uz
Feedback
AAU EXAM COLLECTION

AAU EXAM COLLECTION

Kanalga Telegram’da o‘tish

Welcome to our channel! This platform is dedicated to providing valuable information and support for AAU students, with a special focus on first-year students. Here, you can access last year's exam papers and assignments to aid your studies!! @Sirawdink

Ko'proq ko'rsatish
5 971
Obunachilar
+1324 soatlar
+847 kunlar
+19730 kunlar
Postlar arxiv
የ69 ዓመቱ የእድሜ ባለፀጋ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ አቶ ወልደየስ አያና አሻቦ ይባላሉ፡፡ በ4ኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ፈተና ከሚፈተኑ ተማሪዎች መካከል አንዱ ናቸው፡፡ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ ወላይታ
የ69 ዓመቱ የእድሜ ባለፀጋ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ አቶ ወልደየስ አያና አሻቦ ይባላሉ፡፡ በ4ኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ፈተና ከሚፈተኑ ተማሪዎች መካከል አንዱ ናቸው፡፡ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ ወላይታ ዞን የተወለዱት አቶ ወልደየስ፤ እስከ 8ኛ ክፍል ድረስ ተምረው በደርግ ዘመን ትምህርታቸውን ለማቋረጥ ተገደው ነበር፡፡ ነገር ግን ለትምህርት ያላቸው ቁርጠኝነት ሳይቀንስ ከረጅም ዓመታት በኋላ በ2015 ዓ.ም ወደ ትምህርት ተመልሰው ከ9ኛ ክፍል በመጀመር፣ ዛሬ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኝ ለመሆን በቅተዋል፡፡ "የግብርና ሥራዬን በዘመናዊ መንገድ ለማሻሻልና በተሻለ ሁኔታ ለማምረት እውቀት ለማግኘት ነው” ሲሉ ትምህርት ለመማር የቀጠሉበትን ምክንያት ያስረዳሉ፡፡ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርቲ የመልቀቂያ ፈተናቸውን እየወሰዱ የሚገኙት የስድስት ልጆች አባት የሆኑት አቶ ወልደየስ፤ በፈተናው ውጤታማ ለመሆን ተስፋ እንዳላቸው ይገልጻሉ፡፡ ትክክለኛ መረጃ የምትገኙበት የ 12ኛ https://t.me/+esqs-EEENtxlM2Q8               Share share🙏🙏 ለተጨማሪ መረጃ👇👇👇👇 ╔═══════════╗ ♨️ ♦️ @ethiouniversity1  ♨️ ♨️ ♦️ @ethiouniversity1  ♨️ ♨️ ♦️ @ethiouniversity1  ♨️ ╚═══════════╝

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ የሚገኙ ከትግራይ ክልል የመጡ ተማሪዎች፣ የክረምት ወራት የእረፍት ጊዚያቸውን በዩኒቨርሲቲው እንዲቆዩ ዩኒቨርሲቲው ፈቅዷል፡፡ ተማሪዎቹ በትግራይ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ የሚገኙ ከትግራይ ክልል የመጡ ተማሪዎች፣ የክረምት ወራት የእረፍት ጊዚያቸውን በዩኒቨርሲቲው እንዲቆዩ ዩኒቨርሲቲው ፈቅዷል፡፡ ተማሪዎቹ በትግራይ ክልል አለ ባሉት "አስገዳጅ የውትድርና ምልመላ" እና የፀጥታ ስጋት ምክንያት ወደ ቤተሰቦቻቸው መመለስ እንደማይችሉ በመግለፅ የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር በክረምት የዕረፍት ወራት የማደሪያ አገልግሎት (Dormitory Service) እንዲፈቅድላቸው በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ጥሪ አቅርበው ነበር፡፡ ተማሪዎቹ ወደ ትግራይ የሚሔዱ ከሆነ ትምህርታቸው ሊቋርጥባቸው እንደሚችልም ስጋታቸውን ገልፀው ነበር፡፡ አሁን ላይ ተማሪዎቹ እስከሚቀጥለው የትምህርት ዓመት ድረስ አስፈላጊውን የምግብ እና የዶርም አገልግሎት እያገኙ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እንዲቆዩ የተፈቀደላቸው መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከተማሪዎቹ ሰምቷል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኮምዩኔኬሽን ዳይሬክተር ኤልያስ ወርቁ (ዶ/ር) ተማሪዎቹ በዩኒቨርሲቲው እንዲቆዩ መፈወዱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል። "አስፈላጊው በጀት እንዲመጣ ተደርጎ ተማሪዎቹ በግቢው እንዲቆዩ ተደርጓል" ብለዋል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት ጄይሉ ዑመር (ዶ/ር) ተማሪዎቹ በግቢው ያሉ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ላቀረቡት ቅሬታም ምላሽ የተሰጠ መሆኑን ገልፀዋል። ትክክለኛ መረጃ የምትገኙበት የ 12ኛ https://t.me/+esqs-EEENtxlM2Q8               Share share🙏🙏 ለተጨማሪ መረጃ👇👇👇👇 ╔═══════════╗ ♨️ ♦️ @ethiouniversity1  ♨️ ♨️ ♦️ @ethiouniversity1  ♨️ ♨️ ♦️ @ethiouniversity1  ♨️ ╚═══════════╝

🎓 " ከ2010 ዓ/ም እስከ 2015 ዓ/ም የዲግሪ ተመራቂዎች በሙሉ የትምህርት ማስረጃቸውን ለማረጋገጥ በድጋሚ ፈተና ሊፈተኑ ነው " በሚል እየተሰራጨ ያለው መረጃ የተሳሳተና ህዝብ አደናጋሪ ነው።
+2
🎓 " ከ2010 ዓ/ም እስከ 2015 ዓ/ም የዲግሪ ተመራቂዎች በሙሉ የትምህርት ማስረጃቸውን ለማረጋገጥ በድጋሚ ፈተና ሊፈተኑ ነው " በሚል እየተሰራጨ ያለው መረጃ የተሳሳተና ህዝብ አደናጋሪ ነው። በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች (በፌስቡክ እና ቲክቶክ) ላይ የኢፌዴሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ያዘጋጀውንና ለህዝብ አስተያየት ይፋ ያዳረገውን አዲስ ረቂቅ መመሪያ በማዛበት፣ " ከ2010 እስከ 2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ሳይፈተኑ በመጀመሪያ፣ ሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ የተመረቁ ተማሪዎች በሙሉ የትምህርት ማስረጃቸውን ለማረጋገጥ ሲባል በድጋሚ ፈተና ሊሰጣቸው ነው " በሚል እየተሰራጨ ያለው መረጃ ፍጹም የተሳሳተ እና ህዝብን የሚያደናግር ነው። ህዝብ አስተያየት እንዲሰጥበት ይፋ የተደረገው መመሪያ በትክክል እነማንን ነው የሚመለከተው ? ይህ መመሪያ/አሰራር የሚመለከተው በቀድሞው ዲፕሎማ (10+3፣ 12+2 ወይም ቴክኒክና ሙያ ደረጃ 4 ስልጠና) ተመርቀው፣ ነገር ግን የደረጃ አራት የብቃት ማዕቀፍ (COC) ሳይኖራቸው የመጀመሪያ ዲግሪ፣ ሁለተኛ ዲግሪ (MA) ወይም ሦስተኛ ዲግሪ (PhD) የያዙትን ብቻ ነው። እነዚህ ዜጎች የትምህርት ማስረጃቸውን ለማረጋገጥ አሁን በያዙት የትምህርት ደረጃ/የያዙት ዲግሪን መሰረት ተደርጎ የሚሰጠውን ፈተና መውሰድና ማለፍ ይኖርባቸዋል። በአጭሩ የሚመለከተው ወይም ተፈጻሚነቱ :- - ለዲግሪ ትምህርት ከመግባታቸው በፊት የሙያ ብቃት ማረጋገጫ (COC) ፈተና ሳይወስዱ ዲግሪ የተማሩ እና የተመረቁ። - የሙያ ብቃት ማረጋገጫ (COC) የወሰዱት ለዲግሪ ትምህርት ከተመዘገቡ በኋላ የሆኑ ተማሪዎች ላይ ነው። በመደበኛው መንገድ የመግቢያ መስፈርቱን አሟልተው (ለምሳሌ የ12ኛ ክፍል ማለፊያ አምጥተው) የገቡ፣ ወይም ከዲፕሎማ ተነስተው የCOC ፈተና አልፈው ዲግሪ የጫኑ እና የተመረቁ ዜጎችን ይህ መመሪያ አይመለከታቸውም። የትምህርት ማስረጃቸውም ያለ ምንም ተጨማሪ ፈተና እንደ ቀድሞው ይረጋገጥላቸዋል። መመሪያው በአሁኑ ወቅት በረቂቅ ደረጃ ላይ ያለና እስከ ሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለህዝብ አስተያየት ክፍት የተደረገ መሆኑ ታውቋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ አዲስ አበባ ሃምሌ 4 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

Breaking news From 2010 to 2015, the Ministry of Education has decided to re-examine all undergraduate, graduate and PHD grad
Breaking news From 2010 to 2015, the Ministry of Education has decided to re-examine all undergraduate, graduate and PHD graduates. . . . The ministry has decided that students who graduated from 2010 to 2015 without taking the final examination(exit) and have certificates in their possession will be re-examined for the exit examination. . . . The Minister of Education, Professor Birhanu Nagga, said those who did not take the exit examination will not have their educational certificates verified.

🌟YOUR LEADERSHIP JOURNEY STARTS HERE Applications for the Young Leaders Development Program (YLDP) 2026 are now OPEN! Are yo
+1
🌟YOUR LEADERSHIP JOURNEY STARTS HERE Applications for the Young Leaders Development Program (YLDP) 2026 are now OPEN! Are you a recent graduate ready to lead, grow, and make a meaningful impact? Gain hands-on experience, develop essential leadership and professional skills, connect with industry experts, and become part of a community committed to driving Ethiopia's development. Your future starts here. Apply now! https://forms.gle/rPtc3P6LBDusyXpe9 JD( job description) https://surl.li/kkxyen

ለራሱ ምርቃት የተገዛው በሬ ወግቶት ህይወቱ ያለፈው ተመራቂ የቀብር ስነ-ስርዓት ተፈጸመ😭 በቅርቡ ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ በኤሌክትሪካል ኢንጅነሪንግ ዘርፍ በታላቅ ስኬት ተመርቆ፣ ለነገው ህይወቱ ትልቅ
ለራሱ ምርቃት የተገዛው በሬ ወግቶት ህይወቱ ያለፈው ተመራቂ የቀብር ስነ-ስርዓት ተፈጸመ😭 በቅርቡ ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ በኤሌክትሪካል ኢንጅነሪንግ ዘርፍ በታላቅ ስኬት ተመርቆ፣ ለነገው ህይወቱ ትልቅ ተስፋ ሰንቆ የነበረው ፍሰሐ አስማማው እጅግ ልብ በሚሰብር አደጋ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል። ይህ ተስፋ የተጣለበት ወጣት ከሳምንት በፊት ነበር የምርቃት ካባውን የደረበው። ወላጆችና ዘመድ አዝማድም የምርቃቱን ደስታ አብረውት ለማሳለፍ ከጎንደር ጋይንት (ጎብጎብ) ከተማ ወደ ተወለደበት አካባቢ ይዘውት አምርተው ነበር። ነገር ግን በትላንትናው ዕለት ለምርቃቱ ድግስ ተብሎ የተገዛው በሬ በድንገት ወግቶት ህይወቱ ሊያልፍ ችሏል። የዚህ ወጣት ስኬትና ህልም በአጭር የተቀጨበት አሳዛኝ የቀብር ስነ-ስርዓት ዛሬ በጋይንት ጎብጎብ ቀራኒዮ መድሃኒዓለም ቤተክርስቲያን ወዳጅ ዘመዶቹ፣ የክፍል ጓደኞቹና የአካባቢው ማህበረሰብ በተገኙበት ተፈፅሟል። ለወላጆቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ እንዲሁም ለጓደኞቹ በሙሉ ፈጣሪ ፍጹም መፅናናትን ይስጥልን። Via ጉርሻ @AAUMEREJA

Academic calender 2025/26 for summer In Service (PGDT) Programs. @AAUMEREJA✅
Academic calender 2025/26 for summer In Service (PGDT) Programs. @AAUMEREJA

ማስታወቂያ ለ PGDT ተማሪዎች በሙሉ፣ @AAUMEREJA
ማስታወቂያ ለ PGDT ተማሪዎች በሙሉ፣ @AAUMEREJA

Call for training School of Commerce, AAU @AAUMEREJA
Call for training School of Commerce, AAU @AAUMEREJA

2019_Academic Calender_2026_27_FINAL.pdf4.56 KB

📢 AAU Public Lecture College of Business & Economics “The Future of Work & Implications for Business Schools” 👤 Prof. Ian O
📢 AAU Public Lecture College of Business & Economics “The Future of Work & Implications for Business Schools” 👤 Prof. Ian O. Williamson, UC Irvine 📅 09 July 2026 ⏰ 2:00 – 4:00 PM 📍 Room Eshetu Chole 206 🌐 Online: https://meet.google.com/dtu-uwbj-twc Join us to explore how changing work trends are reshaping business education and leadership. Don’t miss this insightful session!

የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና ለወሰዳችሁ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ _______ በሰኔ 2018 ዓ.ም በጤና ሚኒስቴር በኩል የተሰጠውን የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና የወሰዳችሁ ተመዛኞች ከሰኔ 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ
የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና ለወሰዳችሁ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ _______ በሰኔ 2018 ዓ.ም በጤና ሚኒስቴር በኩል የተሰጠውን የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና የወሰዳችሁ ተመዛኞች ከሰኔ 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ https://hple.moh.gov.et ላይ በመግባትና የብሄራዊ መለያ ቁጥር(FAN) እና Password በማስገባት የፈተና ውጤታችሁን መመልከት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን በውጤታችሁ ላይ ቅሬታ ያላችሁ ተመዛኞች ውጤት ከተገለጸበት ዕለት አንስቶ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የስራ ቀናት በስልክ ቁጥር 952 በስራ ሰዓት በመደወል ሙሉ ስም፣ ዲፓርትመንት እና የተማራችሁበትን የትምህርት ተቋም ስም በማሳወቅ ጥያቄዎቻችሁን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡ ማሳሰቢያ፦ የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተናውን ያለፋችሁ ተመዛኞች ከሰኞ ሃምሌ 6/2018 ዓ.ም ጀምሮ ስም ዝርዝራችሁ ወደ ክልል የሚላክ ስለሆነ የሙያ ፍቃዳችሁን 12ተኛ ክፍል በተማራችሁበት ክልል ማውጣት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡ Website: moh.gov.et Facebook: Ministry of Health,Ethiopia Twitter: x.com/fmohealth YouTube: youtube.com/@FMoHealthEthiopia Tiktok: tiktok.com/@mohethiopia Telegram: t.me/M0H_EThiopia Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VA

#AAU #GAT በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሚሰጠውን የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) ለመውሰድ ይመዝገቡ! የ GAT ማመልከቻ ጊዜ 👇 ከግንቦት 29 እስከ ነሐሴ 05/2018 ዓ.ም
#AAU #GAT በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሚሰጠውን የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) ለመውሰድ ይመዝገቡ! የ GAT ማመልከቻ ጊዜ 👇 ከግንቦት 29 እስከ ነሐሴ 05/2018 ዓ.ም https://portal.aau.edu.et ይግቡ። 'Online Exams' የሚለውን ይጫኑ። Quick Links ከሚለው ስር 'Apply for GAT' የሚለውን ይጫኑ። 'Test Taker Registration' የሚለውን ቅፅ ይሙሉ። የፓስፖርት መጠን ያለው ፎቶ ያስገቡ። 'Submit' የሚለውን ይጫኑ። ሲስተሙ የሚሰጥዎን የመለያ ቁጥር ይያዙ። ቴሌብር በመጠቀም የምዝገባ ክፍያ ይፈፅሙ። አድሚሽን ቲኬትዎን በማውረድ ፕሪንት ብለው፡፡ የ GAT ፈተና በሁለት ዞሮች ይሰጣል፦ ከሐምሌ 20-24/2018 ዓ.ም እና ከነሐሴ 07-08/2018 ዓ.ም

🛑 Stop searching for opportunities.✨ Let them find YOU🫵. 💼 Jobs 🎓 Internships 📚 Scholarships 🎉 Events All matched to yo
🛑 Stop searching for opportunities.✨ Let them find YOU🫵. 💼 Jobs 🎓 Internships 📚 Scholarships 🎉 Events All matched to your profile by AI. 🤖 ——————-You just show up. We handle the rest.-—————— 🌐 Visit now / እዚህ ይግቡ: portal.sabisa.app

Interview ያለባቹ ተማሪዎች specially Fresh graduates! እነሆ የInterview ጥያቄዎች ከነመልሶቻቸው JOIN US 👇 @cobe2018council

📢 CGA Internship Program 2026 – Apply Now! The Commercial Graduates Association (CGA) invites Accounting and Finance student
📢 CGA Internship Program 2026 – Apply Now! The Commercial Graduates Association (CGA) invites Accounting and Finance students and fresh graduates to join the 2026 Internship Program. Internship Locations: 📍 In Front of Civil Service University 📍 Yeka Sub-City, Woreda 08, House No. 493 📍 Around Kera ✅ Selection is on a First-Come, First-Served basis. Limited seats are available, so apply early to secure your internship placement. 📝 Apply now: https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSd66uWYb-eZUqZ-yV73iD1gK9N4EeP_c_3DkjF2sQalrvZ0Fg/viewform?usp=publish-editor 📢 Join our Telegram channel for updates: https://t.me/commercialgraduatesassoc Complete the application form today and reserve your internship seat! CGA – Promoting Professionalism Since 1950

Updated! The Ethiopian Capital Market Authority invites high-potential university students and young professionals to a 2-week immersive program combining: Foundational capital market training Departmental internship at ECMA Designed to bridge academia and industry, this merit-based program prioritizes academic excellence, financial sector interest, and inclusive participation. Apply now to gain a competitive edge in Ethiopia’s evolving financial landscape. Interested applicants who meet the requirements are invited to fill in this application form: https://forms.office.com/Pages/ResponsePage.aspx?id=Ge63UMjmKUexGVwGKXoH40IfgUxmqllKlQM4mvODCihUMk84Q082SU1JOFlPQkNXTDFCMFFCTEZUWS4u and send their supporting documents (CV, motivation letter, and grade report/transcript/tempo) to: summercamp@ecma.gov.et Application Deadline: July 8, 2026

ውድ ተመራቂ ተማሪዎች፤ የሚከተሉትን ወሳኝ መመሪያዎች በጥብቅ እንድታከብሩ እናሳስባለን፦ የመግቢያ በሮች (ጌቶች)፦ ተመራቂዎች በበራፍ ቁጥር 5 (Gate 5) በኩል ይገባሉ። ቤተሰቦች በበራፍ ቁጥር 6 (Gate 6) በኩል ይገባሉ። ማንኛውም ተመራቂ ወደ ምርቃት አዳራሹ ለመግባት የዩኒቨርሲቲውን ይፋዊ የምርቃት ጋውን (Gown) መልበስ ግዴታ አለበት። ለቤተሰብ የተሰጡ የQR ኮዶች ለአንድ ጊዜ አገልግሎት ብቻ የሚያገለግሉ ናቸው። አንዴ ከተነበቡ (ስካን ከተደረጉ) በኋላ ወዲያውኑ ስለሚሰረዙ በድጋሚ መጠቀምም ሆነ ለሌላ ሰው ማጋራት አይቻልም። ተመራቂዎችም ሆኑ ቤተሰቦች በሰዓቱ መገኘት አለባቸው። በሮቹ በተቀመጠው ሰዓት በጥብቅ የሚዘጉ በመሆኑ፣ ዘግይቶ የሚመጣ ሰው አይስተናገድም። የምርቃት ፕሮግራማችን የተሳካና የተደራጀ እንዲሆን ለምታደርጉት ትብብር እናመሰግናለን!

ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም የተሰጠው የ2018 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጤት ይፋ ተደረገ። ተፈታኞች የመውጫ ፈተና ውጤታቸውን በ https://result.ether
ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም የተሰጠው የ2018 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጤት ይፋ ተደረገ። ተፈታኞች የመውጫ ፈተና ውጤታቸውን በ https://result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት መመልከት ይችላሉ። መጀመሪያ የተቀመጠውን ሊንክ ይጫኑ በመቀጠል 'Exit Examination' ላይ 'View Results' የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤት መመልከት ይቻላል። ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ/ም Via @tikvahuniversity