Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
Kanalga Telegram’da o‘tish
Ko'proq ko'rsatish
1 068
Obunachilar
+224 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
+230 kunlar
Postlar arxiv
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአብይ ፆምን እና የረመዳን ወር ጾምን ምክንያት በማድረግ ማዕድ አጋራ::
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የታላቁን አብይ ፆምን እና የታላቁን ረመዳን ወር ጾምን ወቅትን ምክንያት በማድረግ ለተለያዩ ማህበረሰብ አካላቶች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት በቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያንና በኮሌጁ ግቢ ውስጥ ማዕድ አጋርቷል።
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከመማር ማስተማር ሂደቱ በዘለለ ማህበረሰባዊ እሴቶች ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና የመደጋገፍ እና የመረዳዳት ባህልን ለማጠናከር ይሰራል ያሉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ አያይዘውም በጾሙ ወቅት ስንሰራቸው የነበሩ በጎቶች ከጾሙ ውጪም ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ብለዋል፡፡በመጨረሻም ለዚህ መርሃ ግብር መሳካት አስተዋጽኦ ላላቸው ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በመርሀ ግብሩ ላይ ተሳታፊ የሆኑት አካላቶች ለታላቁ የረመዳን ወርና ለአብይ ፆም እንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን በማስተላለፍ እርስ በእርስ የመረዳዳትና የመዳጋገፍ ባህልን ማዳበር እንደሚገባና ይህንንም ተግባር የኮሌጁ ማህበረሰብ ማስቀጠል እንደሚገባቸው እንዲሁም ይህንን ተግባር ሌሎችም አካላቶች ሊከተሉትና እንደ አርአያ ወስደው ሊተገብሩት እንደሚገባ ተናግረዋል አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
መጋቢት 19/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአብይ ፆምን እና የረመዳን ወር ጾምን ምክንያት በማድረግ ማዕድ አጋራ::
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የታላቁን አብይ ፆምን እና የታላቁን ረመዳን ወር ጾምን ወቅትን ምክንያት በማድረግ ለተለያዩ ማህበረሰብ አካላቶች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት በቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያንና በኮሌጁ ግቢ ውስጥ ማዕድ አጋርቷል።
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከመማር ማስተማር ሂደቱ በዘለለ ማህበረሰባዊ እሴቶች ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና የመደጋገፍ እና የመረዳዳት ባህልን ለማጠናከር ይሰራል ያሉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ አያይዘውም በጾሙ ወቅት ስንሰራቸው የነበሩ በጎቶች ከጾሙ ውጪም ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ብለዋል፡፡በመጨረሻም ለዚህ መርሃ ግብር መሳካት አስተዋጽኦ ላላቸው ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በመርሀ ግብሩ ላይ ተሳታፊ የሆኑት አካላቶች ለታላቁ የረመዳን ወርና ለአብይ ፆም እንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን በማስተላለፍ እርስ በእርስ የመረዳዳትና የመዳጋገፍ ባህልን ማዳበር እንደሚገባና ይህንንም ተግባር የኮሌጁ ማህበረሰብ ማስቀጠል እንደሚገባቸው እንዲሁም ይህንን ተግባር ሌሎችም አካላቶች ሊከተሉትና እንደ አርአያ ወስደው ሊተገብሩት እንደሚገባ ተናግረዋል አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
መጋቢት 19/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ላይ ያተኮረ የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድር ተካሄደ፤
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱሰትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ችግር ፈቺ የሆኑ ጥናትና ምርምሮችን በዘርፉ የሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን እና ባለሙያዎች እንዲሰሩ ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ድጋፍ እንደሚያደርግ ይታወቃል፡፡
በዚህም በዘርፉ ላይ በተለይም በኮሌጆች ላይ በአሰልጠኝ መምህሩ የሚነሱ ጥያቄዎች እና በሰልጣኝ ተማሪዎች ላይ የሚስተዋሉ መፍትሄ የሚሹ ጉዳዮች ማለትም አውቶሜትድ የተማሪዎች አቴንዳንስ ማኔጅመንት ሲስተም፣ ከጤና እና ደህንነት አጠባበቅ፣ የቢዝነስ ፕላን ጥራትና ውጤት ማሻሻል፣ የተሽከርካሪ የቴክኒክ ብቃት ምርመራ(ቦሎ) እና የማህበረሰብ ድጋፍ ላይ ትኩረታቸውን ያደረጉ ጥናቶች ቀርበው ውድድር የተካሄደ ሲሆን ከተወዳዳሪዎችም አንደኛ ሆኖ ያጠናቀቀው በአገር አቀፍ ደረጃ ለሚካሄደው ውድድር ድሬዳዋን ወክሎ የሚሳተፍ ይሆናል፡፡
ይህም ውድድር በዋነኛነት ለዘርፉ ችግር ፈቺ የሆኑ ሃሳቦች በማፍለቅ አሰራሮችን ለማሻሻል እና ለመከለስ በግብዓት የሚየገለግሉ እንደሚሆኑና ተወዳዳሪዎች በኮሌጆቻቸው በተግባር ፈትነው ያቀረቧቸው እነዚህ ተግባራዊ ጥናትና ምርምሮች ለዘርፉ መሻሻልና ማደግ ከፍተኛ ሚና የሚጫወቱ ይሆናል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 18/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
"የመጋቢታዊያን የለውጥ ፍሬዎችና የነገ ተስፋዎች" በሚል መሪ ቃል የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የብልፅግና ህብረት አባላት የውይይት መድረክ አካሄዱ።
በለውጡ ሂደት ውስጥ የተሰሩ ሰው ተኮር ስራዎች፣ የተፈቱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን፣ የልማት ስራዎች ውጤታማነት እና ሌሎችንም መሰል ዝርዝር ሀሳቦችን በመድረኩ ማብራሪያ ተሰቶባቸዋል።
የመጋቢት ወር በኢትዮጵያ ፖለቲካ ልዩ ልዩ ታሪካዊ ኩነቶችን ያሳለፈ እንደሆነና ፓርቲው ከምስረታው ጀምሮ አበይት ጉዳዮች የተከናወኑበት መሆኑን የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በመግለፅ በኢትዮጵያ ራስን የመቻል ልዕልና ውሳኔ ማሳያ የሆነው የታላቁ የህዳሴ ግድብ የመሠረት ድንጋይ የተጣለበትና የማጠናቀቂያ ዋዜማ ታሪካዊ ወር መሆኑን ተናግረዋል።
በመድረኩ "የመጋቢታዊያን የለውጥ ፍሬዎችና የነገ ተስፋዎች" ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 18/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
"የአንድ ማዕከላትን አቅም ማጎልበትና ተልዕኳቸውን በሚጠበቀው ልክ እንዲፈጽሙ መከታተልና መደገፍ በቢሮው ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ነው"
አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ
በዛሬው ዕለት በአስተዳደሩ ከተማና ገጠር የሚገኙ የአንድ ማዕከላትን ከሚያስተባብሩ አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር በአጠቃላይ የሥራ ዕድል ፈጠራ አፈጻጸምና ቀጣይ ትግበራ ላይ ሰፊ ውይይት ተካሄደ፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የተሰጠውን ሀገራዊና አስተዳደራዊ ተልዕኮዎችን ወደ ተግባር ለውጦ ውጤት ለማምጣት የአንድ ማዕከላት ሚና ላቅ ያለ ሲሆን በተለይም ቢሮው በስራ ዕድል ፈጠራ የዜጎችን ስራ አጥነት ለመቀነስ በሚደረገው ሁሉን አቀፍ እርብርቦሽ የአንድ ማዕከላቱ በቀጥታ ከህብረተሰቡ ጋር በመገናኘት ምቹ ሁኔታዎች እንዲፈጠሩ ያስቻሉ መሆኑን አቶ ሮቤል ጌታቸው ተናግረዋል።
በተጨማሪም አንድ ማዕከላቱ እንደ አስተዳደር የሚሰጡ ተልዕኮዎችን በጋራ እና በተናጠል ተከፋፍለው የሚፈጽሙበት ሁኔታና አግባብነትን በተጠናከረ መልኩ ከማስቀጠልና የሚታዩ ክፍተቶችን በማረም የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት በብቃት እንዲወጡ ያሳሰቡ ሲሆን በቀጣይ በተለይ የገጠሩን ሥራ ዕድል ፈጠራ ከማጠናከር አኳያ አደረጃጀቱን የማጠናከርና የአቅም ግንባታ ስራዎች ትኩረት እንደተሰጣቸውና በተያያዘ በቀጣይ ቢሮው በድጋፍና ክትትል የሁሉንም አንድ ማዕከላት ውጤታማነት ማረጋገጥ የሚያስችል አቅጣጫ ማስቀመጡን ገልጸዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 17/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
"የአንድ ማዕከላትን አቅም ማጎልበትና ተልኳቸውን በሚጠበቀው ልክ እንዲጽሙ መከታተልና መደገፍ በቢሮው ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ነው"
አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ
በዛሬው ዕለት በአስተዳደሩ ከተማና ገጠር የሚገኙ የአንድ ማዕከላትን ከሚያስተባብሩ አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር በአጠቃላይ የሥራ ዕድል ፈጠራ አፈጻጸምና ቀጣይ ትግበራ ላይ ሰፊ ውይይት ተካሄደ፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የተሰጠውን ሀገራዊና አስተዳደራዊ ተልዕኮዎችን ወደ ተግባር ለውጦ ውጤት ለማምጣት የአንድ ማዕከላት ሚና ላቅ ያለ ሲሆን በተለይም ቢሮው በስራ ዕድል ፈጠራ የዜጎችን ስራ አጥነት ለመቀነስ በሚደረገው ሁሉን አቀፍ እርብርቦሽ የአንድ ማዕከላቱ በቀጥታ ከህብረተሰቡ ጋር በመገናኘት ምቹ ሁኔታዎች እንዲፈጠሩ ያስቻሉ መሆኑን አቶ ሮቤል ጌታቸው ተናግረዋል።
በተጨማሪም አንድ ማዕከላቱ እንደ አስተዳደር የሚሰጡ ተልዕኮዎችን በጋራ እና በተናጠል ተከፋፍለው የሚፈጽሙበት ሁኔታና አግባብነትን በተጠናከረ መልኩ ከማስቀጠልና የሚታዩ ክፍተቶችን በማረም የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት በብቃት እንዲወጡ ያሳሰቡ ሲሆን በቀጣይ በተለይ የገጠሩን ሥራ ዕድል ፈጠራ ከማጠናከር አኳያ አደረጃጀቱን የማጠናከርና የአቅም ግንባታ ስራዎች ትኩረት እንደተሰጣቸውና በተያያዘ በቀጣይ ቢሮው በድጋፍና ክትትል የሁሉንም አንድ ማዕከላት ውጤታማነት የሚያረጋገጥ አቅጣጫ ማስቀመጡን ገልጸዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 17/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት ለኮሌጁ የድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች ሲሰጥ የቆየው የ3ኛዙር የአቅም ግንባታ ስልጠና ተጠናቀቀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ከድሬዳዋ ስራ አመራር ኢንስቲትዩት ጋር በጋራ ለመስራት በገባው ውል መሰረት ለ3ኛ ዙር ለኮሌጁ የፅዳትና ጥበቃ ሰራተኞች ለተከታታይ 3 ቀናት ሲሰጥ የቆየው የአቅም ግንባታ ስልጠና በዛሬው እለት ተጠናቋል::
ለ3 ተከታታይ ቀናት የተሰጠውን ስልጠና በአግባቡ ተከታትለው ላጠናቀቁ ሰልጣኞች ምስጋና ያቀረቡት የድሬዳዋ ስራ አመራር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አወቀ ለገሰ አክለውም ኮሌጁ ሰራተኞች በስራ ገበታቸው ላይ የሚሰጡት አገልግሎት እንዲሻሻል በማቀድ ይህንና መሰል ስልጠናዎችን እንዲወስዱ ማመቻቸቱ የሚበረታታ ነውም ብለዋል::
በዚህ 3ኛ ዙር ስልጠና ላይ የተካፈሉ ሰልጣኞች የወሰዱትን ስልጠና በተግባር ላይ ማዋል የሚጠበቅባቸው መሆኑን የገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አክለውም በቀጣይ በሚፈጠርላቸው መሰል የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች ላይ በንቃት በመሳተፍ አቅማቸውን እንዲገነቡና በተመደቡበት የስራ ዘርፍ የተሻለ አገልግሎት በመስጠት ለተቋሙ ራዕይና ስኬት የድርሻቸውን እንዲወጡም ጠይቀዋል::
ሰልጣኞች ከዚህ ስልጠና በኃላ በስራ ገበታችሁ ላይ ያመጣውን ለውጥ በተግባር እንድታሳዩ ያስፈልጋል ያሉት የኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ስራ ሂደት ም/ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ አክለውም በመሰል ስልጠናዎች የሚመዘገቡ ውጤቶችን በድጋፍና ክትትል እናረጋግጣለንም ብለዋል::
የ3ኛው ዙር ስልጠና ቀደም ብለው ከተሰጡት የ1ኛና 2ኛ ዙር ስልጠናዎች በተለያየ ምክንያት ዘግይቶ እንደተሰጠ ያስታወሱት የEASE ፕሮጀክት ዋና አስተባባሪ የሆኑት ኢንጂነር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ አክለውም ይህ ስልጠና ማስጀመርያ መሆኑንና ኮሌጁ ከኢንስቲትዩቱ ጋር በቅንጅት ለመስራት ባደረገው ስምምነት መሰረት አስፈላጊ የሆኑ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች በቀጣይ እንደሚዘጋጁም ገልፀዋል::
የማጠቃለያ መርሃ-ግብሩ ላይ ስልጠናውን በአግባቡ ተከታትለው ላጠናቀቁ ሰልጣኞችም ከእለቱ ክብር እንግዶች የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
መጋቢት17/2017 ዓ.ም
"ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች" በሚል መሪ ሃሳብ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት የሚካሄደው የ2017 ዓ.ም የክህሎት ውድድር በክላስተር ደረጃ መካሄድ ጀመረ።
በዛሬው ዕለት በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እና በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች በጋርመንት፣ ዉድ ወርክ፣ ኤሌክትሪክ፣ ሆቴል እና ቱሪዝም፣ ኮንስትራክሽን፣ አውቶሞቲቭ፣ ማኑፋክቸሪንግ እና በአይሲቲ ላይ ሰልጣኝ ተማሪዎች በአስተዳደር ደረጃ ለሚካሄደው ውድድር ኮሌጃቸውን ወክለው ለመሳተፍ ከየዘርፉ በተመረጡ ዳኞች ፊት ክህሎታቸውን በመጠቀም ስራዎቻቸውን በማቅረብ ላይ ይገኛሉ።
በዚህም በክላስተርና በአስተዳደር ያለውን ውድድር በበላይነት የሚያጠናቅቁ ተወዳዳሪዎች ኮሌጆቹን እንዲሁም አስተዳደሩን በመወከል በአገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄደው የክህሎት ውድድር የሚሳተፉ እንደሚሆን በዳይሬክቶሬቱ የቴክኒካል ክህሎት አቅም ግንባታ ቡድን መሪ ወ/ሮ አለምጸሃይ ጌታቸው ገልጸዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 16/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
