Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
Kanalga Telegram’da o‘tish
Ko'proq ko'rsatish
1 089
Obunachilar
+324 soatlar
+257 kunlar
+1730 kunlar
Postlar arxiv
ህገወጥ የሰዎችን ዝውውርን ለመከላከል እና ህጋዊ የስራ ስምሪትን ለመዘርጋት የህብረተሰብ በተለይም የሴቶችና ወጣቶችን ትኩረት ያደረጉ ግንዛቤ ፈጠራዎች ውጤት እንደሚያስገኙ ተገለጸ፤
በድሬዳዋ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የውጪ አገር ስራ ስምሪትና የሰራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት በተለያዩ አዋጆች ዙሪያ ከአስተዳደሩ ዘጠኙም የከተማ ቀበሌዎች ለተወጣጡ ሴቶችና ወጣቶች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጀ።
በመድረኩም ተሳታፊ ለሆኑ በሰዎች መነገድ፣ ሰዎችን በህገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር እና ለስራ ወደ ውጭ ሀገር መላክ ወንጀል አዋጅ ቁጥር 1178/2012 እና ህጋዊ የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት አዋጅ ቁጥር 1246/2013 ላይ ግንዛቤ የሚያስጨብጣቸውን ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋ።
በዚህም አዋጆቹን በመረዳት በሰዎች የመነገድ፣ በህገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር እና በህገወጥ መንገድ ለስራ ወደውጭ ሀገር መላክ ወንጀልን በመከላከል ረገድ የህብረተሰቡን በተለይም የሴቶችንና የወጣቶችን ግንዛቤ ማሳደግ ዓላማው አድርጎ ከዚህ ጎን ለጎን ህጋዊው የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት አካሄድ ላይ ገለፃ ተደርጎላቸዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 8/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
‹‹የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል እንደ መሆኑ መጠን ከምስራቅ አፍሪካ የሚመጡ ተማሪዎችን በመቀበል እና አሰልጥኖ በማብቃት ለቀጠናው ትስስር ከፍተኛውን ሚና እየተጫወተ ይገኛል።››
አቶ ሳሊም ኡስማን
የኮሌጁ ዲን
****
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከሶማሌ ላንድ የመጡ 10 ሰልጣኞችን በኤሌክትሪክ ኢንስታሌሽንና ፍሪጅ ጥገና እንዲሁም በICT የሞያ መስኮች ተቀብሎ ማሰልጠን ጀመረ፡፡
ስልጠና ማስጀመሪያው ላይ ንግግር ያደረጉት እና ለሰልጣኞች ደግሞ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን ሲሆኑ ዲኑ በንግግራቸውም ትምህርት እና ስልጠና ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ እድገት ቁልፍ መሳሪያ ነው። ይህን መሳርያ ደግሞ ለከተማችን ወጣቶች ብቻ ሳይሆን ለምስራቅ አፍሪካ ወጣቶችም ማድረስ ይኖርብናል፡፡ለዚህም በዛሬው እለት በኤሌክትሪክ ኢንስታሌሽንና በICT የሞያ መስኮች ስልጠና ለመከታተል በኮሌጃችን የተገኙት የሶማሌ ላንድ ዜግነት ያላቸው ወጣቶች አንዱ ማሳያው ናቸው ብለዋል፡፡ የኮሌጁ ዲን በማስቀጠል የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የምስራቅ አፍሪካ ተማሪዎችን በመቀበል እና አሰልጥኖ በማብቃት ለቀጠናው ትስስር ከፍተኛውን ሚና እየተጫወተ ይገኛል። በቀጣይም ከሌሎች የምስራቅ አፍሪካ ሀገሮች የተለያዩ ሰልጣኞችን በመቀበል የምስራቅ አፍሪካን በትምህርትና ስልጠናው የማዋሃድ ስራን የሚሰራ ይሆናል፡፡ ያሉ ሲሆን በመጨረሻም ወደ ምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ወደሆነው ኮሌጃችን በደህና መጣችሁ በሚኖራችሁ ቆይታ ሁሉ የኮሌጁ ማኔጅመንት ከጎናችሁ እንደሚሆን ለመግለጽ እወዳለሁ ብለዋል፡፡
በመቀጠልም ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ም/ዲንና የውጤት ተኮር ትምርትና ስልጠና ኃላፊ የሆኑት አቶ ሰልሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ በንግግራቸውም እንኳን የፍቅር ተምሳለሌት ወደሆነችው ትንሿ ኢትዮጵያ ድሬዳዋ ከተማ እና የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ወደሆነው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በደህና መጣችሁ ፡፡ ድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከጎረቤት ሀገራት ሶማሌላንድ፣ ከሶማሊያ፣ጅቡቲ፣ከኬንያ፣ከታንዛንያ እንዲሁም ከሌሎች የምስራቅ አፍሪካ ሃገራት ጋር በትምህርትና ስልጠና ለማዋሃድ በንቃት ሲሰራ መቆየቱ የሚታወስ ነው ያሉ ሲሆን አያይዘውም በዛሬው እለት ስልጠናችሁን የጀመራችሁ የሶማሌ ላንድ ሰልጣኝ ተማሪዎች ለዚህ ውህደት ማሳያ ናችሁ ብለዋል፡፡ከዚህ ኮሌጅ ስልጠናችሁን ጨርሳችሁ ወደ ሀገራችሁ ስትሄዱ በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ያገኛችሁትን ስልጠና ሌሎች ወጣቶች እንዲያገኙ የአባሳደርነት ሚናችሁን እንድትወጡ አደራ እላለሁ ብለዋል፡፡
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከዚህ ቀደም ከ18 በላይ የምስራቅ አፍሪካ ሰልጣኞችን ተቀብሎ ማሰልጠኑና ለምርቃት ማብቃቱ የሚታወስ ሲሆን የአሁኑ ስልጠና ለሁለተኛ ጊዜ የሚደረግና አብዛኛው ስራ ማለትም የምግብ፣የመኝታ ወጪን ኮሌጁ ሸፍኖ እያሰለጠነ ይገኛል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጥር 8/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
‹‹የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል እንደ መሆኑ መጠን ከምስራቅ አፍሪካ የሚመጡ ተማሪዎችን በመቀበል እና አሰልጥኖ በማብቃት ለቀጠናው ትስስር ከፍተኛውን ሚና እየተጫወተ ይገኛል።››
አቶ ሳሊም ኡስማን
የኮሌጁ ዲን
****
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከሶማሌ ላንድ የመጡ 10 ሰልጣኞችን በኤሌክትሪክ ኢንስታሌሽንና በICT የሞያ መስኮች ተቀብሎ ማሰልጠን ጀመረ፡፡
ስልጠና ማስጀመሪያው ላይ ንግግር ያደረጉት እና ለሰልጣኞች ደግሞ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን ሲሆኑ ዲኑ በንግግራቸውም ትምህርት እና ስልጠና ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ እድገት ቁልፍ መሳሪያ ነው። ይህን መሳርያ ደግሞ ለከተማችን ወጣቶች ብቻ ሳይሆን ለምስራቅ አፍሪካ ወጣቶችም ማድረስ ይኖርብናል፡፡ለዚህም በዛሬው እለት በኤሌክትሪክ ኢንስታሌሽንና በICT የሞያ መስኮች ስልጠና ለመከታተል በኮሌጃችን የተገኙት የሶማሌ ላንድ ዜግነት ያላቸው ወጣቶች አንዱ ማሳያው ናቸው ብለዋል፡፡ የኮሌጁ ዲን በማስቀጠል የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የምስራቅ አፍሪካ ተማሪዎችን በመቀበል እና አሰልጥኖ በማብቃት ለቀጠናው ትስስር ከፍተኛውን ሚና እየተጫወተ ይገኛል። በቀጣይም ከሌሎች የምስራቅ አፍሪካ ሀገሮች የተለያዩ ሰልጣኞችን በመቀበል የምስራቅ አፍሪካን በትምህርትና ስልጠናው የማዋሃድ ስራን የሚሰራ ይሆናል፡፡ ያሉ ሲሆን በመጨረሻም ወደ ምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ወደሆነው ኮሌጃችን በደህና መጣችሁ በሚኖራችሁ ቆይታ ሁሉ የኮሌጁ ማኔጅመንት ከጎናችሁ እንደሚሆን ለመግለጽ እወዳለሁ ብለዋል፡፡
በመቀጠልም ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ም/ዲንና የውጤት ተኮር ትምርትና ስልጠና ኃላፊ የሆኑት አቶ ሰልሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ በንግግራቸውም እንኳን የፍቅር ተምሳለሌት ወደሆነችው ትንሿ ኢትዮጵያ ድሬዳዋ ከተማ እና የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ወደሆነው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በደህና መጣችሁ ፡፡ ድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከጎረቤት ሀገራት ሶማሌላንድ፣ ከሶማሊያ፣ጅቡቲ፣ከኬንያ፣ከታንዛንያ እንዲሁም ከሌሎች የምስራቅ አፍሪካ ሃገራት ጋር በትምህርትና ስልጠና ለማዋሃድ በንቃት ሲሰራ መቆየቱ የሚታወስ ነው ያሉ ሲሆን አያይዘውም በዛሬው እለት ስልጠናችሁን የጀመራችሁ የሶማሌ ላንድ ሰልጣኝ ተማሪዎች ለዚህ ውህደት ማሳያ ናችሁ ብለዋል፡፡ከዚህ ኮሌጅ ስልጠናችሁን ጨርሳችሁ ወደ ሀገራችሁ ስትሄዱ በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ያገኛችሁትን ስልጠና ሌሎች ወጣቶች እንዲያገኙ የአባሳደርነት ሚናችሁን እንድትወጡ አደራ እላለሁ ብለዋል፡፡
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከዚህ ቀደም ከ18 በላይ የምስራቅ አፍሪካ ሰልጣኞችን ተቀብሎ ማሰልጠኑና ለምርቃት ማብቃቱ የሚታወስ ሲሆን የአሁኑ ስልጠና ለሁለተኛ ጊዜ የሚደረግና አብዛኛው ስራ ማለትም የምግብ፣የመኝታ ወጪን ኮሌጁ ሸፍኖ እያሰለጠነ ይገኛል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጥር 8/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
የሁለተኛ ሩብ አመት የ EASTRIP ፕሮጀክት የህንጻ ግንባታ አፈጻጸም በክብርት ወ/ሮ አይናለም ተዘራ የተመራ ከድሬዳዋ ምክር ቤት የተወውጣጣ የSupervision team በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግምገማ አከናወነ፡፡
በዚህም ቡድኑ በምልከታውም ኮሌጁ ወስጥ እየተገነባ ያለውን የ EASTRIP ፕሮጀክት የህንጻ ግንባታ በግማሽ አመቱ የተከናወኑ በርካታ ሥራዎች መመልከት የቻለ ሲሆን የተሰሩ ስራዎችን መረጃ በአግባቡ በማደራጀት እረገድም ጥሩና ከዚህ በበለጠ እያጠናከሩ መሄድ እንደሚገባ ያስገነዘቡ ሲሆን የድጋፋዊ ክትትሉም አላማ ኮሌጁ በግማሽ አመት ያከናወናቸውን ተግባራት አፈፃፀም በመገምገም ግብረ መልስ ለመስጠት ያለመ መሆኑ በምልከታው ወቅት ተገልጿል፡፡
የSupervision team የመሩት ክብርት ወ/ሮ አይናለም ተዘራ እንዳሉት ኮሌጁ በበጀት አመቱ ከዝግጅት ምእራፍ እስከ ትግበራ ምእራፍ ድረስ የተሰሩ ስራዎች መልካም ናቸው በተጨማሪም የ EASTRIP ፕሮጀክት የህንጻ ግንባታ የተሻለ አፈጻጸም እንዲያስመዘግብ ኮሌጁ እንዲሁም የፕሮጀክቱ ፈጻሚዎች በትጋትና በጥንቃቄ መስራት እንደሚገባቸው አቅጣጫ ያስቀመጡ ሲሆን በቀጣይም በኮሌጁ ያሉ ጠንካራ አፈጻጸሞችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንዲሁም በኮሌጁ ውስጥ እየተገነባ የሚገኘውም የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት መአከል ግንባታ በከፍተኛ ፍጥነት ተከናውኖ ለሚፈለገው አላማ መዋል እንዲችል በትጋት ምስራት ይኖርበታል ብለዋል ፡፡በተጨማሪም ፕሮጀክቱ በሚተገበርበት ወቅት በከተማ አስተዳደሩና በኮሌጁ ማኔጅመንት የሚወሰዱት የመፍትሄ እርምጃዎች ለሌሎች ኮሌጆች እንደ መልካም ተሞክሮ የሚወሰድ ነው ብለዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ታህሳስ 3/05/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
በድሬዳዋ የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የውጪ አገር ሥራ ስምሪትና የሰራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት ለአሰሪና ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጀ።
የስልጠና መድረኩ የሥራ ቦታ ማህበራዊ ምክክር በአዋጅ 1156 በሕብረት ድርድር ዙሪያ ሲሆን በይበልጥ ትኩረቱን በሥራ ቦታ ማህበራዊ ምክክር ያደረገና በአሰራና ሠራተኛ መካከል የሚከሰቱ ግጭቶችን ለማስቀርትና ምርታማነት ለማሳደግ የሥራ ቦታ ማሕበራዊ ምክክር የሚጫወተውን ሚና ለማስገንዘብ ያለመ ነው።
በመድረኩም ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ለተወጣጡ አሰሪና ሰራተኞች በሁለትዮሽ ማህበራዊ ምክክር ዝርጋታ እና በአሰሪና ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ላይ ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል።
በዚህም አዋጁን በመረዳት የአሰሪውንና ሰራተኛውን ግንዛቤ ማሳደግ ዓላማው አድርጎ ከዚህ ጎን ለጎን የኢንዱስትሪውን ሰላም በማረጋገጥ ምርታማነትን ለማሳደግ የሚኖሩ አለመግባባቶችን በመቀነስ የስራ ክርክሮችን በምክክር መፍታት የሚያስችላቸው ይሆናል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 2/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በድሬዳዋ የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የውጪ አገር ሥራ ስምሪትና የሰራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት ለአሰሪና ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጀ።
የስልጠና መድረኩ የሥራ ቦታ ማህበራዊ ምክክር በአዋጅ 1156 በሕብረት ድርድር ዙሪያ ሲሆን በይበልጥ ትኩረቱን በሥራ ቦታ ማህበራዊ ምክክር ያደረገና በአሰራና ሠራተኛ መካከል የሚከሰቱ ግጭቶችን ለማስቀርትና ምርታማነት ለማሳደግ የሥራ ቦታ ማሕበራዊ ምክክር የሚጫወተውን ሚና ለማስገንዘብ ያለመ ነው።
በመድረኩም ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ለተወጣጡ አሰሪና ሰራተኞች በሁለትዮሽ ማህበራዊ ምክክር ዝርጋታ እና በአሰሪና ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ላይ ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል።
በዚህም አዋጁን በመረዳት የአሰሪውንና ሰራተኛውን ግንዛቤ ማሳደግ ዓላማው አድርጎ ከዚህ ጎን ለጎን የኢንዱስትሪውን ሰላም በማረጋገጥ ምርታማነትን ለማሳደግ የሚኖሩ አለመግባባቶችን በመቀነስ የስራ ክርክሮችን በምክክር መፍታት የሚያስችላቸው ይሆናል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 2/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬደዋ አስተዳደር የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን ቡድን በሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አካሄደ።
በዚህም ቡድኑ በምልከታውም ቢሮው በግማሽ አመቱ የተከናወኑ በርካታ ሥራዎች መመልከት የቻለ ሲሆን የተሰሩ ስራዎችን መረጃ በአግባቡ በማደራጀት እረገድም ጥሩና ከዚህ በበለጠ እያጠናከሩ መሄድ እንደሚገባ ያስገነዘቡ ሲሆን የድጋፋዊ ክትትሉም አላማ ቢሮው በግማሽ አመት ያከናወናቸውን ተግባራት አፈፃፀም በመገምገም ግብረ መልስ ለመስጠት ያለመ መሆኑ በመድረኩ ተገልጿል፡፡
በበጀት አመቱ የትግበራ ምእራፍም ቢሮው የተሻለ አፈጻጸም ያስመዘገበ መሆኑን በመግለጽ በቀጣይም ያሉ ጠንካራ አፈጻጸሞችን አጠናክሮ በማስቀጠል ቀልጣፋ አገልግሎትን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ በማሳሰብ በከተማ እና በገጠር ለሚገኙ ስራ አጥ ወጣቶችቋሚ የስራ ዕድል ለመፍጠር እንዲያስችል የግሉን ዘርፍ፣ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እንዲሁም የግለሰብ/ቡድን/ አንቀሳቃሾችን የመደገፍ ውጤታማነትን በትኩረት ተመልክቷል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 2/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት በአስተዳደሩ ከሚገኙ የግል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጅ አመራሮችና የሚመለከታቸው አካላት ጋር የኢንስፔክሽን ግብረመልስ መስጫ መድረክ አካሄደ።
በዳይሬክቶሬቱ የተወጣቱ የባለሙያዎች ቡድን በተያዘ ፕሮግራም መሠረት በአስተዳደሩ የሚገኙ የግል ኮሌጆችን ከዘርፍ መስሪያ ቤት ባለሙያዎች ጋር በመቀናጀት የኢንስፔክሽን ስራ ተሰርቷል፤ በዚህ የኢንስፔክሽን ሪፖርት የሚቀርብበት መድረክ ላይ በቢሮው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ታሪኩ ለገሰ ባስተላለፉት መልዕክት የትምህርትና ስልጠና ዘርፍ የግሉ ባለሃብት ተሳታፊ እንዲሆን መንግስት ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑ ገልጸዋል ነገርግን የኮሌጆች የስልጠና ጥራት ለማስጠበቅ ዳሬክቶሬቱ ጉልህ ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል፤
በሪፖርቱ በተመላከቱት ክፍተቶች ላይ ትኩረት በመስጠት በአጭር ጊዜ ውስጥ ማስተካከያ በማድረግ በ2016 ዓ.ም የትምህርትና ስልጠና ዘመን ጥራትን ከመምጣት አንፃር ትኩረት አድርጎ መስራት ይጠበቅባቸዋል፤ ውስንነት የተገኘባቸው ኮሌጆችም የቅርብ ክትትል በማድረግ የታየባቸውን ውስንነት የመሙላትና የማስተካከል ስራዎችን እንደሚሰራ በመግለጽ በቀረበው የኢንስፔክሽን ሪፖርት ላይ ሰፊ ውይይት ማካሄድ ተችሏል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 1/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
የድሬደዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ በኮሌጁ ሣተላይት ካንፓሥ ለሚማሩ ተማሪዎች ማዕድ አጋራ::
በማዕድ ማጋራቱ ላይ በመገኘት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሳሊም ኡሥማን ሲሆኑ በመልእክታቸውም እንኳን ለገና በዓል አደረሣችሁ በዓሉን ከእናንተ ጋር ሥናከብር በጣም ደሥተኞች ነን የተለያዩ በዓላትን ስናከብር ያለንን ለአቅመ ደካሞችና ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው አካላት በማካፈል መሆን ይጠበቅበታል ብለዋል::በቀጣይም በተለያዩ በዓላትም እንዲ አይነት መርሐግብሮች በማድረግ ያለንን የምናካፍል ይሆናልም ብለዋል::
በመቀጠል ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ም/ዲን አቶ ሰልልሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ በንግግራቸውም እንኳን ለገና በዓል አደረሣችሁ ያሉ ሢሆን እንደሚታወቀው ድሬደዋ የፍቅር ከተማ ነች ይህን የፍቅር ስም ደግሞ የእውነት እንዲሆን እንዲ አይነት ተግባራ በሠፊው መከናወን ይኖረበታል በዚህም መሰረት በዛሬው እለት የተደረገው መርሃግብር የማህበረሠቡን አንድነት ባሥጠበቀመልኩ ነው:: ይህን መርሐግብር ላሥተባበረወ አቶ ታምራትም ምሥጋና አቀርባለሁ ብለዋል::
የኮሌጁ ኮምንኬሽን
ታህሳስ 28/2016 ድሬደዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው የገና በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ!!
"መላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለጌታችንና መድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
በዓሉ የሠላም፣ የደስታ፣ የጤና፣ የመተሳሰብ፣ የአንድነትና የፍቅር ይሁንላችሁ እያልኩ መልካም ምኞቴን እገልጻለሁ። በዓሉን ስናከብር አንዳችን ለሌላው በማሰብና ያለንን በማካፈል በቆየውና በምንታወቅበት ኢትዮጵያዊ ዕንቁ ባህላችን ሊሆን ይገባል፡፡
የኢየሱስ ክርስቶስ መወለድ ለክርስትና እምነት ተከታዮች የህይወታችን አዲስ ምዕራፍ ብስራት እንደመሆኑ በዓሉ ከመቼውም ጊዜ በላይ ለተሻለ ነገ የምንሰራበትና በሁላችን ትብብር የገነባነውን ኢትዮጲያዊ አንድነታችንን የምናጠናክርበት በዓል እንዲሆን እየተመኘሁ በድጋሚ መልካም የገና በዓል ።
መልካም በዓል!!
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
