Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
Kanalga Telegram’da o‘tish
Ko'proq ko'rsatish
1 069
Obunachilar
+224 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
+230 kunlar
Postlar arxiv
ከሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች ለተመረጡ አሰልጣኝ መምህራን አቅም የሚገነባ ስልጠና ተሰጠ፤
የሙያ ስነ-ምግባር /PROFESSIONAL WORK ETHICS, MORALITY AND PATRIOTISM በሚሉ የስልጠና ርእሶች ላይ በድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ የህግ ትምህርት ክፍል እጩ ፕሮፌሰር በሆኑ መምህር ለሶስት ተከታታይ ቀናት መስጠት ተችሏል፤
በዚህም ስልጠና አእምሮን፣ ልብን እና እጅን በተግባር ማገናኘት የሚችሉ፤ ሁለንተናዊ ብቃትን የተላበሱ የአስተሳሰብ፤ የአመለካከት እና የስነ- ምግባር ባህሪ ለውጥ የሚያመጡ ስልጠና አጠናቃቂ ሰልጣኞችን ለማፍራት ሰው ተኮር ልል ክህሎትን መሰረት ያደረገ ሃገር ወዳድነት እና ሙያዊ ስነ-ምግባርን ለማላበስ በሙያ ደረጃው ውስጥ የተካተቱትን ብቃት አሃዶች እና ኮርሶችን ያካተተ ሆኗል፤
በመሆኑም የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ ትኩረት ሰጥቶበት እየሰራ ካለባቸው የክህሎት ልማት ጉዳዮች ውስጥ ወቅቱ የሚጠይቀን የአርበኝነት አይነት ግልፅ አላማ እና ተልእኮ ያለው ትውልድ የማፍራት በመሆኑ አሰልጣኙ ሲበቃ ብቁ ሰልጣኞችን የማፍራት እድሉ ከፍተኛ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ገልፀዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 1/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ ግራንድ ግሩፕ ከተባለ በድሬዳዋ የመጀመሪያው የሆነ በዲጂታል ማርኬቲንግ እና የበቃ የሰው ሀይል ለኢንዱስትሪዎች አቅራቢ ኢንተርፕራይዝ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ውይይት አካሄዱ።
ውይይቱ በዋናነት ከቢሮው ጋር በተቀናጀ እና በተናበበ አግባብ ከመስራት አንጻር ሰራተኞችን ከማስቀጠር ባሻገር ያሉ ጉዳዮችን በጥናት ላይ የተመሰረተ ችግር ፈቺ ስራዎችን ለመስራትና በአስተዳደሩ የሚገኙ ዜጎችና ተቋማት በዲጂታል ማርኬቲንጉ ተጠቃሚነታቸውን የሚያረጋግጥ ስራዎችን ለማስፋት ትኩረት እንደሚሰጠው ተገልጿል።
የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንደገለጹት ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ማስቀጠር ላይ የሚቆም አለመሆኑና ዘላቂ የሆነ የሥራ ዕድል መፍጠር ላይ ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል፤ ለዚህም መሰል ኢንተርፕራይዞች በአስተዳደሩ መፈጠራቸውና ወደ ስራ መግባታቸው ትልቅ አቅም የሚፈጥር መሆኑና በቀጣይም ተቀራርበው የሚሰሩና አስፈላጊውን ድጋፍ ቢሮው የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 30/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
"ብቃት" የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት ሶስተኛ ዙር ትግበራ በድሬዳዋ ሁለቱም የመንግስት ኮሌጆች ላይ ሰልጣኝ ወጣቶችን ተቀብሎ ማሰልጠን ጀመረ።
በዚህም ለሚቀጥሉት 12 ቀናት የህይወት ክህሎትና የሥራ አፈላለግ ስልጠና በኮሌጆቹ ውስጥ ይሚሰጣቸው ሲሆን ይህንንም ሲያጠናቅቁ በመረጡት የሙያ ዘርፍ በአስተዳደሩ በሚገኙ አምራችና አገልግሎት ሰጪ ኢንደስትሪዎች ላይ የኪስ ገንዘብ እየታሰበላቸው በተግባር እየሰሩ እውቀትና ክህሎታቸውን የሚያዳብሩ ይሆናል።
በተከታታይ ዙሮች ሰልጣኞች በተመሳሳይ ተጠቃሚ የሆኑ ሲሆን በስልጠና ቆይታቸውም በኮሌጆቹ የህጻናት ማቆያ ቦታዎች ተዘጋጅተውላቸዋል በዚህም የልጅ እናት የሆኑ የፕሮጀክቱ ተጠቃሚዎች ስልጠናውን ሳይስተጓጎሉ እንዲወስዱ የሚደረግ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ገልጸዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 29/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
+9
ወጣቶች የኤች.አይ.ቪ ኤድስ ስርጭትን ለመግታት በሚደረገው ርብርብ ጉልህ ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ ተገለፀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከተለያዩ ዲፖርትመንቶች ለተወጣጡ ሰልጣኝ ተማሪዎች የኤች.አይ.ቪ ኤድስ ስርጭትን ለመግታት ያለመ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ::
በመድረኩ ለሰልጣኞች መልዕክት ያስተላለፉት የኮሌጁ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ም/ዲን አቶ ኤሊያስ አህመድ በንግግራቸው ይህን ስልጠና መስጠት ያስፈለገው በሀገራችን በአሳሳቢ ሁኔታ እየጨመረ የመጣው የቫይረሱን ስርጭት አስመልክቶ በተቋሙ ወጣት ሰልጣኝ ተማሪዎች ላይ ሰፊ የግንዛቤ ስራ መስራት በማስፈለጉ እንደሆነ የገለፁ ሲሆን አክለውም ሰልጣኞች የተፈጠረላቸውን ግንዛቤ በየአካባቢያቸው መረጃውን በማካፈል የተሻለ ግንዛቤ ያለው ማህበረሰብ ለመፍጠር በሚደረገው ርብርብ ተሳታፊ ሊሆኑ ይገባልም ብለዋል::
በእለቱ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናውን ለሰልጣኞች የሰጡት አቶ ፈቲ መሀመድ የተዘጋጀውን ሰነድ ለተሳታፊዎች ያቀረቡ ሲሆን በተጨማሪም "የስሜት ብልህነት" በሚል ርዕስ ራስን ስለማወቅ እንዲሁም ራስን ስለመምራትና ስለመቆጣጠር ለመድረኩ ተሳታፊዎች ስልጠና ተሰጥቷል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
መጋቢት 27/2017 ዓ.ም
ለኢንተርፕራይዞች የሚሰጠው ድጋፍ ውጤታማነት እና ቀጣይነትን ለማረጋገጥ የባለድርሻ ተቋማት ቅንጅትና ትብብር ወሳኝ ሚና እንዳለው ተገለጸ።
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱሰትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ለጥቃቅን አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ላይ እየተሰጠ ያለውን የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ በተመለከተ የሱፐርቪዥን ሪፖርት ድጋፉን ለሚያደርጉ አሰልጣኝ መምህራኖች በማቅረብ የውይይት መድረክ ተካሄደ።
ዳይሬክቶሬቱ በተለያዩ ዘርፎች ለተደራጁ ጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ድጋፍ በዋናነት ኢንተርፕራይዞች ምርትና ምርታማነት እንዲጨምርና የስራ እድል እንዲፈጥሩ ማስቻል መሆኑን በመረዳት ከአሰልጣኝ መምህራኑ ጋር የጋራ ስምምነትና መግባባት በመፍጠር ውይይት ማካሄድ ተችሏል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 26/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
እንኳን ደስ አላችሁ!!
#የድል_ዜና
በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የተሰሩ የፈጠራ ስራዎች በተሳተፉበት የቴክኖሎጂ ውድድር አሸናፊ ሆኑ::
በክልል/በአስተዳደር ደረጃ በተካሄደው የቴክኖሎጂ ውድድር የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅን ወክለው የተወዳደሩ ቴክኖሎጂዎች ውድድሩን በአሸናፊነት አጠናቀቁ::
ለቴክኖሎጂ ጥራት መሻሻል ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ታምኖበት በየሁለት አመቱ የሚዘጋጀው የቴክኖሎጂ ውድድር ዘንድሮም በደማቅ ሁኔታ የተካሄደ ሲሆን በክልል ደረጃ በሁለቱ ፖሊቴክኒኮች መካከል በተደረገው ውድድር ኮሌጃችንን ወክለው የተለያዩ ቴክኖሎጂዎች መሳተፍ የቻሉ ሲሆን ውድድሩንም በአሸናፊነት አጠናቀዋል::
በውድድሩ አጠቃላይ ውጤትም በኮሌጃችን አሰልጣኝ መምህራን የተሰሩ ቴክኖሎጂዎች 1ኛ እና 2ኛ በመውጣት ውድድሩን በፍፁም የበላይነትና አሸናፊነት ማጠናቀቅም ችለዋል::
በውድድሩ 1ኛ በመሆን ያሸነፈውና በኮሌጃችን አሰልጣኝ መ/ር ያሬድ ሁሉአለም አማካኝነት በሀገራችን የሚስተዋለውን የነዳጅ ችግር መነሻ በማድረግ የተሰራው ከእፅዋትና ከተለያዩ ግብአቶች የተመረተ የነዳጅ ዘይት የውድድሩ አሸናፊ መሆን ችሏል::
በውድድሩ 2ኛ በመሆን ያጠናቀቀው ደግሞ በኮሌጃችን አሰልጣኝ መ/ር ሲሳይ ምንዳ፣ አሰልጣኝ መ/ር አበበ ተረፈ እና አሰልጣኝ መ/ር ያሬድ ሁሉአለም የተሰራውና የአርሶ አደሩን ችግር በዘላቂነት የሚፈታ የእርሻ ማረሻ መሳሪያ ውድድሩን በ2ኛ ደረጃ አጠናቋል::
በተጨማሪም በውድድሩ ኮሌጁን ወክሎ የተወዳደረውና በአሰልጣኝ መምህር ግሩም ታምራት እንዲሁም አሰልጣኝ መምህር አበበ ተረፈ የተሰራው ዘመናዊ የእንቁላል ማስፈልፈያ ኢንኩቤተር በውድድሩ 5ኛ በመውጣት አመርቂ ውጤት ማስመዝገብም ችሏል::
በዚህም መሰረት የውድድሩ አሸናፊ ቴክኖሎጂ በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄድው የቴክኖሎጂ ውድድር ላይ አስተዳደራችንን ድሬዳዋን በመወከል በሚደረገው የቴክኖሎጂ ውድድር ላይ የሚሳተፍም ይሆናል::
በክልል ደረጃ ኮሌጃችንን በመወከል አሸናፊ የሆናችሁ የቴክኖሎጂ ባለቤቶች እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን እያልን በሀገር አቀፍ ደረጃ ድሬዳዋን ወክላችሁ የምታደርጉት ውድድርም በውጤት የታጀበ እንዲሆን ኮሌጁ መልካም ምኞቱን ይገልፃልም::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
መጋቢት 26/2017 ዓ.ም
በድሬዳዋ አስተዳደር የተዘጋጀው፥ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎች ውድድር ዛሬም ቀጥሎ ተካሄደ።
ይህ ውድድር በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ እንዲሁም በሳይንስ፥ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኤጀንሲ የጋራ ትብብር የተዘጋጀ ነው።
የተለያዩ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችን በማበልፀግ በአስተዳደሩ ጥቅም ላይ እንዲውሉ ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ረገድ፥ ይህ የፈጠራ ስራዎች ውድድር ጉልህ አስተዋፅኦ የሚያበረክት ይሆናል።
እየተካሄደ ባለው የቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎች ውድድር ላይ ከአስተዳደሩ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ተማሪዎችና መምህራን እየተካፈሉ ይገኛሉ።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 25/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
