Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
Kanalga Telegram’da o‘tish
Ko'proq ko'rsatish
1 067
Obunachilar
+424 soatlar
-27 kunlar
+230 kunlar
Postlar arxiv
+2
#አሁን
#Happening_Now
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሞዴል ኢንተርፕራይዞች የምረቃና ሽግግር በዓል
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
#|የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ላይ ትኩረቱን ያደረገ መግለጫ
ከሰኔ 23 እስከ ሀምሌ 8 የሚቆየውን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተናን አስመልክቶ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሙሉ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታወቀ፡፡
በ2017 ዓ.ም የሚሰጠውን ሀገር አቀፍ ፈተና ለመፈተን በቂ የቅድመ ዝግጅት ስራ ማከናወኑን የገለጹት የኮሌጁ ዲን ክቡር አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ ዲኑ አያይዘውም በዘንድሮዉ 2017 በአስተዳደሩ 12ተኛ ክፍልን አጠናቀው በሃገር አቀፍ ደረጃ የሚሰጠውን ፈተና ለመውሰድ ከተመዘገቡት ውስጥ 1100 በላይ ተማሪዎች በኮሌጁ በመገኘት በኮምፒውተር የታገዘ online exam ይፈተናሉ ያሉ ሲሆን፡፡
እነዚህ ተፈታኞች ምንም አይነት ችግር እናዳይገጥማቸው ፈተናው ከመድረሱ በፊት የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ሲሰሩ እንደነበረ የገለጹ ሲሆን እንደ ማሳያም በኮሌጁ የሚገኙ ከ13 በላይ ዘመናዊ የኮምፒውተር ላብራቶሪዎች ዝግጅት፣የመብራት ችግር እንዳይገጥም ደግሞ የጀነሬተር ዝግጅት እንዲሁም የኢንተርኔት ፍጥነቱን በፊት ይጠቀምበት ከነበረው 200mbps ወደ 500mbps የኢንተርኔት ፍጥነት የማሳደግ ስራዎች ተሰርተዋል ብለዋል፡፡
የኮሌጁ ዲን እንደገለጹት ከ2016 የፈተና ሂደት ጥሩ ትምህርት በመውሰድ ድክመቶችን በማረም ፈተናው የተሳካ እንዲሆን ርብርብ በማድረግ የ2017 ዓ.ም የፈተና ሂደት በፈጣሪ ድጋፍ ያለምንም ችግር እንዲሳካ ኮሌጁ እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡በመጨረሻም በኮሌጁ ተገኝታችሁ ፈተናችሁን የምትወስዱ ውድ ተማሪዎች መልካሙን ሁሉ እየተመኘሁ ፈተናውም መልካም ፈተና እንዲሆንላችሁ በራሴና በኮሌጁ ማህበረሰብ ስም ምኞቴን እገልጻለሁ፡፡
በዘንድሮዉ 2017 ዓ.ም በአስተዳደሩ 12ተኛ ክፍልን አጠናቀው በሃገር አቀፍ ደረጃ የሚሰጠውን ፈተና ለመውሰድ ከተመዘገቡት ውስጥ 1100 በላይ ተማሪዎች በኮሌጁ በመገኘት በኮምፒውተር የታገዘ online exam እንደሚፈተኑ ለማወቅ ተችሏል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ሰኔ 20/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
በኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር አገልግሎት ዋና ስራ ሂደት የበጀት አመቱን የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት መድረክ ማካሄድ ጀመረ::
ሰኔ 20/2017ዓ.ም ድሬዳዋ
በእለቱ በነበረው መርሀ-ግብር በዋና ስራ ሂደቱ የሚገኙ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ የወረዳ ተጠሪዎች እና በሂደቱ የጥናት፣ቴክኖሎጂ ሽግግር ስር የሚገኙ ባለሙያዎችን የአፈፃፀም ሪፖርት መመልከት ተችሏል::
በመድረኩም በ2017 በጀት ዓመት በዋና ስራ ሂደቱ ይከናወናሉ ተብለው በእቅድ ከተያዙ ተግባራት አንፃር የተሰሩ ስራዎች አፈፃፀምን የተመለከት ሪፖርት በተጠሪዎች ቀርቧል::
በሪፖርት መድረኩ በዋናነት በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት በአራቱ የድጋፍ ማዕቀፎች ላይ የተከናወኑ ተግባራትን፣ ቴክኖሎጂንዎችን ከማሸጋገር አንፃር የተሰሩ ስራዎችን እንዲሁም በጥናትና ምርምር የተገኙ ውጤቶችን ጨምሮ በኮሌጁ የሚሰጡ ተጨማሪ ተልዕኮዎችን ከመፈፀም አኳያ የተከናወኑ ተገባራትን በዝርዝር የሚዳስስ ሪፖርትም ቀርቦበታል::
በቀረቡት ሪፖርቶች መነሻነትም በመድረኩ ሰፊ ውይይት የተካሄደበት ሲሆን የታዩ ጠንካራ ጎኖችን በይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል እንዲሁም ክፍተት በተስተዋለባቸው ጉዳዮች ላይም በቀጣይ በትኩረት መስራት እንደሚገባም ተገልፇል::
የሪፖርት መድረኩ በቀጣይ ቀናትም ቀጥሎ የሚካሄድ ሲሆን ተጨማሪ የተሰሩ ስራዎችን ጨምሮ የዋና ሂደቱን አጠቃላይ አፈፃፀም የሚመለከት ይሆናል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
የዜጎችን የማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ አበረታች ስራ እየተሰራ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ።
በድሬዳዋ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ መስመር የብድር ምችችት ፕሮግራም በድሬደዋ አስተዳደር ከሚገኙ የባንክ እና የፋይናንስ አገልግሎት ከሚሰጡ ብሎም በዘርፉ ላይ ከተሰማሩ አካላት ጋር ውይይት አድርጓል።
የድሬዳዋ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው መስመር ኘሮግራም የባንክ የብድር አገልግሎት ተጠቅመው የማያውቁ ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ጠቅሰው ይበልጥ ተደራሽ ያልሆኑ ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚያስችል ተናግረዋል።
በመስመር ፕሮግራም በተለመደው የባንክ አገልግሎት ስርዓት ውስጥ የሌሉትን አካላት የሞያ ክህሎት ስልጠና እንዲያገኙ እና የብድር ምችችት ከባንኮች ጋር በማስተሳሰር የተሻለ ውጤት እንዲያገኙ ማስቻሉን የተናገሩት ደግሞ የመስመር ፕሮግራም መሪ የሆኑት ቀነኦ ኢታና ናቸው።
ከዚህ ቀደም በድሬዳዋ ከ1ሺ በላይ ኢንተርፕራይዞች ተጠቃሚ እንደሆኑ እና ከነዚህ መካከልም 78 በመቶ ሴቶች መሆናቸው ተጠቅሷል።
በፕሮግራሙ 3,671 ኢንተርፕራይዞች የተመዘገቡ ሲሆን 58 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸው ተገልጿል።
ለብድር ተጠቃሚዎች ተገቢውን ሞያዊ እና በፋይናንስ አስተዳደር ዘርፍ ላይ ያተኮረ ተገቢውን ስልጠና በመስጠት ብድሩን እንዲያገኙ ይደረጋል ተብሏል ።
ዳሽን ባንክ አዋሽ ባንክ ህብረት ባንክ እና አቢሲኒያ ባንክ ከመስመር ፕሮግራም ጋር በጋራ የሚሰሩ ድርጅቶች ናቸው።
በውይይት መድረኩ ላይ በተነሳው አስተያየት በዘርፉ ላይ ብድር ወስዶ አለመመለስ ፣የብድር አገልግሎት ላይ የጠራ አመለካከት አለመኖር ፣ የብድር መጠኑ አነስተኛ መሆን እና በቶሎ ተስፋ መቁረጥ ዋነኛ ችግር መሆናቸው ተጠቅሷል ።
©️ DireTvአማርኛ | ሰኔ 20፣ 2017 ዓ.ም| ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የበጀት ኢኮኖሚ ንግድና ኢንደስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የአፈፃፀም ግምገማና የመስክ ምልከታ አካሄደ::
ቋሚ ኮሚቴው የፕሮጀክቶች አፈፃፀም በተመለከተ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአዳራሽ እድሳት ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝና ከቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲሁም ከስራ እድል ፈጠራ ጋር የተሰሩ ስራዎችን ቋሚ ኮሚቴው በምልከታው አካቷል።
የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአዳራሽ እድሳ ፊዚካል አፈፃፀሙ 87በመቶ የደረሰ ሲሆን የወንበር ገጠማና የማጠናቀቂያ ስራዎች የሚቀሩት መሆኑን ኮሚቴዉ ተመልክቷል።
በተጨማሪም የዶሮ ማቀነባበሪያ ፣ የንብ ቀፎ ÷ የኮሪደር ልማትን ታሳቢ ያደረገ የመንገድ ላይ መቀመጫዎች በኮንቴነር ተለዋጭ የሚሆን ሱቅ በኮሌጁ የተሰሩ ስራዎችን ቋሚ ኮሚቴዉ በመዘዋወር ምልከታ አድርጓል ።
በተለያዩ የስራ ዘርፍ ላይ ካሉ የኮሌጁ አመራሮች ጋር በተደረገው ውይይት ኮሌጁ ከአገልግሎት አሰጣጥ አንፃር አለም አቀፍ የጥራት ደረጃ እዉቅና የተሰጠዉና በክህሎት ዉድድር በአይሲቲ ዘርፍ አንደኛ በመዉጣት ያጠናቀቀ ፣ የተማረ በክህሎት የላቀ ዜጋን ለማፍራት በርካታ ስራዎችን እየሰራ መሆኑ ተገልጿል።
በተጨማሪም ኮሌጁ የሴቶችን፣ ህፃናትንና አካል ጉዳተኞችን ማዕከል ያደረገ የመማር ማስተማር ሂደት ቀርፆ እየሰራ እንደሚገኝ ለቋሚ ኮሚቴው ገለፃ አድርገዋል ።
የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት ኢኮኖሚ ንግድና ኢንደስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴም ኮሌጁ ከጊዜ ወደ ጊዜ እራሱን እያሳደገ መሆኑ ገልፀዉ በቀጣይ ዉስጠ ገቢን የማሳድግ ስራ ትኩረት ተሰጥቶበት መሰራት እንዳለበት ጠቁመዋል።
ከአምራች ኢንዱስትሪዎች ጋር ኮሌጁ ቅንጅታዊ አሰራር በማጠናከር በሀገር ዉስጥ ተኪ ምርት የማምረት እና የገጠሩንም የማህበረሰብ ክፍል አካታች የሆኑ ስራዎች መሰራት እንዳለባቸው ቋሚ ኮሚቴው አፅኖት ሰጥቶቷል ።
የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
‹‹የSIFA ፕሮጀክት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ሲደረግ እንደ ሀገር የሚጠቅመው ጥቅም የላቀና ብዙ ወጣቶችን የክህሎት፣የስራ ባለቤት እንዲሁም የስራ ፈጣሪ የሚያደርግ እንደሆነ እና ከተማችንን ደግሞ ዲጂታል አሰራሮች የሚያሳድግ ፕሮጀክት እንደሆነ እተማመናለሁ፡፡›› ክቡር አቶ ሮቤል ጌታቸው የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ
በAUDA NEPAD እና EU የገንዘብ ድጋፍ እየተተገበረ የሚገኘው የ Skill Initiative For Africa(SIFA) ፕሮጀክት የICT የልህቀት ማእከል የጨረታ ሂደት ለመገምገምና የልህቀት ማእከሉን ግንባታ ሂደት ለማስጀመር ያለመ AUDA NEPAD እና EU የግዢ ስራ ክፍል ከፍተኛ ባለሙያዎች አቶ ቪንሴንት እና ከSIFA ፕሮጀክት ተወካዮች የተውጣጣ የግምገማ ቡድን በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጉብኝት አደረገ፡፡
በግምገማና ውይይት ሂደቱ ላይ በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ሮቤል ጌታቸው ሲሆኑ በንግግራቸውም የSIFA ፕሮጀክት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ሲደረግ እንደ ሀገር የሚጠቅመው ጥቅም የላቀና ብዙ ወጣቶችን የክህሎት፣የስራ ባለቤት እንዲሁም የስራ ፈጣሪ የሚያደርግ እንደሆነ እና ከተማችንን ደግሞ ዲጂታል አሰራሮች የሚያሳድግ ፕሮጀክት እንደሆነ እተማመናለሁ፡፡ ይህ በጀርምን መንግስት ድጋፍ የሚተገበረው በተጨማሪም በኮሌጁ እየተተገበረ ያለው ይህ የSIFA ፕሮጀክት መሳካት የከተማችን አስተዳደር ፕጀክቱ ከግብ እንዲደርስ ማቺንግ ፈንድ በመመደብ ለሌሎች ከተሞች አርአያ የሆነ ተግባር ፈጽመዋል ይህም ፕሮጀክቱ ከግብ እንዲደርስ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡
በኮሌጁ የሚተገበረው ይህ የSIFA ፕሮጀክት ወጣቶቻችን የሙያና የስራ ፈጣሪ የሚያደርግ ትልቅ ፕሮጀክት ነው፡፡ ያሉት የኮሌጁ ዲን ክቡር አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ አያይዘውም ዘመኑ የAI ዘመን እንደመሆኑ መጠን ይህ በኮሌጁ የሚገነባው የልህቀት ማእከል ከተማችንን ብሎም ሃገራችንን የICT ማእከል የሚያደርጋት ነው ብለዋል፡፡
በግምገማና ውይይቱ ሂደቱ ወቅት የSIFA ፕሮጀክት እስካሁን የደረሰበት የፕሮጀክት አፈጻጸም በአቶ ሃምዲ ሙሃመድ ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን በስተመጨረሻም በኮሌጁ ውስጥ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ተዘዋወውረው ጎብኝተዋል፡፡
በጉብኝቱና በሪፖርቱ መሰረትም ልኡክ ቡድኑ የመሩት አቶ ቪንሴንት እንዳሉት ኮሌጁ የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ለመሆን እየሰራ ያለውን ስራ አድንቀው በቀጣይ በኮሌጁ ውስጥ የሚገነባው የICT ልህቀት ማእከል ሲጠናቀቅ ደግሞ ለኮሌጁ ብሎም ለከተማው እንዲሁም ለሃገሪቱ የሚሰጠው ጥቅም ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡አያይዘውም የልህቀት ማእከሉን ግንባታ በፍጥነት ተጀምሮ እንዲያልቅ አስፈላጊውን ስራ በAUDA NEPAD እና EU በኩል እንደሚፈጸም ተናግረዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ሰኔ 19/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
ሥራ አጥነትን ለመቅረፍ በሚደረገው ጥረት የቴክኖሎጂ ፈጠራ እና የንግድ ሃሳብ ያላቸው ዜጎችን መደገፍ እንደሚገባ ተገለፀ፡፡
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የተዘጋጀ የ2017 ዓ.ም "ብሩህ" የንግድ ፈጠራ ሃሳብ ውድድር የሽልማትና የእውቅና መርሃግብር ተካሄደ፡፡
በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በሀገራችን የሚታየውን ስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ በሚደረገው ጥረት የቴክኖሎጂ ፈጠራና የንግድ ሃሳብ ያላቸውን አካላት መደገፍ ይገባል ብለዋል፡፡
ውድድሩ የፈጠራ ስራ ያላቸውን አካላት ሃሳባቸው ተግባራዊ የሚደረግበትን መድረክ ለመፍጠር ከማስቻሉም በላይ ለበርካቶቹ የሥራ ዕድል የመፍጠር ዓላማ እና ግብ አለው።
በመርሃግብሩ ከዚህ ቀደም በተከታታይ አመታት በተደረጉ ውድድሮች ተሳታፊና አሸናፊ በመሆን ሃሳቦቻቸውን ወደ ስራ የቀየሩ ወጣቶች ልምዳቸውን ለተወዳዳሪዎች ማካፈል ችለዋል።
ተወዳዳሪዎችና የውድድሩ አሸናፊዎች የገንዘብ ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን ውድድሩ በመዘጋጀቱና በመሳተፋቸው የፈጠራ ስራቸውን ለታለመለት አላማ ለማዋል ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 19/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
#አሁን
#Happening Now
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የተዘጋጀ የ2017 ዓ.ም ብሩህ የንግድ ፈጠራ ሃሳብ ውድድር የሽልማትና የእውቅና መርሃግብር
ረቂቅ አዋጁ ቅንጅታዊ አሰራሮችን የሚያጠናክርና የዜጎችን ደህንነት፣ ብቃትና ተወዳዳሪነት ማጎልበት የሚያስችል ነው
የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ረቂቅ አዋጅ ቅንጅታዊ አሰራሮችን የሚያጠናክርና የዜጎችን ደህንነት፣ ብቃትና ተወዳዳሪነት ማጎልበት የሚያስችል መሆኑ ተመላከተ።
በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ ስራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በውጭ ሀገር ስራ ስምሪት ረቂቅ አዋጅ ላይ ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሀላፊዎች ጋር ተወያይቷል።
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አዋጁን ማስፈጸም የሚያስችል የሰው ሀይል የማደራጀትና ሌሎች የዝግጅት ስራዎችን ማከናወንን ጨምሮ የአዋጁ ማስፈጸሚያ ደንብና መመሪያዎችን የማዘጋጀት ስራ ከወዲሁ በትኩረት ሊሰራ ይገባል።
አዋጁ በተለያዩ ሙያዎች ሰልጥነው ስራ የሚፈልጉ ዜጎችን ማካተቱ እንዲሁም፣ ኤጀንሲዎች በማህበር ተደራጅተው እንዲሰሩ የሚያደርግ መሆኑ መልካም ነው ብለዋል።
በረቂቅ አዋጁ ላይ የጤና ምርመራ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት ምርጫ፣ የኮሚሽን ድርድር በኤጀንሲዎችና ፌዴሬሽን ብቻ መገደቡና የባህረኞችና የሹፌሮች የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት ላይ ያተኮሩ ጥያቄዎች ከቋሚ ኮሚቴውና የህግ ጥናት ዳይሬክቶሬት ቀርበዋል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በሰጡት ምላሽ ረቂቅ አዋጁ ቅንጅታዊ አሰራሮችን የሚያጠናክርና የዜጎችን ደህንነት፣ ብቃትና ተወዳዳሪነት ማጎልበት የሚያስችል ነው ብለዋል።
ህገወጥነትን ከመከላከል አንጻርም ቀደም ሲል በነበረው አዋጅ ላይ የታዩ ክፍተቶችን መፍታትና ጠንካራ እርምጃዎች መውሰድ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።
የዜጎችን ደህንነት ከማስጠበቅ፣ ሀገሪቱ ከውጭ ምንዛሬ ማግኘት ያለባትን ገቢ፣ በዘርፉ የዳበረ ልምድ ያላቸው ሀገራትን ተሞክሮ መሰረት በማድረግ የኮሚሽን ድርድር በኤጀንሲዎች ብቻ እንዳይደረግ መደረጉን ጠቅሰዋል።
በውጭ ሀገራት የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አመራር አባል እና ቤተሰቦች የኤጀንሲ ፍቃድ እንዳያገኙ ክልከላ የተደረገው የዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅና የጥቅም ግጭትን ለመከላከል መሆኑንም አንስተዋል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ(ዶ/ር) ወደ ውጭ ሀገራት ለስራ ስምሪት የሚሄዱ ዜጎች ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ በመዳረሻ ሀገራት ከሚቀያየሩ ሁኔታዎች አንጻር የክለሳ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን አንስተዋል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ዳንኤል ተሬሳ በበኩላቸው፤ የዜጎችን ደህነነት ለማስጠበቅና ህገወጥነትን ለመከላከል በማሰብ በረቂቅ አዋጁ ጠንካራ ህጎች መካተታቸውን ገልጸዋል።
በምክር ቤቱ በተደጋጋሚ ሲነሳ የነበረው የኤጀንሲዎች መብዛትንም በጋራ ሆነው እንዲሰሩና ለአስተዳዳር ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር በማህበር እንዲደራጁ የሚያስችል መሆኑን ጠቅሶ የዘገበው ኢዜአ ነው።
“ዕቅዶቻችን በዋናነት የክህሎት፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአሰሪና ሰራተኛ ዘርፉን ግቦች ሊያሳኩና የአስተዳደሩን ነዋሪ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ላይ ያተኮሩ ተግባራትን እንደ ቢሮ ተናብቦ እና ተቀናጅቶ መፈጸም ትኩረት ተሰጥቶታል፡፡”
አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ለቀጣይ በጀት ዓመታት ማለትም በመካከለኛ የዕቅድ ጊዜ ከ2018 እስከ 2020 ዓ/ም የሚሰሩ ስራዎችን እንዲሁም ለነዚህ ተግባራት ማስፈፀሚያ ተብሎ በተዘጋጀ የፕሮግራም በጀት ዕቅድ ላይ ውይይት አደረገ፡፡
ቢሮው ከዘርፉ ተግባራት አንፃር አገራዊ የፖሊሲና የትኩረት አቅጣጫዎችን መሰረት ያደረጉ ተግባራት በዕቅዱ ተካተው እንዲዘጋጁ የተደረገበት ሁኔታ በስፋት የገመገመ ሲሆን ለዕቅዱ ተግባራዊነት አስፈላጊ የሆኑ ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ በመወያየት ዕቅዱን ማጽደቅ ተችሏል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 17/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
