uz
Feedback
Bashewam Primary & Junior School 1-8

Bashewam Primary & Junior School 1-8

Kanalga Telegram’da o‘tish

Bashewam School Grade 1-8

Ko'proq ko'rsatish
2 763
Obunachilar
+524 soatlar
+157 kunlar
+6530 kunlar
Postlar arxiv
የባሸዋም ትምህርት ቤት ሁለተኛ ዙር የወላጆች ስልጠና "ማንበብ የመቻል እና ያነበቡትን ነገር የመረዳት ጉዳይ ለገጠመን የትምህርት ስብራት ፍቱን መፍትሔዎች ምንድናቸው " በሚል ስልጠና እየሰጠ ነው።

የትምህርት ቤት ወርሀዊ ክፍያ ያልከፈላችሁ ነገ ቅዳሜ ጥቅምት 10/2016 የሂሳብ ክፍሎች ስለሚገቡ ክፍያችሁን ያለቅጣት እንድትከፍሉ እናሳስባለን ።

የባሸዋም ትምህርት ቤት የተማሪ ወላጆች ጥቅምት 10/2016 ዓም የማጠናከሪያ ትምህርት የሚጀመር መሆኑን እያሳወቅን 2:30 - 6:30 ትምህርት የሚሰጥ መሆኑን እናሳውቃለን ። የማጠናከሪያ ክፍያ በትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ ንብ ባንክ አገልግሎት እየሰጠ ስለሆነ እና የትምህርት ቤቱ ፋይናንስ ክፍል ቅዳሜ ቀን አገልግሎት እየሰጠ ስለሆነ ትምህርት ቤት በመምጣት መክፈል ትችላላችሁ ።

የባሸዋም ትምህርት ቤት ሰርቪስ የምትጠቀሙ የተማሪ ወላጆች የጥቅምት ወር የትራንስፖርት የሰርቪስ ክፍያ እንድትከፍሉ እናሳስባለን። ከሰኞ 12/02/2015ዓም ጀምሮ ደረሰኝ እየታየ አገልግሎት የምንሰጥ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን ፡

ሁሉም ጥፋቶች በቅጣት ብቻ አይታረሙም!!!! ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡ ☞ ወጣቱ ልጅ የመጀመሪያ ደረጀ ት/ቤት አስተማሪውን በሆነ ሰርግ ላይ ያየዋል። ሮጦ ሄዶ በትህትናና በአድናቆት ሰላም ካለው በኃላ አስተማሪውን "አስታወስከኝ ወይ?" አለው።አስተማሪውም ግራ በመጋባት ውስጥ ሆኖ "ይቅርታ አላስታውስህም እንዴት እንደተዋወቅን ልትነግረኝ ትችላለህ?" አለው፤ወጣቱም ልጅ እንዲህ እያለ ተረከለት "3ኛ ክፍል እያለን ያንተ ተማሪ ነበርኩ፤ታዲያ አንድ ቀን የክፍል ጓደኛዬን ቆንጆና ልዩ የሆነውን የእጅ ሰዓቱን ሰርቄበት ነበር።እሱም እያለቀሰ ሄዶ የእጅ ሰዓቱ እንደተሰረቀበት ላንተ ይናገራል፤አንተም መጥተህ ልትፈትሸን ሁላችንም ክፍል ውስጥ ያለን ልጆች አይናችንን ጨፍነን እጃችንን ከፍ አድርገን ፊታችንን ወደ ግድግዳ አዙረን እንድንቆም አዘዝከን።በዛን ጊዜ እኔ የፍተሻውን ውጤት እያሰብኩ በጣም ተረበሽኩ፤የምገባበትን አጣሁ።አስበው ሰዓቱ በኔ ኪስ ውስጥ ተገኝቶ ሁሉም ተማሪ ሌባ እያለ ሲሰድበኝ፤ ግቢ ውስጥ መጠቋቆሚያ ስሆን፤ከት/ቤት ተባርሬ ወላጅ አምጣ ስባልና ወላጆቼ ይሄን አሳፋሪ ድርጊቴን ሲሰሙ።በዚህ ጭንቅ ውስጥ እያለሁ የፍተሻው ተራ ደርሶ እጅህ ወደ ኪሴ ሲገባና ሰዓቱን ቀስ አድርገህ ከኪሴ ስታወጣ ተሰማኝ፤በቃ መጥፎ ዜናው ሊነገር ነው አለቀልኝ ብዬ ስጠባበቅ አንተ ግን ምንም ሳትል የመጨረሻው ልጅ እስክትደርስ ፍተሻውን ቀጠልክ።ፍተሻውም ሲያልቅ አይናችሁን ግለጡና ወደየቦታችሁ ተመለሱ አልከን።እኔ ግን መልሰህ ታስቆመኛለህ ብዬ መቀመጡን ፈራሁ።በጣም የሚገርመው አንተ ሰዓቱን አውጥተህ ለባለቤቱ መለስክለት፤ግን ከማን ኪስ ውስጥ እንዳገኛህና ማን እንደሰረቀበት ምንም አልተናገርክም ነበር።በት/ቤት ቆይታዬም ምን እንደተፈጠረ ማንም አላወቀብኝም ነበር፤አንተም ምንም ብለኸኝ አታውቅም።እኔ ግን ስሜንና ክብሬን እንዳዳንክና ስብዕናዬን እንደጠበክልኝ ዛሬም ድረስ አስታውስሃለው።አንተም ይሄን ታሪክ ቶሎ ትረሳለህ ብዬ አልገምትም አሁንስ አስታወስከኝ?" አለው።አስተማሪውም በመገረም ውስጥ ሆኖ "ትንሽ ትንሽ አስታውሳለው በማን ኪስ ውስጥ እንዳገኛሁ ግን አላስታውስም፤ ምክንያቱም እኔም ስፈትሻችሁ የነበረው አይኔን ጨፍኜ ነበር!!"አለው። በህይወታችን ለምናከናውናቸው ነገሮች ሁሉ ጥበብ ያስፈልገናል።እንደ አስተማሪ እንደ ወላጅ እንደ መሪ...ወዘተ ለአንዳንድ ነገሮች አይናችንን መጨፈን አለብን ምክንያቱም ሁሉም ጥፋቶች በቅጣት ብቻ አይታረሙም!!!!

የጥቅምት ወር የትምህርት ቤት ክፍያ ይክፈሉ ።

የመልካም ስነምግባር ባህሪ

16ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን አከባበር በትምህርት ቤታችን (አዲስ አበባ 06/2/2016 ዓ.ም) የዘንድሮው የሰንደቅ አላማ ቀን ለ16ኛ ጊዜ የተከበረ ሲሆን እለቱም "የሰንደቅ ዓላማችን ከፍታ ለሕብረ-ብሔራዊ አንድነታችንና ለሉዓላዊነታችን ዋስትና ነው!" በሚል መሪ ቃል በትምህርት ተቋማት ላይ ተከብሩዋል፡፡

የባሸዋም ትምህርት ቤት "ንባብ የሁሉም ትምህርት መሰረት ነው" ። በሚል ፅንሰ ሐሳብ ለተማሪ ወላጆች ስልጠና ሰጠ።