የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ምልከታ
(St. John chrysostom's observation )
በጥንቲቷ ቤተ ክርስቲያን የቍስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳስ የነበረው ዮሐንስ አፈወርቅ (John chrysostom ) ቅዱሳን መጽሐፍት በግልጥ የሚያትቱትን የክርስቶስ አስታራቂነት,ሊቀ ክህነት ለማስገንዘብ እንዲህ ይጠይቃል ....
"ከእርሱ( ከኢየሱስ) በቀር ራሱ ብቻውን ኃጢያት ማሥተሰረይ የሚችል የታመነ አስታራቂ ማነው ?
ለማስታረቅ ኃጢያትንስ ለማስተሰረይ ያቀረበው መሥዋዕትስ ምንድነው?"
(ሃይማኖተ አበው, ዘዮሐንስ አፈወርቅ
ክፍል 2, ምዕራፍ 82, ቁጥር 14)
ከክርስቶስ ውጪ አማላጅ አስታራቂ ሊቀ ካህን መካከለኛ እንዳላችሁ የምታስቡ ወገኖች :
አሉን ያላችኋቸው ሊቀ ካህናት
ኃጢያትን ማስተሰረይ ችለው ይሆንን ??
ያቀረቡትስ መስዋዕት ምን ይሆን ? " የሚል እንድምታ ያለው መጠይቅ ነው
..መጠይቁ ተገቢ እና አሁንም መጠየቅ ያለበት ነው !
በዚህ አዕላፉ አዕላፍ "አስታራቂ?" አንግቦ በሚኳትንበትም ዘመን የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅን ጥያቄ ደጋግመን እንጠይቃለን
"ከእርሱ( ከኢየሱስ) በቀር ራሱ ብቻውን ኃጢያት ማሥተሰረይ የሚችል የታመነ አስታራቂ ማነው ?
ለማስታረቅ ኃጢያትንስ ለማስተሰረይ ያቀረበው መሥዋዕትስ ምንድነው?"
እርሱ [ኢየሱስ] ግን
🛑 ባሕርያችንን ባሕርይ አድርጎ #ሊቀ ካህናት #( አስታሪቂ ) ሆነን እንጂ ስለ እኛም ሥጋውን መሥዋዕት አድርጎ ወደ አባቱ አቀረበ : እንጂ በታመመበት በሥጋው ለርሱ ገንዘብ ለመሆን አበቃን !
ሃይማኖተ አበው, ዘዮሐንስ አፈወርቅ
ክፍል 2, ምዕራፍ 62, ቁጥር 16)
🛑ከዚህም በኃላ የምናምንበትን #አስታራቂ ሐዋሪያ እርሱም አብነት አድርጉት አለ አብ : ከወዲያ ዓለም ወደዚህ ዓለም ስለ ላከው ሐዋሪያ አለው ስለ አመንብት በጎ ስራ ለመስራት የምንቀና ደግ ወገን አድርጎ ገንዘብ አደረገን : ለእኛ #ማልዶልናልና የምናምንበት #ሊቀ ካህነት ( አስታራቂ ) ነው !!!
(ሃይማኖተ አበው, ዘዮሐንስ አፈወርቅ
ክፍል 2, ምዕራፍ 63, ቁጥር 26)
🛑ክርስቶስ ስጋውን መስዋዕት አድርጎ አቀረበ #ሊቀ ካህናታችን ነውና ወደ እርሱ ስላቀረበው በስልጣኑ ስለ አሳረገው
ስለ ስጋው : ስለ ደሙ ወደ እርሱ መቅረብ ከተቻለው ከዚህ መስዋዕት የተነሳ አብ አደነቀ ( ዕብ 10 : 1 - 15,)
(ሃይማኖተ አበው, ዘዮሐንስ አፈወርቅ
ክፍል 23, ምዕራፍ 66, ቁጥር 23)
በአጠቃላይ ....ከሰው መካከል ሊቤዥ ሀጢያትንም ሊያተሰረይ የሚችል አንድም እንኳ ስላልነበረ.. አካላዊው ቃል
(እግዚአብሔር ወልድ) - ቃልነቱ ሳይለወጥ
ስጋ ሆኖ ,የሰውነትን ባሕርይ ተገንዝቦ ( ከኃጢያት በቀር)
#ራሱንም( ደሙን, ስጋውን) ንጹህ መስዋዕት አድርጎ አቀረበ !
በዚህም በእግዚአብር አብ እና በእኛ መካከል ያለውን የጥል ግድግዳ አፍርሶ ከአብ ጋር አስታረቀን( አማለደን) , በርሱም #የኃጢያት ስርየት ሆኖልናል !
በምድር ላይ ካሉት ስጋ ለባሾች, በሰማይ ካሉ መላዕክቶች መካከል ይሄንን ያደረገ ማን ነው ?
የኃጢያት ዕዳ በመስቀል የከፈለ?
ቅዱስ ደሙን, ክቡር ስጋውን ለመሰዋዕት አቅርቦ አብን ደስ ያሰኘ ያስታረቀንስ ማን ነው ???
ማንም የለም!! .. ከ ኢየሱስ በቀር....
🗣ወኮነ አራቂ ለአዲስ ኪዳን
ሊቀ ካህናት ኢየሱስ🙌
ወስብሐት ለእግዚአብሔር 🙏