uz
Feedback
የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

Kanalga Telegram’da o‘tish
916
Obunachilar
+224 soatlar
+37 kun
-530 kun
Postlar arxiv
በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብ/ፓርቲ ፅ/ቤት ከወረዳው ጠቅላላ አመራር ጋር በምርጫው ሂደት ያሳየውን ቁርጠኝነት ና ቅንጅታዊ አሰራር በቀሪ ጊዜያት በልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ላይ ሊደገም እንደሚገባ ተገለጸ። ሰኔ 02/2018 ዓም መሀል አምባ ይህ የተገለጸው በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ልዩ ትኩረት በሚሹና ወቅታዊና መደበኛ ስራዎችን በመገምገም በቀጣይ በበጀት አመቱ ቀሪ ስራዎች በሚቀጥሉት 20 ቀናት እንዲጠናቀቁ ኦሬንቴሽን በተሰጠበት ወቅት ነው። መድረኩን የጉራጌ ዞን ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ኸይሩ መሀመድ፣የገደባኖ ገየታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን፣ እና የወረዳው ዋና የመንገስት ተጠሪ የሆኑት አቶ አ/ረሂም ርዳ በጋራ መርተዋል። በዚህም ወቅት በወረዳው በሁሉም ዘርፎች የላቀ ውጤት በማስመዝገብ ህዝቡን ተጠቃሚ ለማድረግ በተለያዩ ጊዚያቶች ታቅዳው እየተሰሩ ያሉ ስራ በቀጣይ በተያዘለት ግዜ ውጤታማ ስራዎች በመስራት ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባ ተገልጿል። በሚቀጥለው በ20 ቀናት ዕቅድ አፈጻጸሞችን ከግብ ለማድረስ ትኩረት በመስጠት ለህዝቡ ተጠቃሚነት በመስራት አመራሮች የበኩላቸውን ሀላፊነት ሊወጡ እንደሚገባ ተመላክቷል። በተለይም የፋይዳ መታወቂያ ስርጭት፣ የኢቲዮ ኮደርስ ስልጠና፣ የገጠርና የከተማ ኮሪደር ልማት ስራዎች፣ የገቢ፣ የግብርና፣ የንግድ፣ የስራ እድል ፈጠራና ሌሎች ልማት ቀጣይ 20 ቀናት ለማስፈጸም ውጤታማ እንዲሆኑ ከመቼውም ጊዜ በላይ የተጠናከረ ክትትልና ርብርብ ማድረግ የሚጠበቅ ጉዳይ እንደሆነ ተገልጿል። በመጨረሻም በቀጣይ ቀናት የቀሩ ተግባራትን በተመለከተ እያንዳንዱ አመራር ልዩ ዕቅድ በማዘጋጀት ቀሪ ስራዎችን በከፍተኛ ትኩረትና በተሻለ ቅንጅት ማስፈፀም እንደሚገባ አቅጣጫ ተቀምጧል።

ግንቦት 30/2018 ዓ/ም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውሃ መስኖና ማዕድን  ልማት ቢሮ በዋን ዋሽ ፕሮግራም በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ኮንበል ከተማ ለሚያስገነባው የንጹህ መጠጥ ውሃ ማጠራቀሚያ ታንከር የቦታ ርክክብ ተደረገ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውሃ መስኖና ማዕድን  ልማት ቢሮ በዋን ዋሽ ፕሮግራም በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ኮንበል ከተማ ለሚያስገነባው የንጹህ መጠጥ ውሃ ማጠራቀሚያ ታንከር የቦታ ርክክብ እና ግንባታውን ከሸነፈው ተቋራጭ ጋር የውል ስምምነት ተደርጓል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውሃ መስኖና ማዕድን  ልማት ቢሮ በዋን ዋሽ ፕሮግራም መለሰ ጩፋ በሳይት ርክክቡ ወቅት እንዳሉት የክልሉን ህዝብ የንጹህ መጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ ተቋማቸው ከተለያዩ አጋር ድርጅቶች ጋር እየሰራ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸው በዛሬው በዋን ዋሽ ፕሮግራም በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ኮንበል ከተማ አንድ ባለ 100 እና አን ባለ 50 የንጹህ መጠጥ ውሃ ማጠራቀሚያ ታንከር ከ9 ሚሊዮን ብር በላይ ለማሰገንባት የቦታ ርክክብ መደረጉን አስታውቀዋል። የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን የህብረተሰቡን የንጹህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የመንግስት፣የህዝብና የባለሃብት አቅም በማቀናጀት በረካታ ስረዎች መሰራታቸውን ጠቅሰው የኮንበል ውሃ ጉዳይ ለበርካታ ጊዜ ጥረት ሲደረግ ቆይቶ በዛሬው እለት የክልሉ መንግስትና ወረዳው በጋራ በቅንጅት በመስራት በዛሬው እለት ሁለት የውሃ ማጠራቀሚያ ታንከር የቦታ ርክክብ ተደርጓል። የወረዳው ውሃና ማዕድን ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አ/ጀሊል ቱሉ በበኩላቸው የኮንበል ከተማ የንጽህ መጠጥ ውሃ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውሃ መስኖና ማዕድን  ልማት ቢሮ በዋን ዋሽ ፕሮግራም አማካኝነት ሁለት የውሃ ማጠራቀሚያ  ታንከር ግንባታ ለኮንትራክተር የቦታ ርክክብ መደረጉን ገልጸው ግንባታው ተገንብቶ እስኪጠናቀቅ ድረስ አስፈላጊውን እገዛ በወረዳ ደረጃ እንደሚያደርጉ አስታወቀዋል። በርክክቡ ወቅት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን፣የክልልና የዞን የውሃ ተቋማት ባለሙያዎች፣ የወረዳው ውሃ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አ/ጀሊል ቱሉ እና ባለሙያዎች እንዲሁም የኮንበል ከተማ አመራሮችና የሀገር  ሽማግሌዎች ተገኝተዋል።

ግነቦት 27/2018 ዓ/ም በአስገድዶ መድፈር  ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በ17 አመት ፅኑ እስራት ተቀጣ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ተከሳሽ መሃመድአሚን አረብ የተባለው ግለሰብ በቀን 12/08/2018 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 አካባቢ ላይ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሰፋቶ ቀበሌ ልዩ ስሙ አዳር ገበያ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ የግል ተባዳይ የሆነችውን ነዚፋ ሸምሱን ዕድሜዋ 5 ሲሆን እናትሽ እየጠራችሽ ነው በማለት ከምትጫወትበት ስፍራ አታሎ በመውሰድ ቤት ውስጥ በማስጋባት የግብር ስጋ ድፍረት በደል ወንጀል ፈፅሞባታል በሚል በወረዳው ዓ/ህግ ክስ የተመረተበት ሲሆን ተከሳሽም ድርጊቱ አልፈፀምኩም በማለት ክዶ ተከራክሯል። ዓ/ህግ አሉኝ የሚላቸው የሰው እና የሰነድ ማስረጃዎችን በማቅረብ ካሰማ በኃላ ፍርድ ቤቱ ተከሳሽ ይከላከል በማለት ብይን ቢሰጥም ተከሳሽ በተከሰሰበት ድንጋጌ ሊከላከል ባለመቻሉ ተከሳሽ ጥፋተኛ ሲል ፍርድ ሰጥቷል ። በመቀጠልም ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን የቅጣት አስተያየት የተቀበለ ሲሆን በዚህም ተከሳሽ ጥፋተኛ የተባለበት የወንጀል ህግ ድንጋጌ በተሻሻለው የቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 3/2016 መሰረት ደረጃ 5 እና እርከን 42 የሚያርፍ ነው ። ዓ/ህግ ድርጊቱ የተፈፀመው በእድሜዋ ምክንያት እራሷን መከላከል በማትችል ህፃን ልጅ ላይ ነው በማለት በወንጀል ህጉ አንቀጽ 84(1)(ሠ) መሰረት አንድ የቅጣት ማክበጃ ምክንያት ያቀረበ በመሆኑ ከእርከን 42 ወደ እርከን 43 ከፍ ይላል በመቀጠልም ተከሳሽ ሶስት የቅጣት ማቅለያ ምክንያቶችን ጠቅሶ አቅርቧል 1ኛ የወንጀል ሪከርድ የለብኝም 2ኛ ታማሚ የሆኑ ቤተሰቦቼን የምንከባከበው እኔ ነኝ 3ኛ ያለኝ የትምህርት ደረጃ ዝቅተኛ ነው በማለት ያቀረበ ሲሆን ፍርድ ቤቱም ሶስቱን የቅጣት ማቅለያ ምክንያቶችን በመቀበል ከእርከን 43 ወደ 40 ዝቅ አድርጎታል ። ፍርድ ቤቱም እርከን 40 ከሚያስቀምጠው ከ17 ዓመት እስከ 19 ዓመት ፅኑ እስራት ውስጥ ተከሳሽን ያርማል ሌሎችንም ያስተምራል ያለውን የ17 ዓመት ፅኑ እስራትን ወስኗል ። መፈጃው የወረዳው ፍትህ ጽ/ቤት ነው።

ግንቦት 25/2018 ዓ/ም የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን በትላንትናው ዕለት የተካሄደውን የ7ተኛ ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት በወረዳው ካለምንም የፀጥታ ችግር በከፍተኛ የህዝብ ተሳትፎ በሰላም መጠናቀቁን ተከትሎ አስተዋፅዎ ላደረጉ አካላት ምስጋና አቀረቡ። ፨፨፨፨፨////፨፨፨፨፨ ሀገራችን ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ስርዓትን ለመገንባትና የህዝቧን የሉዓላዊነት ስልጣን ለማረጋገጥ በከፍተኛ ቁርጠኝነት በጀመረችው ጉዞ ውስጥ፣ የወረዳችን ህዝብ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ያሳየው ከፍተኛ ተሳትፎና የሰለጠነ ዲሞክራሲያዊ ባህል አዲስ ታሪክ የጻፈ ስኬት ሆኖ መመዝገቡን አቶ ሚፋታ ሁሴን አስታውቀዋል። አቶ ሚፋታ በመልእክታቸው ምርጫው ፍጹም ሰላማዊ፣ ነጻ፣ ፍትሃዊና ተአማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የድርሻችሁን ለተወጣችሁ በሙሉ በተለይም በከተማና በገጠር ለሚገኘው ህዝባችን ምርጫው በሁሉም አካባቢ ተመሳሳይ ድጋፍ በመስጠት ከመንግስት ጎን በመሰለፍ ላደረገው አስተዋጾ በወረዳው አስተዳደር እና በራሳቸው ስም የላቀ ምስጋና አቀርበዋል። የወረዳው ህዝብ ከለሊቱ 11 ሰዓት ጀምሮ ምርጫ ቦርድ  የምርጫው ሂደት መጠናቀቁን እስኪያሳውቅ ጊዜ ድረስ ብርድ፣ውርጩ፣ዝናቡ፣ህመሙ፣ ፀሃይና ሀሩሩ ሳይበግረው እንደዚሁም የሙስሊሙ ህብረተሰባችን ሀገር ስትቀጥል ነው በዓልን ተረጋግቶ ማክበር የሚቻለው በማለት ምርጫውን በሰላማዊ መንገድ ሲያካሄድ በመዋሉ ከፍተኛ ምስጋና ይገባዋል ብለዋል። የወረዳችን የፀጥታ አካላት ከቅድመ ምርጫው ጀምሮ የምርጫ ቁሳቁስ በመጠበቅ፣በማጓጓዝ፣ እንደዚሁም በየምርጫ ጣቢያው የፀሃዩ ሙቀት፣ብርድና ውርጩን ችለው መኝታና ምግብ ሳይመቻችላቸው ከሁሉም ነገር ሀገር ትበልጣለች በማለት ካለምንም የፀጥታ ስጋትና ችግር ህዝቡ በሰላም መርጦ እንዲመለስ በማድረግ ላደረጉት አስተዋጽኦ ምስጋናቸውን ችረዋል!! በዘንድሮ የምርጫ ስራችን ላይ የታየው ሁለንተናዊ ድጋፍ፣ ጠንካራ ትብብርና መተጋገዝ የወረዳችን ሕዝብ ታላቅነትና አንድነት ዳግም ያስመሰከረ ሆኗል በመሆኑም በተደረገው ዘርፈ-ብዙ ድጋፍ የተሰማቸውን ታላቅ ክብርና ምስጋና በድጋሚ አቅርበዋል። ምርጫው በሰላም መጠናቀቁ የትግላችን መጀመሪያ እንጂ መድረሻችን አይደለም በቀጣይ ጊዜያትም ይህንን የሰላም አየር ተጠቅመን፣ በአሁኑ ወቅት ትኩረት በተሰጣቸውና እየተከናወኑ ባሉ ወቅታዊ የልማት አጀንዳዎቻችን ላይ ይበልጥ በማተኮር፣ ለውዷ ሀገራችን ብልፅግናና ለአካባቢያችን ዕድገት በጋራና በቁርጠኝነት እንድንተጋ ጥሪዬን አቀርባለሁ ብለዋል።

ከአዲስ አበባ ወደ ጉራጌ ዞን የኢደል-ዓድሃ የአረፋ በዓል ለማክበር ለምትመጡ እንግዶች በአዲስ አበባ አማራጭ የባስ የትራንስፖርት አገልግሎት እንድታገኙ የጉራጌ ዞን አስተዳደር ከፌደራል ትራንስፖርትና ሎጂስቲክ አገልግሎት ጋር በመቀናጀት ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል፦ በዚህም መሰረት ከግንቦት 16 /2018 ጀምሮ በአዲስ አበባ ባሶች የሚገኙበት ቦታዎች #በአየር ጤና #በሉካንዳ #በየሺ ደበሌ #በካራቆሬ #በቄራ #በጀሞ #በቤተል #በአለም ባንክ #በዘነበወርቅ #በሎሚ ሜዳ  #በላምበረትና በሁለቱ መናሀሪያዎች  ከግንቦት 16/2018 ዓመተ ምህረት ጀምሮ አገልግሎት የሚሰጡ ይሆናል። ለጉራጌ ዞን ለአረፋ በዓል ተጓዦች በሙሉ ከአዲስ አበባ መነሻና የጉራጌ ዞን ወረዳዎች መድረሻ ፣ ያደረገ የትራንስፖርት አገልግሎት የታሪፍ መጠን ይፋ የተደረገ ሲሆን ለሚፈጠሩ ቅሬታዎች ስልክ ቁጥሮች ተያይዘዋል። መረጃው የጉራጌ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ነው!!!

ግንቦት 11/2018 ዓ.ም የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ 7ተኛውን ጠቅላላ ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ አስመልክቶ በአረዳ ክላስተር ለ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚወዳደርበት ምልክት ማኒፌስቶና እጩዎችን የማስተዋወቅ እንዲሁም ይፋዊ የይምረጡኝ የቅስቀሳ ተካሄደ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ በአረዳ ክላስተር በኮኪር ምርጫ ክልል የሚወዳደሩ እጩዎቹ የምርጫ ምልክትና ማኒፌስቶ ለህዝብ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር በዛሬው እለት አካሂዷል። በዚህ የይምረጡኝ የቅስቀሳ መድረክ የማዕከላዊ ኢትዮጰያ ክልል መሬት አስተዳደር ኤጀንሲ ኃላፊ አቶ አብድልሀፊዝ ሁሴን፣ የጉራጌ ዞን ዋና አፈጉባኤ አቶ ኸይሩ መሀመድ፣ የጉራጌ ዞን ሴቶችና ህፃናት መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ነጅብያ ማህሙድ፣ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን፣ የገ/ጉ/ወ/ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ፈትያ መህዲን ጨምሮ የዞንና የወረዳ የስራ ኃላፊዎችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል። በዝርዝር ዜና እንመለሳለን።

ግንቦት 10/2018 ዓ.ም በመደመር እሳቤ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር የማድረስ ራዕያችንን ለማሳካት በ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በተግባር ማሳየት ይኖርብናል፦ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት እና 7ኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በማስመልከት በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ መሀል አምባ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳና የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል። በመድረኩ የተገኙት የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ እንደገለጹት፣ የኢኮኖሚ ሪፎርሙና የብልጽግና ጉዞ የዜጎችን ተጠቃሚነት ማዕከል ያደረገ ሲሆን፣ በዞኑ በተለይም በትምህርት፣ በግብርና፣ በጤና፣ በውሃና በመንገድ ልማት ዘርፎች በርካታ ውጤቶች ተመዝግበዋል። አክለውም በባህልና ቋንቋ፣ በከተሞች ልማት፣ በወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ፣ በገቢ ማሻሻያና በሌሎችም አበረታች የልማት ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል። በግብርና ዘርፍ ከ100 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ወደ እርሻ በማስገባት ከ5 ሚሊየን ኩንታል በላይ ተጨማሪ ምርት መገኘቱን ጠቁመዋል። እንዲሁም የጉራጊኛ ቋንቋ የትምህርት፣ የስራና የሚዲያ ቋንቋ እንዲሆን የተሰሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸው፣ ከ96 ሺህ በላይ ተማሪዎች በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው እየተማሩ መሆኑን አስታውቀዋል። በትምህርት ልማት ላይ ከ1 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ሰፊ ስራዎች መከናወናቸውንና አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ ተጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን ገልጸዋል። በተጨማሪም በንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ላይ ከ1 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ከ208 ሺህ በላይ ህዝብ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ መሆኑን አስገንዝበዋል። እንደ አቶ ላጫ ጋሩማ ገለጻ፣ ከ1 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ በማድረግ 1 ሺህ 213 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገዶች ተሰርተዋል። በዞኑ የተከናወኑ የልማት ስራዎች የዜጎችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት በማሳደግ ኢትዮጵያን ወደ ከፍታ እያሸጋገሯት መሆናቸውን ገልጸዋል አቶ ላጫ ጋሩማ። “በመደመር እሳቤ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር የማድረስ ራዕያችንን ለማሳካት በ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በተግባር ማሳየት ይኖርብናል” ሲሉም መልእክት አስተላልፈዋል። በመድረኩ የተገኙት የጉራጌ ዞን ሴቶችና ህጻናት ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ እና የፓርቲው የኮኪር ምርጫ ክልል የፓርላማ ተወካይ ወ/ሮ ነጅሚያ መሀመድ በበኩላቸው፣ ብልጽግና ፓርቲ ካለፉት ልምዶች መልካሙን ወስዶ፣ የጎደለውን በማሟላትና ስህተቶችን በማረም ለህዝብ ጥቅምና ለሀገር ለውጥ የሚተጋ ፓርቲ መሆኑን ገልጸዋል። ግንቦት 24 የነገዋን ውብና የበለጸገች ኢትዮጵያ ለመገንባት ቃል ኪዳናችንን የምናረጋግጥበትና ድጋፋችንን በተግባር የምናሳይበት ቀን በመሆኑ ሁሉም በእለቱ ወጥቶ ድምጹን እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበዋል። ፓርቲው ትውልድ ተሻጋሪ ስራዎችን በማከናወን ከሀገር አልፎ በዓለም ደረጃ የሚታወቁ ስራዎችን በመስራት የኢትዮጵያን ገናናነት ማስመስከሩን ጠቁመዋል። በመሆኑም እነዚህ አበረታች የለውጥ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉና ኢትዮጵያ ተምሳሌት ሀገር እንድትሆን በመደመር እሳቤ ምርጫውን ማሳካት የሁሉንም ዜጋ ትብብርና ርብርብ እንደሚጠይቅ ገልጸዋል። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን እንደገለጹት፣ በወረዳው የመንግስት፣ የባለሀብቶች፣ የተራዶ እና የበጎ አድራጊ ድርጅቶችን አቅም በማቀናጀት አመርቂ የልማት ስራዎች ተከናውነዋል። በተለይም በመንገድ፣ በመብራት፣ በትምህርት፣ በንጹህ መጠጥ ውሃና በጤና ዘርፍ ፕሮጀክቶች በመገንባትና በማስመረቅ የህዝቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ መቻሉን ገልጸዋል። ከዚህ በፊት በወረዳው አንድ ማዘጋጃ ቤት ብቻ ከነበረው አሁን ወደ 6 ማዘጋጃ ቤቶች ማደጉን የገለጹት አቶ ሚፍታ፣ ከተሞቹ ለኑሮ አመቺና ሳቢ እንዲሆኑ ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል። አክለውም በግብርና፣ በባህልና ቋንቋ፣ በወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ፣ በሰላምና ጸጥታ እንዲሁም በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዘርፎች አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን አብራርተዋል።