uz
Feedback
Bashewam Primary & Junior School 1-8

Bashewam Primary & Junior School 1-8

Kanalga Telegram’da o‘tish

Bashewam School Grade 1-8

Ko'proq ko'rsatish
2 747
Obunachilar
-224 soatlar
+207 kunlar
+4230 kunlar
Postlar arxiv
በባሸዋም ትምህርት ቤት የ2018ዓም በዛሬው እለት ተጀምሯል።

ለባሸዋም ትምህርት ቤት የተማሪ ወላጆች ወይም ህጋዊ አሳዳጊዎች በሙሉ ፡ ፡ ውድ የባሸዋም ተማሪዎች እና ወላጆች እንኳን ለ2018ዓም የትምህርት ዘመን በሰላም አደረሳችሁ ፡ እያልን ከዚህ በታች ባለው
ለባሸዋም ትምህርት ቤት የተማሪ ወላጆች ወይም ህጋዊ አሳዳጊዎች በሙሉ ፡ ፡ ውድ የባሸዋም ተማሪዎች እና ወላጆች እንኳን ለ2018ዓም  የትምህርት ዘመን በሰላም አደረሳችሁ ፡ እያልን ከዚህ በታች ባለው መመሪያ መሰረት ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት እንድትልኩልን በአክብሮት እንጠይቃለን ። የ2018ዓም ትምህርት ከኬጂ (ቅድመ አንደኛ) እስከ 12ኛ ክፍል  ሰኞ መስከረም 5/2018 ዓም ይጀምራል ።  መስከረም 5 /2018ዓም ትምህርት የሚሰጠው ለግማሽ ቀን በመሆኑ ወላጆች ልጆቻችሁን ከቀኑ 6:30 ትምህርት ቤት በመምጣት እንድትወስዱ እናሳስባለን ። ትምህርት ከጠዋቱ 2:30 ስለሚጀመር ተማሪዎች ቀደም ብለው ከጠዋቱ 2:00 በፊት ትምህርት ቤት መገኘት ይኖርባቸዋል ።  ከኬጂ( ቅድመ አንደኛ) እስከ 6ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች ፡ ወላጆች ትምህርት ቤት በመምጣት ልጅዎን በየክፍሉ ለተመደቡ ረዳት መምህራን በአግባቡ እንዲያስረክቡ በጥብቅ እናሳስባለን። ከቅድመ አንደኛ እስከ 6ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች ምሳ እቃ እና ቦርሳቸው ላይ ስማቸው መፃፍ አለበት ። ሁሉም ተማሪዎች የተማሪ የደንብ ልብስ Uniform አሟልተው መምጣት አለባቸው ፡ ዩኒፎርም ሳይለብስ እና መታወቂያ ሳይዝ የሚመጣ ተማሪ ትምህርት ቤት ውስጥ የማናስገባ መሆኑን ከወዲሁ እናሳውቃለን። ማንኛውም ተማሪ ከመስከረም 5/2018ዓም  ጀምሮ ወደ ትምህርት ቤት የሚገባው የተማሪ መታወቂያ በማሳየት በመሆኑ ልጅዎ መታወቂያ ይዞ(ዛ) ወደ ትምህርት ቤት መምጣቱን(ቷን) እንዲያረጋግጡ እናሳስባለን ።   ጀማሪ ተማሪዎች መታወቂያቸውን አንገታቸው ላይ ማንጠልጠል አለባቸው ። ወላጆች ትምህርት ቤት ሲመጡ የህፃኑን(ኗን) መታወቂያ መያዝ አለባቸው። ባሸዋም ትምህርት ቤት ፡ "ትውልድ እንቀርፃለን ፡ሁሌም ለለውጥ ዝግጁ ነን"። መስከረም 2/2018ዓም