uz
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ko'proq ko'rsatish
1 063
Obunachilar
-224 soatlar
-77 kunlar
+130 kunlar
Postlar arxiv
“ብቃት” የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት ሶስተኛ ዙር የድሬዳዋ አስተዳደር አፈጻጸም በፌደራል የሱፐርቪዥን ቡድን ተገመገመ፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት በስሩ ከምገኙ የወረዳ አንድ ማዕከላት ከሚያስተባብሩ አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር የሶስተኛ ዙር በአጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም ላይ ከፌደራል በመጡ የሱፐርቪዥን ቡድን የተመላከቱ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመንቀስ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ማድረግ ተችሏል፡፡ በዚህም መድረክ ላይ ፕሮጀክቱ ባለፉት አመታት እንደ አስተዳደር ያስገኘውን ጠቀሜታ ከጅምሩ ሰልጣኞች በስልጠና ላይ ሆነው ከአመለካከት አንስቶ በኢንደስትሪዎች ተመድበው በሥራ ላይ ልምምድ እያደረጉ እስከሚገኝበት አሁናዊ ሁኔታ ወጣቶቹ እያሳዩ የሚገኙትን ለውጥ ቤተሰብ የመሰከረለት በሚሰሩበት ኢንደስትሪም በሥራ ላይ ልምምዱ ቋሚ ቅጥር እየፈጸሙ መሆኑ የሚያበረታታ መሆኑን የቢሮው ም/ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ገልጸዋል፡፡ በተያያዘ ወጣቶቹ የአቻ ለአቻ ውይይቶችንና መሰረታዊ የአይ.ሲ.ቲ እንዲሁም የህይወት ክህሎትና የሥራ አፈላለግ ስልጠናዎችን እንዲያገኙ የተደረገ መሆኑና ጥቂት የታዩ የመጠነ ማቋረጥ አዝማሚያዎችን ከኢንደስትሪዎቹ ጋር ተናቦና ተቀራርቦ ከፌደራል በተዘረጋው የድጋፍና ክትትል ስርዓት የፕሮጀክቱን ውጤታማነት ከዚህ በላይ ለማሳደግና ለማጠናቀቅ አቅጣጫዎች ተቀምጠው ወደ ስራ መገባቱ ታውቋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 24/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የ2018 ዓ.ም የአዲስ ገቢ ሰልጣኞች ቅበላ በመንግስትና በግል ኮሌጆች ላይ የትምህርት ማስረጃ ጥራትና አግባብነት የማረጋገጥ ሥራ መጀመሩ ተገለጸ፤ በዚህም በየአመቱ በአስተዳደሩ የሚገኙ ሁሉም የግልና የመንግስት ኮሌጆች የሰልጣኝ ቅበላ ሲያካሂዱ በተላለፈላቸው የአሰራር መመሪያ ማከናወኛ መሰረት ሲሆን ከዚህ በተለየ ኮሌጆች ለራሳቸው በሚያመቻቸው መንገድ ከተቀመጠላቸው መመሪያ ውጪ በሚገባ ባልተፈተሸና ባልተረጋገጠ ሀሰተኛ ማስረጃ ሰልጣኝ ከተቀበሉ በእነዚህ እና በሌሎች ምክንያት የሚፈጠሩ ክፍተቶችን በወቅቱ ለማረምና ለመቆጣጠር የትምህርት ማስረጃ ጥራትና አግባብነት የማረጋገጥ ሥራ የሚከናወን ይሆናል፡፡ በዋናነት ኤጀንሲው ባለው ስልጣንና በተሰጠው ኃላፊነት መሰረት ኮሌጆቹ ከመነሻው በወረደላቸው የቅበላ መመሪያ መሰረት ምዝገባ ማከናወናቸውን የማረጋገጥና ሰልጣኞች ያቀረቧቸው የትምህርት ማስረጃዎች ትክክለኛውን ከሀሰተኛው በመለየት ቅበላው በየደረጃው መቁረጫ ነጥብ መሆኑን ፈትሾ በሚገኙ ክፍተቶችና ከመመሪያ ውጪ በሆኑ አካሄዶች ላይ ፈጣንና አግባብነት ያለው የማስተካከያና የእርምት ስራዎችን ለመስራት አላማው አድርጎ የሚሰራ መሆኑ ታውቋል፡፡ በመሆኑም በመንግስትና በግል ኮሌጆች በ2018 ዓ/ም በአገር አቀፍ ደረጃ በተላለፈው የመቁረጫ ነጥብ መሠረት የ2018 ዓ.ም የአዲስ ገቢ ሰልጣኞች ቅበላ ላይ የትምህርት ማስረጃ ጥራትና አግባብነት ትክክለኛ መሆኑን በማረጋገጥ በተሰጣቸው ህጋዊ የማሰልጠን ፈቃድ ብቻ መስፈርቱን የሚያሟሉ ሰልጣኞችን በሞያ መስኩና ደረጃ መቀበላቸውን በተቀመጠው የቴ/ሙ/ት/ስ የስልጠና ጥራት ስታንዳርድ መሰረት መሆኑን በማስጠበቅና በማረጋገጥ ተቋማት ህግና ደንብን በሚገባ አክብረው እንዲሰሩ ኤጀንሲው ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃን በመቆጣጠር በህግ የተሰጠውን ተግባርና ኃላፊነት እንዲወጣ ያስችለዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 24/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአንድ ጀምበር ለ30 ሺህ ወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ ንቅናቄ አስጀመሩ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአንድ ጀምበር ለ30 ሺህ ወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ ንቅናቄን አስጀመሩ። ከንቲባዋ በንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ እንዳሉት፥ የከተማ አስተዳደሩ ወጣቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ በልዩ ትኩረት እየሰራ ይገኛል፡፡ ዛሬ የምንገነባው ትውልድ በክህሎትና በዕውቀት የበለጸገና ችግር ፈቺ እንዲሆን እየተጋን ነው ያሉት ከንቲባዋ፥ በአንድ ጀምበር ለ30 ሺህ ወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ መርሐ ግብር የዚህ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። በዚህም ወጣቶች ከዛሬ ጀምሮ በከተማ ግብርና፣ በኮንስትራክሽን፣ በንግድ፣ በአገልግሎትና በአምራች ዘርፎች ስራ ይጀምራሉ ነው ያሉት። በመዲናዋ የሚፈጠረው የስራ ዕድል ፈጠራ የስራ ገበያው በሚፈልገው ልክ እንዲሆን ለወጣቶች ስልጠና እየተሰጠ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። ከንቲባዋ ለወጣቶቹ የስራ መሳሪያ ስጦታዎችን ያበረከቱ ሲሆን፥ በቀጣይም በሚሰማሩበት የስራ መስክ ውጤታማ እንዲሆኑ አስፈላጊው ድጋፍ እንደሚደረግላቸው አረጋግጠዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማ አስተዳደሩ የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ሚሊዮን ማቴዎስ በበኩላቸው፥ በመዲናዋ የስራ አጥነትን ለመቀነስና ለስራ ዕድል ፈጠራ ያሉ ጸጋዎችን በጥናት በመለየት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በ2017 በጀት ዓመት ለ366 ሺህ ዜጎች የስራ ዕድል መፈጠሩን አስታውሰው፥ በ2018 ባለፉት አራት ወራት ብቻ ለ158 ሺህ ዜጎች ቋሚ የስራ ዕድል መፈጠሩን ጠቁመዋል። በመዲናዋ ለወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ የብድርና የመስሪያ ቦታ አቅርቦት ለማመቻቸት ከተማ አስተዳደሩ እየሰራበት እንደሚገኝም ነው የተናገሩት። በመዲናዋ ለክህሎት መር የስራ ዕድል ፈጠራ ትኩረት መሰጠቱን ጠቅሰው፥ በ14 የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት ወጣቶችን በማሰልጠን የስራ ዕድል እየተፈጠረ ይገኛል ብለዋል። በአዲስ አበባ ስታዲየም እየተካሄደ በሚገኘው የንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና የመርሐ ግብሩ ተጠቃሚ ነዋሪዎች ተገኝተዋል። አዲስ አበባ፣ ሕዳር 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ)

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከEDI ጋር በመተባበር ዘንድሮ ስልጠናቸውን ለሚያጠናቅቁ የኮሌጁ ሰልጣኝ ተማሪዎች ስራ ፈጣሪነት ላይ ያተኮረ የኢንተፕርነርሺፕ ስልጠና ሰጠ:: የኢንተርፕርነርሺፕ ስልጠናው ላለፉት 4 ቀናት በተቋሙ ሲሰጥ የቆየ ሲሆን ወጣቶች በኮሌጁ የሚኖራቸውን ቆይታ አጠናቀው ሲወጡ ኢንዱስትሪውን ከማንቀሳቀስ ባሻገር በሰለጠኑበት የሙያ ዘርፍ የቢዝነስ ሀሳቦችን በማፍለቅ እንዴት የራሳቸውን ስራ መፍጠርና ኢኮኖሚውን መምራት እንደሚችሉ ሰፊ ግንዛቤ ያገኙበትን ስልጠና ለወጣቶቹ መስጠት ተችሏል:: በስልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ ለሰልጣኞች መልዕክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በንግግራቸው ስልጠና አጠናቃቂ ወጣቶች የቀጣይ ህይወታችሁን ምዕራፍ የምትወስኑበት ወሳኝ ጊዜ ላይ እንደመሆናችሁ መጠን ከወዲሁ ስራ ፈጣሪነትን እንድትላበሱ ታስቦ የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ገልፀው በተለይ እንደ ቴክኒክና ሙያ ሰልጣኝ ሀገር መቀየር የሚችሉና በየዘርፉ ለሚስተዋሉ ክፍተቶች መፍትሄ የሚሆኑ የቢዝነስ ሀሳቦችን በማመንጨት ስራ ፈጣሪ ዜጋ መሆን ይጠበቅባችኃልም ብለወዋል:: ሰልጣኞች ወደ ስራ አለም ከመግባታችሁ አስቀድሞ ይህን የስራ ፈጣሪነት ስልጠናን በማግኘታችሁ እድለኛ ያደርጋችኃል ያሉት ደግሞ የኮሌጁ የቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አ ዋና ስራ ሂደት ሀላፊና ም/ል ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ አያይዘውም የተሻለ የቢዝነስ ሀሳብ ይዘው ለሚመጡ ወጣቶች በኮሌጁ የኢንኩቤሽን ሴንተር በኩል አስፈላጊውን ትብብርና ድጋፍ ለማድረግ ኮሌጁ ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ መሆኑንም ገልፀዋል:: ላለፉት 4 ቀናት ለስልጠና አጠናቃቂ ወጣቶች የተሰጠውን የኢንተፕርነሺፕ ስልጠና ኮሌጁ ከEDI(Ethiopian Development Inistitut) ጋር በመተባበር ያዘጋጀ ሲሆን የስራ ፈጣሪነት ስልጠናውም ከEDI በመጡ ባለሙያዎች መስጠት ተችሏል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ህዳር 20/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

“በጋራ እንገንባ/ Together We Build!” ዓለም አቀፍ የኢንተርፕረነርሺፕ ሳምንት የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሺፕ ሳምንት በማስመልከት በዛሬው ዕለት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሄደ። ‘‘በጋራ እንገንባ’’ በሚል መሪ ቃል ሁለት መቶ በሚሆኑ የአለም ሀገራት በተለያዩ ሁነቶች ሲከበር የነበረው የአለም ኢንተርፕረነርሺፕ ሳምንት በድሬዳዋ አስተዳደር ደረጃ  ዘርፍ መስሪያ ቤት ተወካዮች በተገኙበት ሰነድ ቀርቦ የፓናል ውይይት ማድረግ ተችሏል፡፡ በመድረኩ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍና ስራ ፈጣሪዎች ተቀናጅተው እንዲሰሩ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን በተመለከተ ውይይት የተደረገ ሲሆን በዋናነትም የወጣቱን በስራ ዕድል ተጠቃሚነት መረጋገጥ ረገድ ያሉ ማነቆዎች ላይ ትኩረት ተሰጥቶታል። የቢሮው ም/ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በመድረኩ ተገኝተው እንደተናገሩት ስራ ፈጣሪዎች ከተለምዷዊ አሰራር ተላቀው ንቁ፣ ችግር ፈቺና የስራ ዕድል ፈጣሪ እንዲሆኑ በቅንጅት መስራት ይገባል ብለዋል። አያይዘውም በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ማስተባባሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ እንደገለጹት በአስተዳደሩ የተለያየ ክህሎት ያላቸው ዜጎች እውቀታቸውን ወደ ተግባር የሚቀይሩበት ምህዳር በማዘጋጀትና ከፋይናንስ ተቋማት በማገናኘት ድጋፍ እንዲያገኙ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 19/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለሀገር የሚጠቅሙ ዜጎችን ለማፍራት ስራችን ዘመናዊ በሆነ መልኩና ሰልጣኞችን በስነ ምግባር የታነጹ ዜጎች እንዲሆኑ እየሰራ እንዳለ ተገለጸ፡፡ 22ተኛው የአለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ትውልድን በስነ-ምግባር ተቋምን በአሰራር በሚል መሪ ቃል በፓናል ውይይት ተከበረ፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ በመገኘት መድረኩን በንግግር የከፈቱትና በተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄና አስተያየቶች ምላሽ የሰጡት የኮሌጁ ኢ/ኤ/ቴ/ሽግግር ም/ዲን የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በዙ ሲሆኑ በንግግራቸውም ኮሌጃችን የትምህርትና ስልጠና ተቋም እንደ መሆኑ መጠን አሰራራችንን በማዘመን ሰልጣኞቻችንን አገር ወዳድ ሆነው እንዲወጡ በስነ ምግባር እንዲታነጹ አብረን በጋራ መስራት አለብን ያሉ ሲሆን፣ ወ/ሮ ትግስት አያይዘውም የዘመነ አሰራር ተከትለን ስራዎቻችንን መስራት እንዳለብን ሁሉ የተቋሙን እሴትና የስነ ምግባር መርህ ተከትለን ህዝብን በቅንነትና በታማኝነት ልናገለግል ይገባንል ብለዋል፡፡ በዛሬው እለት በኮሌጁ የተከበረው 22ተኛው የአለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ህዳር 19/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ