሆነ ተዋረደ ሆነ የተጠላ ተገረፈ መከራውን በላ እግዚአብሔር ወልድ ሰው ሆነ የአለም ፈጣሪ ሰው ሆነ እንዲያ ሲያናንቁት አንዳች አልመለሰም ሲዘባበቱበት ሲሰድቡት ታገሰ እጁ ባበጃቸው እጅ ላይ ወደቀ የህማም ሰው ሆነ በደዌ ደቀቀ ያ መሲህ ዝቅ አለ ያ ንጉስ ዝቅ አለ ከአብርሀም በፊት የነበረው እርሱ ሰው ሆነ የአለም ፈጣሪ ሰው ሆነ ተዋረደ ሆነ የተጠላ ተገረፈ መከራውን በላ እግዚአብሔር ወልድ ሰው ሆነ የአለም ፈጣሪ ሰው ሆነ ተንኮል የሌለበት ፃድቅ ሆኖ ሳለ ደዌአችንን ወስዶ ስለኛ ቆሰለ የሁላችን በደል በእርሱ ላይ ሆነ ነፍሱን አሳልፎ ለሞት አቀረበ የድል ንጉስ(4) እንደሞተ አልቀረም ተነስቷል ኢየሱስ መቃብሩ ባዶ ነው የኛ ጌታ ህያው ነው። መቃብሩ ባዶ ነው በዚያ የለም ህያው ነው ህያው ነው የምናመልከው ህያው ነው መስኪዬ ተባርከሻል Meskerem Getu YouTube 👇 https://youtube.com/@meskeremgetu586?si=_8gu_MVpNHRRvQwb 04 Ya Mesih | ያ መሲህ | Meskerem Getu New Album.
113
12
https://www.facebook.com/100022892917114/posts/1745878146185266/?mibextid=xu5OvmQjzDyq7Bl8
75
13
#የራሳችን_አይደለንም🙋 👇 #በዋጋ_ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ #በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ። 1ኛ ቆሮንቶስ 6፥19-20 ብሩህ ቀን ይሁንላችሁ❤ T.E
64
14
+2
04_Ya_Mesih_ያ_መሲህ_Meskerem_Getu_HPqgfaMUkOk_140.mp3
72
15
መስከረም ጌቱ ተገዳ ከእሁድ በፊት አልበሟን ዛሬ ለቃለች። የተገደደችበት ምክንያት መዝሙሮቿ ባልታወቁ ሰዎች ተሰርቃ በሌላ በማይታወቅ YouTube ስለተለቀቁ ነው። 🙆👇
66
16
SELAM-DESTA-ሳበኝ-SABEGN-New-Ethiopian-Gospel-Song-2024.m4a
72
17
SELAM DESTA💓 #ሳበኝ! ከደረቅ መሬት እደስር ብቀል ከቆላ አበባ ፅድቅን እዳገኝ የታረድክልኝ በእዛ በኮረብታ አይኔን አልነቅልም ከተከልኩበት ከመስቀልህ ላይ መስቀሌን ይዤ እከተልሀለው ሳበኝ እላለው 🥹 ረቢ ሆይ ከወዴት ትኖራለህ ውዴ ሆይ ወዴት ታሰማራለህ ሁሉም ጥዬ እድከተልህ ሳበኝ ልሩጥ ከኻላህ ሁሉም ንቄ እድከተልህ ሳበኝ ልሩጥ ከኻላህ😥ለጥቂት ግጦሽ እዳልቀላዉጥ መሰማሪያ ለምለም መስኬ ነህ ከያዕቆብ ጉድጓድ ትበልጣለህ የዘላለም ዉሃ ምንጭ ነህ ለአንዴና ለሁሌም የምትሆን ፋሲካዬ ነህ አንተ ያለህበት የነፍሴ በዓል ነው ሳበኝ እላለሁ 👐
72
18
Matn yo'q...
74
19
ደስ የሚል ዜና😍ያ መሢህ የተሰኘው የዘማሪት መስከረም ጌቱ ቁጥር 3 አልበም የፊታችን እሁድ በሁሉም streaming platform ይለቀቃል🤗።
69
20
#ሰው_በእምነት_ብቻ_ሳይሆን_በሥራ_እንዲጸድቅ_ታያላችሁ (ያዕቆብ 2፡24 ) ያዕቆብ 2፡24 እንደተፃፈው “ሰው በእምነት ብቻ ሳይሆን በሥራ እንዲጸድቅ ታያላችሁ" ይላል። ይህ የመፅሐፍ ቅዱስ ክፍል በክርስቲያናዊ ሥነ-መለኮት ውስጥ በእምነት እና በሥራ መካከል ስላለው ግንኙነት በሚደረጉ ውይይቶች ውስጥ ቀዳሚ የመከራከርያ ነጥብ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። በርግጥ ለእኛ ለወንጌላውያን አማኞችና ወንጌል ገብቶናል ለምንል ያን ያህል አስፈላጊ ሀሳብ ባይመስልም በዚህ ጉዳይ እሰጣ'ገባ ላይ ላሉት የሚጠቅምና ለእኛም ያዕቆብ ሊለን የፈለግነውን ተረድተን ምላሻችንን እንድንሰጥ ይጠቅማል ብዬ አስባለሁ። 👉 የክፍሉ ታሪካዊ ዳራ ምን ይመስላል? 1. ፀሀፊውና እና ተደራስያኑ፡- የያዕቆብ መልእክትን የፃፈው የኢየሱስ ወንድም የሆነው ሐዋርያው ያዕቆብ ሲሆን ተደራስያኑ ደግሞ ዲያስፖራ የአይሁድ ክርስቲያኖችን እንደሆኑ ይታመናል። ደብዳቤው ብዙውን ጊዜ በጥንት ክርስቲያኖች መካከል ለነበሩት የእምነት እና የስነ-ምግባር ጉዳዮች ምላሽ ሰጪ ሆኖ ያገልላል። 2. የጥንቱ ክርስትና አውድ ምን ይመስል ነበር? በቀደመችው ቤተ ክርስቲያን ፣ የሕጉ ሚና (ኦሪት) እና ከአሕዛብ የተለወጡ አማኞች የአይሁድ ልማዶችን ይከተሉ ዘንድ እንደሚያስፈልጋቸው ዘለግ ያሉ ክርክሮች ነበሩ። ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን ሐዋርያው ጳውሎስ በእምነት መጽደቅን አፅንዖት በመስጠት በሮሜ 3፡ 27 ላይ "ትምክህት እንግዲህ ወዴት ነው? እርሱ ቀርቶአል። በየትኛው ሕግ ነው? በሥራ ሕግ ነውን? አይደለም፥ በእምነት ሕግ ነው እንጂ።" በማለት ከያዕቆብ በተቃራኒው በመቆም ፅፎልናል። ይህም ሀሳብ ስለ ስራና እምነት የሁለትዮሽ ክርክሮችን ለመፍጠር ችሏል ። በእነዚህ የሁለትዮሽ ሀሳቦች ላይ የተለያዩ ክርስቲያናዊ እይታዎች:- 1. ፕሮቴስታንት ብዙ የፕሮቴስታንት ቤተ እምነቶች (በተለይ በማርቲን ሉተር ተጽእኖ ስር ያሉ) ያዕቆብ 2፡24 እምነትን በአግባቡ መጠቀምን ለማመላከት ብቻ የተነገረ ክፍል እንደሆነ ይተረጉማሉ። ይህም እውነተኛ እምነት በራሱ የመልካም ሥራዎችን ምንጭ ነው ብለው ያምናሉ። በነገራችን ላይ ሉተር ያዕቆብ ካነሳው "ድነት በእምነት ብቻ ሳይሆን በስራም ጭምር ነው ማለቱን መነሻ በማድረግ "epistle of straw" 😑 ብሎታል። ይህ ማለት በጠቅላላው የያዕቆብ መፅሐፍ አያስፈልግም የሚል እንዳልሆነ ልብ ይሏል። 2. ካቶሊክ የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነትም ሆነ ሥራ ለደኅንነት አስፈላጊ መሆናቸውን ታስተምራለች። The Council of Trent (1545-1563) በግልጽ እንዳስቀመጠው መጽደቅ የእግዚአብሔርን ጸጋ እና የሰው የስራ ትብብር ውጤት ነው ብሏል። 3. ኦርቶዶክስ ምስራቃዊ ኦርቶዶክስ ሥነ-መለኮት (Eastern Orthodox theology) በመለኮታዊ ጸጋ እና በሰው ጥረት መካከል ያለውን ውህደት አፅንኦት ይሰጣል። 1. አውዳዊ ንባቡ (Contextual Reading) ያእቆብ 2፡14-26 አብርሃምንና ረዓብ በተግባር የሚያሳዩትን የእምነት ምሳሌ በመጠቀም የእምነትን ባህሪ አብራሮቶ አስቀምጧል። ቁጥር 24 ላይ እንደተቀመጠው ለዚህ መከራከሪያ እንደ ማጠቃለያ ሆኖ የሚያገለግለው እምነት ወደ ተግባር ካልመራ ህያው እንዳልሆነ ብቻ ነው። 2. ቁልፍ ነጥቦች (Key Terms) #ፅድቅ በዚህ ዐውደ-ጽሑፍ መሰረት “መጽደቅ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ መባልን ሳይሆን በሰዎች ፊት ስላለን ምልልስ አፅንኦት እየሰጠ መሆኑን መረዳት አስፈላጊ ነው። #ስራ ስራ የሚለው ገለፃ ከእምነት ጋር የሚጣጣሙ ተግባራትን በተለይም የፍቅር እና የበጎ አድራጎት ተግባራትን ይመለከታል። ለምሳሌ ሁለኛው ምዕራፍን ከቁጥር 15 ጀምሮ ስንመለከት "ወንድም ወይም እኅት ራቁታቸውን ቢሆኑ የዕለት ምግብንም ቢያጡ፥ ከእናንተ አንዱም በደኅና ሂዱ፥ እሳት ሙቁ፥ ጥገቡም ቢላቸው ለሰውነት ግን የሚያስፈልጉትን ባትሰጡአቸው ምን ይጠቅማቸዋል? እንደዚሁም ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው" ብሎ ስራችን በሰዎች ፊት መገለጥ እንዳለበት ያስተምራል። ይህም ቀጥተኛ የሆነ የመዳን ስራ ጋር የማይገናኝ ሲሆን ነገር ግን በስራ ሲገለጥ እምነታችን ህያው መሆኑን ለመጠቆም ነው። ተግባራዊ ምላሽ (Application) 👉 የግል እምነታችንን በተመለከተ በዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ አማኝ እምነቱ በተግባር መታየት አለበት። 👉 በህብረት ደግሞ እምነታችንን በሥራ በማሳየት በተለያዩ አገልግሎቶች ፣ ማህበራዊና ፍትሀዊ ተሳትፎዎች ውስጥ መግለጥ መቻል አለብን። ✍️ ሔኖክ ነጋሽ
77