Bashewam Primary & Junior School 1-8
Kanalga Telegram’da o‘tish
2 747
Obunachilar
-224 soatlar
+207 kunlar
+4230 kunlar
Postlar arxiv
ለባሸዋም ትምህርት ቤት የተማሪ ወላጆች ወይም ህጋዊ አሳዳጊዎች በሙሉ ፡
፡
ውድ የባሸዋም ተማሪዎች እና ወላጆች እንኳን ለ2018ዓም የትምህርት ዘመን በሰላም አደረሳችሁ ፡ እያልን ከዚህ በታች ባለው መመሪያ መሰረት ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት እንድትልኩልን በአክብሮት እንጠይቃለን ።
የ2018ዓም ትምህርት ከኬጂ (ቅድመ አንደኛ) እስከ 12ኛ ክፍል ሰኞ መስከረም 5/2018 ዓም ይጀምራል ።
መስከረም 5 /2018ዓም ትምህርት የሚሰጠው ለግማሽ ቀን በመሆኑ ወላጆች ልጆቻችሁን ከቀኑ 6:30 ትምህርት ቤት በመምጣት እንድትወስዱ እናሳስባለን ።
ትምህርት ከጠዋቱ 2:30 ስለሚጀመር ተማሪዎች ቀደም ብለው ከጠዋቱ 2:00 በፊት ትምህርት ቤት መገኘት ይኖርባቸዋል ።
ከኬጂ( ቅድመ አንደኛ) እስከ 6ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች ፡ ወላጆች ትምህርት ቤት በመምጣት ልጅዎን በየክፍሉ ለተመደቡ ረዳት መምህራን በአግባቡ እንዲያስረክቡ በጥብቅ እናሳስባለን።
ከቅድመ አንደኛ እስከ 6ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች ምሳ እቃ እና ቦርሳቸው ላይ ስማቸው መፃፍ አለበት ።
ሁሉም ተማሪዎች የተማሪ የደንብ ልብስ Uniform አሟልተው መምጣት አለባቸው ፡ ዩኒፎርም ሳይለብስ እና መታወቂያ ሳይዝ የሚመጣ ተማሪ ትምህርት ቤት ውስጥ የማናስገባ መሆኑን ከወዲሁ እናሳውቃለን።
ማንኛውም ተማሪ ከመስከረም 5/2018ዓም ጀምሮ ወደ ትምህርት ቤት የሚገባው የተማሪ መታወቂያ በማሳየት በመሆኑ ልጅዎ መታወቂያ ይዞ(ዛ) ወደ ትምህርት ቤት መምጣቱን(ቷን) እንዲያረጋግጡ እናሳስባለን ።
ጀማሪ ተማሪዎች መታወቂያቸውን አንገታቸው ላይ ማንጠልጠል አለባቸው ። ወላጆች ትምህርት ቤት ሲመጡ የህፃኑን(ኗን) መታወቂያ መያዝ አለባቸው።
ባሸዋም ትምህርት ቤት ፡ "ትውልድ እንቀርፃለን ፡ሁሌም ለለውጥ ዝግጁ ነን"።
መስከረም 2/2018ዓም
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
