uz
Feedback
ታሪክ ቀልድ እና ቁም ነገር😂😂

ታሪክ ቀልድ እና ቁም ነገር😂😂

Kanalga Telegram’da o‘tish

ታሪክ ቀልድ እና ቁም ነገር ------------------- 👉ቀልዶች 👉ቁም ነገሮችን 👉አስደሳች የፍቅ ታሪኮች 👉አስገራሚ እውነታዎች ይቀላቀሉ ቀኑን ሙሉ ሲዝናኑ ነው የሚውሉት በነገራችን ላይ ጥርሳችሁ እስኪረግፍ አስቃቹ ነበር ግን ብከሱኝስ 😅😅 እዴ እስካሁን አልተቀላቀላቹም አረ #join በሉ #cross👉 @ismu_my #ለማንኛውም_አስተያየት @kum_negre

Ko'proq ko'rsatish
336
Obunachilar
+1524 soatlar
+637 kun
+44230 kun

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilarni jalb qilish
Dekabr '24
Dekabr '24
+139
0 kanalda
Noyabr '24
+165
0 kanalda
Get PRO
Oktabr '24
+187
0 kanalda
Get PRO
Sentabr '24
+379
0 kanalda
Get PRO
Avgust '24
+931
0 kanalda
Get PRO
Iyul '240
0 kanalda
Get PRO
Iyun '240
1 kanalda
Get PRO
May '240
3 kanalda
Get PRO
Aprel '240
0 kanalda
Get PRO
Mart '240
0 kanalda
Get PRO
Fevral '240
0 kanalda
Get PRO
Yanvar '240
0 kanalda
Get PRO
Dekabr '230
1 kanalda
Get PRO
Noyabr '230
0 kanalda
Get PRO
Oktabr '230
0 kanalda
Get PRO
Sentabr '230
0 kanalda
Get PRO
Avgust '230
0 kanalda
Get PRO
Iyul '230
0 kanalda
Get PRO
Iyun '230
0 kanalda
Get PRO
May '230
0 kanalda
Get PRO
Aprel '230
0 kanalda
Get PRO
Mart '230
0 kanalda
Get PRO
Fevral '230
0 kanalda
Get PRO
Yanvar '23
+18
0 kanalda
Get PRO
Dekabr '22
+18
0 kanalda
Get PRO
Noyabr '22
+13
0 kanalda
Get PRO
Oktabr '22
+31
0 kanalda
Get PRO
Sentabr '22
+32
0 kanalda
Get PRO
Avgust '22
+67
0 kanalda
Get PRO
Iyul '22
+313
0 kanalda
Sana
Obunachilarni jalb qilish
Esdaliklar
Kanallar
21 Dekabr+7
20 Dekabr+9
19 Dekabr+9
18 Dekabr+10
17 Dekabr+19
16 Dekabr+15
15 Dekabr0
14 Dekabr0
13 Dekabr0
12 Dekabr0
11 Dekabr0
10 Dekabr0
09 Dekabr0
08 Dekabr+7
07 Dekabr+16
06 Dekabr+13
05 Dekabr+8
04 Dekabr+10
03 Dekabr+12
Kanal postlari
​​🌿🌿"ጤዛዉ ፍቅሬ 🌿🌿 🌹🌹ክፍል አስራ አራት🌹🌹 ✍✍(እስማኤል መሀመድ)✍✍ . ... ከቤት እንደወጣ ከኃላዉ ከተል አለችና "ሀቢቢ..." አለችዉ። ጅምር ፍቅሯን አቋርጦባት ከቤት ሲወጣ አላስቻላትም። ግድ ስለሆነ እንጂ ከመንገዱ ብታስቀረዉ ደስ ባላት ነበር። እርምጃዉን ገታ አድረጎ ወደ ኃላ ዘወር አለና .."ወይዬ ፎዚቲ ..." አላት። ... "ልብሴን ልቀያይርና አብረን እንሂድ" አለችዉ አብራዉ ሂዳ አብራዉ መመለስ አሰኛት። ድጋሜ የማታገኘዉ ፤ እንደወጣ የሚቀር ይመስል ሆዷ ባ ባ። ፍርሃት ፍርሃት አላት። በቆመበት ፈግጎ .. "ፎዚዬ አንቺ ልብስ እስከምትቀይሪኮ እዚሁ ይመሻል። እኔ ቶሎ ደርሼ ብመለስ አይሻልም?" አላት። ... "አልቆይምኮ ሀቢቢ .. ቶሎ ቀያይሬ ልምጣ" አለችዉ እንደ መሽኮርመም እያደረጋት። ... "እረሳሸዉዴ ሁቢ? ... (እንደ መሳቅ እያደረገዉ) ... አንቺኮ ልብስ ለመቀየር ገና ሸዋር ቤት መግባት አለብሽ። ከዚያ ደግሞ ያ የፈረደበት መስታወት ፊት መገተር አለብሽ ሃሃ..." ... "ሂድ አንተ ደግሞ .." እያለች ወደ'ሱ ቀረብ አለችና ..."አደራ ሀቢቢ ራስህን ጠብቅ" አለችዉ። ... "አታስቢ የኔ ቆንጆ" ... "በመንገድህ ላይ አደራ.. የዛሬ ሾፌሮች እንደሆኑ መንጃ ፍቃዳቸዉ ካርቶን ቀደዉ የሚያድሏቸዉ ይመስል አብዛኞቹ ህጋዊ አይደሉም።..." እያለች አደጋ እንዳይገጥመዉ በመፍራት ብዙ አስጠነቀቀችዉ። እሱም ፈገግታዉ ከፊቱ ሳይለየዉ የምትነገረዉን ሁሉ በጽሞና ሰማት። ... "እወድሃለሁ የኔ ዉብ..." ብላ በቆመበት ሂዳ ጥምጥም ብላ አቀፈችዉ። እንደወጣ ይቀራል ተብላ የተነገራት ፤ ፍቅርሽ በጅምሩ ይቀራል ተብላ ሹክ የተባለች ይመስል ዉስጧን ባር ባር አላት። ሀቢብም ያቀፈችዉን ሚስቱን እሱም አቀፋት። የሷ አስተቃቀፍ ግን ይለያል!። ... "በቃ ወደ ቤት ግቢ ፎዚዬ እኔም ቶሎ ልሂድ" አላት። ሀቢብ .. በድኑ እሷ ዘንድ ይቁም እንጂ አሁን ሀሳቡ ሁሉ ሀምዛ ላይ ሆኗል። ቆየሁበት እያለ መጨነቅ ይዟል። ከእቅፉ ዉስጥ ሲያወጣት እሷ ግን የጠመጠመችበትን እጇን አላላቀቀችም። 'ይሄን ያክል ፍቅር ርቧት ነበር ማለት ነዉ' ሲል አሰበ። ፍቅር ከምንም ነገር በላይ ይርባል። ከጥም በላይም በጣም ይጠማል። ገንዘብ ያላቸዉ ሰዎች ሁሉ በገንዘባቸዉ የማያገኙት ነገር ቢኖር እዉነተኛ ደስታንና ፍጹምነት የተሞላበት ፍቅርን ነዉ። ፍቅር ከጤናም በላይ ዉድ የሆነ ነገር ነዉ። ምክንያቱም በህይወት ያለ ሰዉ ሁሉ ማፍቀር አይችልም። ምናልባት ሊያፈቅር ቢችል እንኳ አንዳንድ ሰዎች መጥፎነትን ያፈቅራሉ ፤ ጥላቻን ይቀባሉ ፤ ክፉነትን ይመርጣሉ። ነገር ግን በተቃራኒዉ ማፍቀር የሚችሉ ነገሮች ሁሉ ህይወት አላቸዉ። በህይወት መኖርን ትርጉም የሚሰጠዉ ነገር ንጹህ ፍቅር ሲታከልበት ፤ ደስታ ሲጨመርበት ነዉ። ፎዚያ የእስከዛሬ ትርጉም የሌለዉ ህይወቷን ፤ ያለፈዉ ከደስታ የራቀዉ ኑሯዋን ዛሬ በፍቅር ስለተዋበላት ያን የፍቅር ንጉስ መቀናጆዋን በቀላሉ ልትለቀዉ አልቻለችም። በሽንጡ በኩል ሰድዳ ጥምጥም ያደረገችበትን እጇን ቀስ ብሎ አላቀቃቸዉ። ..."ፎዚዬ ቶሎ እመለሳለሁ። ከዚያ ስትመኚዉን የነበረዉን ሁሉ እያደረግን ጣፋጭ የፍቅር ጊዜን እናሳልፋለን - እሺ!" አላት። እንደሚያባብሉት ህጻን ልጅ እሺታዋን በአንገቷና በይኗ ገለፀችለት። የግራ ጉንጯን ሳም አድርጎ ሲሄድበት ወደነበረበት አቅጣጫ ዙሮ መንገዱን ጀመረ። ፎዚያም ጀርባዉን ሰጥቷት የሚሄደዉን ባሏን ከአይኗ እስከሚጠፋ ድረስ በስስት እየተመለከተችዉ ሸኘችዉ። . . .... "መኪዬ.." አላት አይኖቹን በመስኩቱ ወዲያ ማዶ የሚታየዉን ግትር ህንጻ እየተመለከተ። 'ወይ' አለችዉ በተቻኮለ አይነት። .... "መኪዬ አሁን ሀቢብ ሲመጣ ተቻኩለሽ ዶክተሩ ምን እንዳለኝ እንዳትነግሪዉ - እሺ" ብሎ በተኛበት ቦታ እንዳለ አንገቱን መለስ አድርጎ ወደ'ሷ ተመለከተ። መኪያም እንደዚህ ያለበትን ምክንያት ለማወቅ ያክል ..."ለምን ሀምዚ?" ብላ በተቀመጠችበት ቦታ እንደመደላደል እያለች ጠየቀችዉ። ... "ሀቢብ እንዲደነግጥ አልፈልግም። እኔዉ ቀስ ብዬ አረጋግቼ እነግረዋለሁ!" ሲላት የባሏን ትዕዛዝ ጥሳ የማታዉቀዉ መኪያ 'እሺ አልነግረዉም' ብላ ሀሳቡን በይሁንታ ተቀበለች። . . ... ሀቢብ ስለማን እንደሚያስብ ግራ ገብቶታል። አንዴ ስለ ቤቱ ፤ ቀጠል አድርጎም ሰሞኑን ስላቋረጠዉ ስራና ስለ አመለ ቢሱ የቅርብ አለቃዉ ፤ በመሃል ደግሞ ስንቅር የሚልበት .. ሆስፒታል ዉስጥ ክፉኛ እግሩን ተጎድቶ ስለተኛዉ ጓደኛዉ - ሀምዛ ... በሀሳብ ዉጥር ብሏል። ሁሉም 'እሱን ተወዉ' 'እሱን ተወዉና ስለ'ኔ እሰብ እያሉ የሚከፋፈሉት ፤ የሚቦጫጨቁት መሰለዉ። እግሮቹን እሱ ሳይሆን የሚያዛቸዉ ሀሳብ ከኃላዉ ሆኖ እንደ ጋሪ የሚገፋዉ እስኪመስለዉ ድረስ ራሱን አያዉቅም። . . ... ፎዚያ ባሏን በአይኗ ከሸኘች በኃላ ወደ ቤቱ ገባች። ሀቢብ ከቤት ከወጣ ጀምሮ ሀሳብ አይሉት ሰበብ የጭንቀት ናዳ አእምሮዋ ላይ ሰፈረባት። የትጥበት ግዴታዋን ለመወጣት ወደ ሸዋር ቤት ከገባች በኃላ ዉሃዉን በሃይል ከፍታ መታጠብ ጀመረች። ... ከፀጉሯ ኩልል ብሎ የሚወርደዉ ዉሃ በግንባሯ ላይ ተንከባሎ ቅንድቧን አልፎ አይኗ ዉስጥ ሊገባ ሲል አይኖቿን ከደነቻቸዉ - ጨፈነች። በዚህ መካከል ህልም አይሉት ቅዥት በአይነ ህሊናዋ አስደንጋጭ ክስተት ተመለከተች። ከራሷ በላይ የምትወደዉ ባሏ ሀቢብ የእጅ ስልኩን በእጁ ይዞ ስልክ እያነጋገረ አስፖልት በመሻገር ላይ ሳለ የመኪናዉን ፍጥነት መቆጣጠር ያቃተዉ አንድ ሾፌር ሀቢብ በሚሻገርበት መንገድ በፍጥነት መኪናዉን ሲያሽከረክር ተመለከተች። "ሀቢ...ብ" ብላ በቅጽበት የከደነቻቸዉን አይኖቿን ገልጣ በጎኗ በኩል የተንጠለጠለዉን ፎጣ አነሳች። ፎጣዉን በትክክል ሳታሸርጠዉ (ሳታገለድመዉ) ተቻኩላ ከሸዋር ቤት ወጣች።ሰዉነቷ እየተንቀጠቀጠ ነበር። ያየችዉ ክስተት በአይነ ህሊናዋ ሳይሆን በእዉኗ እስኪመስላት ድረስ ያጣፋችዉን ፎጣ በአንድ እጇ ጨምድዳ እንደያዘች ገላዋ ራደ - ተብረከረከች። ስልኳን አነሳችና ወደ ሀቢብ ደወለች። ╔═══❖•💕💕•❖═══╗ ይቀጥላል ╚═══❖•💕💕•❖═══╝ ❥............🍃👑👑🍃..............❥

2
ከዚህ በኋላ ድሮን የምንጠቀመው ሠርግ ለመቅረፅ ብቻ ነው! ሲሉ አንዳንድ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለፁ
351
3
በከንቱ አትጨነቅ! አንዳንዴ አንተ ስለተጨነክ ብቻ የማትቀይራቸው ነገሮች አሉ፤ ሸክላው ራሱን ከሚያውቀው በላይ ጠፍጥፎ የሰራው ሸክላ ሰሪው ጠንቅቆ ያውቀዋል፤ ካንተ በላይ የሚያውቅህና የሚያስብልህ አምላክ አለህ! በከንቱ መጨነቅ አቁም!
341
4
እኔ እኮ ከ ፋዘር ፀባይ ግርም የሚለኝ ቆይ የማዘርን ስም አያውቀውም "እናትህ" እያለ የሚጠራት?
339
5
#Mother:- አንተ ግን መች ለማግባት ወሰንክ... #Me:- ጦርነቱ አብቅቶ ሰላም ሲሰፍን..         አይደርስ መስሏት.... 🙄🙄
331
6
ውጭ ያለው ዘመዴ "DV ሙልተህ or እንደምንም ብለህ ና እንጂ ለሌላው እኔ አለሁልህ" ይለኛል እንዴ... ወዳጄ እንደምንም ብዬ ከመጣሁ በኋላ ምን ትሰራልኛለህ🤷‍♂
322
7
በዚህ ጦርነት መቼ ቢሆን ኑሮ በጣም እናደድ ነበር😉
311
8
​​🌿🌿"ጤዛዉ ፍቅሬ"🌿🌿 🌻🌻ክፍል አስራ ሶስት🌻🌻 ✍✍( እስማኤል መሀመድ)✍✍ .... አንድ ሀሳብ በአንድ ግለሰብ ዉስጥ ዉሎ ካደረ ለሰዉዬዉ ጭንቀትን እንጂ ሌላ ምንንም አያተርፍም። ይሄን ደግሞ ሀቢብ በራሱ ላይ ያረጋገጠዉ ነገር ነዉ። ጉድለት አለብሽ ፤ ሙሉ አልነበርሽም 'ለምን' ተብላ የምትጠየቀዉ ፎዚያ ሆና ሳለች ከእሷ በላይ ግን እሱ ተጨንቋል። 'የትኛዉ አጠያየቅ ትክክል ነዉ?' እያለ በማሰብ ላይ ሳለ በሀሳብ መንጎዱን ያስተዋለችዉ ፎዚያ ... ... "ንገረኛ ሀቢቢ ... '' ስትለዉ ደንገጥ አለና ..'እ' አለ። ... "የፈለግከዉን ጠይቀኝ ሁቢ ... ማወቅ ያለብክን ሁሉ ... እነግረሃለሁ። ካንተ ምንም ምደብቀዉ ነገር የለኝም።" አለችዉ። እሱ እንደሆነ አፉን ይዞታል። ቅንነቷና መልካምነቷ አንደበቱን አሳስሮታል። ፍቅር አሰጣጧ ልቡን ምንም ሳያስቀር እንዲሰጣት አስገድዷታል። ምክንያቱም ፎዚያ ሲበዛ ብልህ ናት። ዛሬ ሲቀርባትና ሲወዳት ብቻ ሳይሆን ያኔም በትድራቸዉ ላይ የጨለማን ጽልመት ሲያጠላበት ፤ እንደ አባቱ ገዳይ ሲጠላትና ሲያመናጭቃት በነበረችበት ጊዜ እንኳን እሱን ከማፍቀር አልቦዘነችም ነበር። ሲወጣም ሆነ ሲገባ እንክብካቤ በማብዛት ፤ ያንን ክፉ ፊት ተቋቁማ ፤ በክፉ ንግግሩ ዉስጧ እየደማ በመቻልና በመታገስ ትዳሯን በቋፍም ቢሆን አቆይታለች። በተለይ የአንዱ ቀን ስድቡ ልቧን ላይሽር የሰበረበት እለት የሚረሳ አልነበረም። "ርካሽ" ሲላት ስቅስቅ ብላ ያለቀሰችበት። በዉሃ ታጥቦ እንደተጠመዘዘ ጨርቅ የተንተራሰችዉ ትራስ ልብስ በእንባዋ ሲርስ የነበረችበት። ... አሁን ግን... ያንን ሁሉ ወደ ጎን ትታ ባሏ የሚሰጣትን ፍቅር መኮምኮምና ዉስጡን የሚያስጨንቀዉን ፤ ማወቅ የሚፈልገዉን እዉነቱን ነግራ ቀሪ ህይወቷን በደስታ ማሳለፍ ፤ ትዳሯን ሙሀባ ዉስጥ ነክራ የኑሮን ጥፍጥና ማጣጣም ፣ የዱንያን ፈተና በድል መወጣት - እዉን ልታደርግ የምትፈልግዉ ህልሟ ነዉ። .... "ፎዚዬ ..." አላት በድጋሜ። ስሟን እያቋላመጠ ፤ አስሬ እያቆለጳጰሰ ከመጥራት ዉጭ ደፍሮ የሚጠይቃት ሀሞቱ ፈሰሰበት። .... "ወይዬ ዉዴ... አታስጨንቀኛ! ,, የፈለከዉን ጠይቀኝ እኔ ምንም ቅር አይለኝም።" እያለች እንደ ህጻን ልጅ ታደፋፈረዉ ያዘች። ዉስጡ ታምቆ የቆየዉን የሀሳብ ክምር በሞቃት ትንፋሹ 'ኡፍፍፍ ...' ብሎ ካወጣ በኃላ ... .... "ፎዚዬ መጀመሪያ ያገባሁሽ ሰሞን ላንቺ ያለኝ ፍቅር ወደር የማይገኝለትና በቀላሉ የማይተመን ነበር። እመኒኝ ማሬ...! አሁንም ያ ስሜት ዉስጤ ላይ አለ...." አይን አይኑን እያየች ጆሯዋንም ልቧንም ከፍታ ከማዳመጥ ዉጭ የሚጠይቃትንና ማወቅ ያለበት ነገር ምን እንደሆነ በዉል አላወቀችዉም። ... ንግግሩን ቀጥሏል.... "ሀቢብቲ... በጣም ነዉ የምወድሽ ፤ ከልቤም አፈቅርሻለሁ። ነገር ግን ... አንድ ዉስጤን የሚከነክነኝ ነገር አለ። የማስበዉ ሀሳብ ፤ ስላንቺ የምገምተዉ ... እንደ ሰደድ እሳት ዉስጥ ዉስጤን እየፈጀ ከሚጨርሰኝ አዉጥቼዉ በግልጽ ልጠይቅሽ እፈልጋለሁ።..." ሲናገር እዉነትም የሆነ ዉስጡን የሚረብሸዉ ነገር እንዳለ ያስታዉቅበታል። ለሷ ፍቅር እንዳይሰጣትና እንዲጠላት ያደረገዉ አሁን የሚነግራት ነገር እንደሆነ አላጣችዉም። ይበልጥ ለማወቅ ጓጓች። ዉስጥን በሚያራራ ሁኔታ ድምጿን ቀነስ አድርጋ በለሆሳስ ... "ምንድን ነዉ እሱ የኔ ዉድ? ምንድን ነዉ ዉስጥህን የሚከነክንህ?..." አለችዉ። ... "ፎዚቲ አንቺ ከ'ኔ በብዙ ነገር ትሻያለሽ። በዚህም ላንቺ የነበረኝ ቦታ እጅግ የገነነ ነበር። በመኃል ግን ስሰጥሽ የነበረዉን ፍቅር ትቼ ፤ ሚስቴ በመሆንሽም ሁሉ ስማረር ነበር። ይሄ ሁሉ የሆነዉ ግን ባንድ ምክንያት ነዉ።..." አሁን ላይ ከሀተታዉ ይበልጥ መስማት የፈለገችዉ 'ሊጠላባት የቻለዉን ምክንያት ስለነበር..."እኮ ምንድን ነዉ ምክንያትህ?" ብላ በንግግሩ መሃል ገባች። ከዚህ በኃላ ወሬ መቀየርም አይችልም። ዳር ላይ ስለደረሰ ሊጠይቃት የሚፈልገዉን በግልጽ ሊጠይቃት ወሰነ። እንደምንም ከራሱ ጋር ታገለና "ክብረ..." ብሎ ቃሉን ሳይጨርሰዉ ስልኩ ጠራ ..."ዝ... ዝ... ዝ..." ንግግሩን አቋረጠና የደዋዩን ማንነት ሲያይ በስልኩ ላይ 'Hamza' ብሎ የመዘገበዉ ስልክ ቁጥር የጓደኛዉ ሀምዛ ነበር። ፎዚያ ዉስጧን የቁጣ ክርቢት ንዴቷን ጫረዉ። ቅስሟ የተሰበረ ያክል አንገቷን ወደ ታች ደፋችና በእጇ መዳፍ አገጯን ደገፍ አደረገች። ... "ኦህ ፎዚ... ለነሀምዛ ቆየሁባቸዉ!" ብሎ ሊያነጋግር የሚያስችለዉን ቁልፍ ተጭኖ .."ሄሎ" አለ። ፎዚን በተቀመጠችበት ትቷት ስልኩን እያነጋገረ ቁም ሳጥኑ ወዳለበት ክፍል ገባ። . ... 'ምን ሊጠይቀኝ ነበር?' ብላ ሀቢብ ገና ከቤት ሳይወጣ ጭንቀቷን ጀመረችዉ። 'እስከ'ዛሬ ትዳሬን የበጠበጥኩት እኔዉ 'ራሴ ነኝ ማለት ነዉ?' እያለች ያሳለፋቸዉና የተጓዘችበት ከሰላም የራቀችበትን መንገድ እያስታወሰች ራሷን ትረግም ገባች። 'ቆይ ግን ምክንያቱ ምን ነበር? ክብረ ብሎ የጀመረዉ ምን ሊል ነበር??" 'የምን ክብር ነዉ?' ... በዚህ መሃል ሀቢብ ልብሱን ልብሶ ከዉስጥ ብቅ አለ። ፎዚም ተነሳችና ወደ'ሱ ተጠጋች። ... "ሀቢቢ ..." አለችዉ። አሁን ፈርታለች። ሀቢብ ደግሞ ግማሽ ያክሉን የሀሳብ ቁልል ወደ'ሷ ንዶ ስላጋባባት ትንሽ ረፍት የተሰማዉ ይመስላል። ሀሳቡን ሙሉ ለሙሉ ባይገልጽላትም ስለጀመረዉ ከሀምዛ ዘንድ ሲመለስ መጨረስ እንደሚችልና ተነጋግረዉ ችግራቸዉን እንደሚፈቱት አምኗል። ... "ወይዬ የኔ ቆንጆ ..." ብሎ ፀጉሯን ባንድ እጁ እንደመዳበስ አደረጋት። እሷም የሸሚዙን ኮሌታ እንደማስተካከል እያደረገች አይኖቿን አይኖቹ ላይ አንከባለለቻቸዉ። ╔═══❖•💕💕•❖═══╗ ይቀጥላል ╚═══❖•💕💕•❖═══╝ ❥............🍃👑👑🍃............
345
9
ጤዛው ፍቅሬ አኋጊ የፍቅር ታሪክ ሊፈፀም ሶስት ክፍል ቀረው ይቀጥል👍 ይቅር👎
319
10
🌿🌿"ጤዛዉ ፍቅሬ"🌿🌿 🍂🍂ክፍል አስራ ሁለት🍂🍂 ✍✍እስማኤል መሀመድ ኡሙሁ አሚና አቡሁ አብደላህ..." የሚለዉ የፎዚያ የስልክ መጥሪያ እስከ ንዝረቱ 'ዝ... ዝ... ዝ...." እያለ የነሀቢብ ፍቅር ማድመቂያ መስሏል። ጆሯቸዉ ከአፍንጫቸዉና ከከናፍሮቻቸዉ መካከል ሾልኮ በሚወጣዉ ሞቃት ትንፍሽ ተደፍኗል። . .... ሀቢብ የፎዚያን ስሜት እየጠበቀ ከጠበቀችዉ በላይ አስደስቷታል። የደስታን ማማ አፈናጧታል። ጋደም ባለበት ፎዚን በቀኝ እጁ ወደ ደረቱ አስጠግቶ አቅፏት በግራ እጁ ያሰረዉን ሰአት ተመለከተ። ከቀኑ 11:25 ይላል። .."ያ አላህ ፎዚዬ ..." አለና ፎዚን ከእቅፉ ዉስጥ አዉጥቶ ተነሳ። እሷም በግንባሯ በኩል ወርዶ የተዘናፈለዉን ጸጉሯን በእጇ ወደ ኃላዋ መለስ እያደረገች ቀስ ብላ ጋደም ካለችበት ሶፋ እየተነሳች.... "ምን ሆንክብኝ ሀቢቢ?" አለችዉ። ..."ሀምዛን እስካሁን ሳልጠይቀዉ!" አላትና እየተቻኮለ ወደ ሸዋር ቤት አመራ። ፎዚያም ሰአቱ ስንት እንደሆነ ለማወቅ ተንተርሳዉ ከነበረችበት ትራስ ስር ስልኳን አዉጥታ ተመለከተች። ስንት ሰአት እንደሆነ ካወቀች በኃላ ቁጥሩን የማታዉቀዉ ስልክ ሰባት ጊዜ ደጋግሞ ተደዉሎባት ነበር። . . . .... "ግን ሀቢብ ምን ሆኖ ነዉ?" ንዴቷን ፊቷ ላይ አንጸባርቃ እየነገረችዉ ነበር። ...."መኪዬ ስለመምጣቱ ሳይሆን ስለደህንነቱ ተጨነቂ ... እሺ!" አላት ሀምዛ። ቀጠል አድርጎም ..."ሀቢብ ደህና ከሆነ ይመጣል። ለጓደኛዬ ዱዓ የማደርግለት በመንገዱ ላይ እንቅፋት እንዳያገኘዉና የ'ኔ እጣ እንዳይደርሰዉ ነዉ።" ብሎ በረዥሙ ትንፋሹን አወጣ። የ'ሱ ቅጽበታዊ አደጋ ለዘላለም ጎደሎ አድርጎ እንዳስቀረዉ ሁሉ ለጓደኛዉ ሀቢብም ይሄ ነገር እንዳይገጥመዉ በመመኘት ነበር። ...." እሱስ ልክ ነህ! ወጥቶ መቅረትም አለ።" አለች መኪያ። ይሄ መልሷ ለሀምዛም ይሆናል። ምክንያቱም ሀምዛ የደረሰበት ዱንያ ላይ ካሉ አደጋዎች ፤ ምድር ላይ ካሉ ችግሮች እጅግ በጣም ትንሹ ሊሆን ይችላል። ምክንያቱም 'ጫማ የለኝም ብለህ አትዘን እግር የሌላቸዉ አሉና!' አይደል ተረቱስ። ከቤታቸዉ እንደወጡ ያልተመለሱ ስንቶች አሉ - መንገድ ላይ በሚገጥማቸዉ አደጋ ህይወታቸዉ ላትመለስ ይከነፈችባቸዉ። ወይም ወደቤታቸዉ ሲመለሱ ቤታቸዉ አልሆኑ ሆኖ ቤት ንብረታቸዉን ፤ ሚስት ልጆቻቸዉን በአደጋ አጥተዉ ህይወት የጨለመችባቸዉ እልፍ ሰዎች እንዳሉ የማይካድ ሀቅ ነዉ። ከነዚህ ሁሉ ፈተናዎች ምናልባትም የሀምዛ ቀላሉ ነበር። 'ወጥቶ መቅረትም አለ' ስትለዉ እዉነት መሆኑን ለማረጋገጥ ያክል ራሱን በአዎንታ ወደ ታችና ወደ ላይ ከፍ ዝቅ አድርጎ ነቀነቀ። . ..."ለይሰል ገሪቡ... ገሪብ አሽ-ሻሚ ወል የመኒ ወላኪነል ገሪበ ... ገሪብ ወለህዲ ወል ከፈኒ ዛሬ የሌሉ ከኛ ጋራ... ትናንት አብረዉን የኖሩ ከመሬት በታች የገቡ ...የተጫናቸዉ አፈሩ እሩቅ አስበዉ በተስፋ... ዳሩ ግን ባጭር የቀሩ የራቁን የረሳናቸዉ ብዙ ወንድሞች ነበሩ....." የሚለዉ የሙሀመድ አወል ነሽዳ ከመኪያ ፖርሳ ዉስጥ ተሰማ - ስልኳ እየጠራ ነበር። ነሽዳዉ አቋርጡኝ አቋርጡኝ አይልም። በተስረቅራቂ ድምፁ ያዜማዉ ነሽዳ ቢሰማ የማይጠገብና የማይሰለች ነዉ። ይበልጥ ከሚያወሩት ርዕስ ጋር ስለገጠመ ተመሰጡብኝ ፤ አስተንትኑብኝ እንጂ ዝጉኝ አይልም - መካሪና ገሳጭ የሆነ ነሽዳ ነበር። መኪያ የፖርሳዋን መቆፊያ ዚፑን ከከፈተች በኃላ ስልኩን አወጣች። ..."የፎዚያ ቁጥር ነዉ" አለችዉ። ሀምዛም አንገቱን መለስ አድርጎ አያት። አንሽዉና አናግሪያት ማለቱ ነበሩ። አይኖቹ እንጂ ልሳኖቹ አላናገራትም። ..."ሄሎ አሰላሙዓለይኩም" አለች መኪያ። ከወዲያ ማዶ ሆና የምታወራዉ ፎዚ የሰላምታዉን መልስ ከመለሰች በኃላ የመኪያን ስልክ ቁጥር ስላላወቀች ማንነቷን ጠየቀቻት። ..."መኪያ ነኝ ፎዚ.. የሀቢብ ስልክ አይሰራም አንቺም አልመለሽልኝም። ችግር አለ እንዴ ፎዚ!?" ብላ ጠየቀቻት። ሀምዛን የሚያስጨንቀዉና የሚያሳስበዉ የሀቢብንና የፎዚያን ወደ ሆስፒታል መምጣት ሳይሆን ደህንነታቸዉንና በመካከላቸዉ እርቅ መስፈኑን፤ በፍቅር አንድ መሆናቸዉን ነዉ። የሄን የምታዉቀዉ መኪያ ሀምዛ በሚፈልገዉ መልኩ ፎዚያን እያናገረቻት ነዉ። በዚህ መካከል ሀቢብ ከሸዋር ቤት ሰዉነቱን በፎጣ እየጠረገ ወጣ። ፎዚያ ለመኪያ የምትነግራት ምክንያት ስላጣች ሀቢብ ከሸዋር እስኪወጣ ተጠባብቃ መኪያን እንዲያናግራት ስልኩን አቃበለችዉ። አንገቱን ወደ ላይና ወደ ታች እየነቀነቀ 'ማን ነዉ?' በሚል አይነት ሁኔታ ጠየቃት። ድምጿን ከፍ ሳታደርግ ከንፈሯንና ምላሷን ብቻ በማንቀሳቀስ ... "መ....ኪ....ያ ...ና...ት" አለችዉ። . ..."መኪ አሰላሙአለይኪ እንዴት ነሽ?" ብሎ ሞቅ ያለ ሰላምታ አቀረበላት። የጓደኛዉን ጉድ አላወቀ ... ... "ወአለይኩም ሰላም ደህና ነህ?" በማለት መልሳ የሱን ደህንነቱን ጠየቀችዉ። የሷን ደህንነት ግን አልነገረችዉም። ምክንያቱም ደህና አይደለችም!። ባሏ በሚሰቃዬዉ ህመም የሷም ዉስጧ ታሟል። ... "አልሀምዱሊላህ ... ሀምዛ እንዴት ነዉ!?" ለመጠየቅ ያክል እንጂ ከሀምዛ ከተለዬ ብዙም አልቆየም። ሀቢብን ከሆስፒታል ወደ ቤቱ አላህ የወሰደዉ የሀምዛን አስደንጋጭ ዜና እንዳይሰማና ከፎዚያ ጋር ጣፋጭ የሆነ የፍቅር ጊዜን እንዲያሳልፍ ሽቶ ይመስላል። ... መኪያ ጭንቀትና ሀሳብ ያሞቀዉን ትንፋሿን በረጅሙ 'ኡህህህፍፍፍ...." ብላ አወጣች። ያወጣዉ ትንፋሽ በጣም ከመሞቁ የተነሳ ፊት ለፊቱ የፕላስቲክ ፌስታል ቢያገኝ ለማጨማድድ የሚያንስ አልነበረም። ... "አልሐምዱሊላህ ያዉ ነዉ..." ... "መጣሁ በቃ መኪ .. ብዙ አትጨነቂ" አላት። መኪያ መንታ ሀሳብ ዉስጥ ሆና ተወዛገበች 'ልንገረዉ ወይንስ ሲመጣ ይሻላል?' እያለች ከራሷ ጋር ስትወያይ ... ሀቢብ "ቻዉ መኪ" ብሎ ስልኩን ዘጋዉ። . ... ፎዚያ አይን አይኑን እያየችዉ ነበር። ዘወር ብሎ ሲመለከታት ሶፋዉ ላይ ተቀመጣ ትቁለጨለጫለች። የሆነ ነገር እንዲላትና እንደሚወዳት እንዲነግራት ፈልጋለች። ... "የኔ ቆ..ን..ጆ...." ብሎ ከተቀመጠችበት ጎን ሂዶ ተቀመጠ። ... "ወይዬ ሁቢ" ስትለዉ ወደ ደረቱ አስጠግቶ እቅፍፍ.. አደረጋት። ፍጹም ሰላም ፤ ልዩ ደስታና ዘላለማዊ ሀሴት በይቅርታ ዉስጥ እንደ ወንዝ ዥረት በዝቶ ይገኛል። ይቅርታ ህመምን ያሽላል ፤ ዉሳኔንና ህግን ያሽራል። የዚህ ዉድ ነገር ባለቤቶች ግን ጠንካራ ሰዎች ናቸዉ። ፎዚ ደግሞ በዚህ አትታማም። እንኳን እሱዉ ይቅርታ ጠይቋትና ራሷ ሂዳ ይቅርታ ላድርግልህ ፍቅራችንን እናድስ እያለች ደጅ የምትጠና ልበ ብርቱ ሴት ናት። ... "እስከዛሬ ላደረግኩሽ ፣ ላስቀየምኩሽና ለበደልኩሽ ሁሉ ከልብ የሆነ ይቅርታሽን እፈልጋለሁ።" አላት። በአይኖቹ አይኖቿን እያየ ዉስጧን ሰርስሮ ልቧ ድረስ ዘልቋል። አሁን አንደበታቸዉ ብቻ ሳይሆን ልባቸዉም ሌላ ዉይይት ይዟል። ሀቢብ ድንግል ያልነበረችበት ምክንያት ምን እንደሆነ ከይቅርታዉ በኃላ ሊጠይቃት ወስኗል። ግን ደግሞ 'እንዳዲስ በግድ ያገኘሁትን ፍቅር የማይሆን ጥያቄ ጠይቄ ባስቀይማትስ' ብሎ ፈራ። 'እሷስ በጥያቄዬ ተናዳብኝ መጥፎ መልስ ብትመልስልኝ የሚታገስ ልብ ይኖረኝ ይሆን?' ሙግቱ ከራሱ ጋር ነዉ። ይሄን እያሰበ ፎዚያ ትክ ብላ ስታዬዉ ቆይታ.... "ሀቢቢ የኔ ዉድ..." አለችዉ ይቀጥላል.....
319
11
#ታካሚ:- ዶክተር አፕራሲዮን ስደረግ የመጀመሪያዬ ነው በጣም  ፈራውት በናትህ #ዶክተር:-አታስብ እኔም የመጀመርያዬ ነው 😂
279
12
የማያልፍ የለም ሁሉም ያልፋል ግን በናታችሁ አትጋፉ😍🤗
269
13
ዛሬ አንድ ሱቅ ውስጥ የቀድሞ ፍቅረኛዬ ፍቅረኛዋን ከፊት ለፊቴ እየሳመች አገኘኋቸው፣ እያየዋቸው ነበር። አየችኝ ከዛ የበለጠ ሳመችው እና እዚህ ምን እየሰራሁ እንደሆነ ጠየቀችኝ?. ባለቤቴ አርግዛ መውለዷን ነገርኳት እና እኔ እዚህ የመጣሁት የልጅ እቃዎችን ለመግዛት ነው በጣም ደስተኛ ነኝ ምናምን ብዬ አቀሳሰርኩ እና  ሱቅ ውስጥ ገባሁ እሷ እያየችኝ ዳይፐር ፣የህፃን ወንበር እና የህፃን አልጋ ስፖንጅ  ፣ብስክሌት ፣የህጻን ልብስ እና የመሳሰሉትን ገዛሁ ከዛ Ride ደወልኩና እቃውን ጭኜ ሄድኩ። እሷ እና የወንድ ጓደኛዋ ተመስጠው እየተመለከቱኝ ነበር እና ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ነበር የሄድኩት... አሁን ወደ ቁም ነገሩ ስገባ የወለደች ሴት የምታውቁ  ዳይፐር፣ የልጅ መቀመጫ ወንበር፣ የአልጋ ስፖንጅ፣ ብስክሌት እና የህፃን ልብስ በተመጣጣኝ ዋጋ እየሸጥኩ ነው ሚገዛኝ ካለ ወዲህ በሉ 😭
279
14
.ጀለስ ሱሪው በጣም ሰፊ ከመሆኑ የተነሳ አንድ እርምጃ ለመራመድ *ሱሪው ውስጥ ሁለቴ ይራመዳል👀
338
15
​🌿ጤዛው ፍቅሬ🌿 🌹ክፍል 11🌹 ✍✍እስማኤል መሀመድ .... "ወይዬ ሀቢቢ..." አለችዉ። በአይኖቿ አይኖቹን ስታይ የመጀመሪያዉን ሀቢብ ሆኖ አገኘችዉ። ፍቅርን እንጂ ጸብን የማያዉቀዉ ሀቢብ! - ፍፁም ተቀይሯል። ያን መጥፎ ባህሪ አስወግዶ ወደራሱ ማንነት ተመልሷል። ..ያን ጣፋጭ ጠረን ካገኘዉ ቆይቷል። ፍቅሯን ሁሌም ባትነፍገዉም በራሱ ሽሽት ግን ገላዋን ከማቀፍ ፤ ጸጉሯን እየደባበሰ ከንፈሯን ከመሳም ርቆ ኑሯል። ሁለቱም ተርበዋል። ከየት እንደሚጀምርና እንዴት ሊያስደስታት እንደሚችል ተደናግሮታል። ......"ታዉቂልሽ ማሬ?" አላት። ......"ምኑን ሀቢቢ?" ......"ልቤ ማፍቀር ከሚችለዉ በላይ እንደማፈቅርሽ!" ድምጹ ልስልስ ያለ ለጆሮ የማይጎረብጥ ፤ ሀሴትን የሚያፈናጥጥ በመሆኑ ዉስጧ በፌሽታ ተሞላ። አይታዉ የማታዉቀዉ አለም ዉስጥ የገባች መሰላት። ምንም ጠራራ ፀሐይ የወጣበት ከቀኑ ስምንት ሰአት ቢሆንም የቤቱ በርና መስኮቶች ተዘጋግተዉ ቤቱ ጨልሟል። እንደተከዘ ህፃን ልጅ ቡዝዝ ፍዝዝ ብላ የምትበራዉ መብራት ፎዚን በዉብት ላይ ዉበት አክሎላታል። .... እጆቿን አንገቱ ላይ ጣል አድርጋቸዉ እሱም ቀጭን ወገቧን በእጆቹ ይዞ ጣፋጭ ጠረኗን እየማገ አንገቷ ስር ዉትፍ ብሏል።.... . . .... ነርሶቹ ሀምዛን አይተዉት ከሄዱ በኃላ በመኪያና በሀምዛ መካከል የዝምታ አዋጅ የተጣለባቸዉ እስኪመስል ድረስ ተኮራርፈዉ ዝምታ በመካከላቸዉ ነግሷል። ቀደም ብሎ ዶክተሩ መኪያን አስጠርቷት የሀምዛ እግሮች ወደ ቀድሞ ሁኔታዉ መመለስ እንደማይችልና ቀሪ ህይወቱን ዊልቸር ላይ ሆኖ እንደሚያሳልፍ አርድቷታል። አላርፍ ያለች ነርስ ደግሞ በማያገባት ጥልቅ ብላ...."አይይ ይሄ እግር ቢቆረጥ እንጂ ከዚህ በኃላ እንኳ አያገለግልም።" ብላ በሁለቱም ፊት ላይ ጨለማ ጥላዉን እንዲያጣላ ፈረደችባቸዉ። ሁለቱም ተፈራርተዋል። መኪያ ቀና ብላ ሀምዛን ስታዬዉ ከአጠገቧ የሀምዛ ዛቱ እንጂ ሙሉ ሆኖ ከአጠገቧ እንደሌለ ፊቱ ላይ ተመለከተች። ..."ይሄዉልህ ዉዴ...." ብላ ጸጥታ የነገሰችበትን ክፍል ፈራ ተባ እያለች ምናልባት ከሰማኝ ብላ ንግግሯን ጀመረች። ነገር ግን ሀምዛ አልነቃም። የሚጓዝበት አለም የማይገፋ ፤ የሚሄድበት መንገድ የማያልቅ ፤ የሚቀዝፈዉ ዉቅያኖስ ክንድን የሚፈትን... ማዶን ተሻግሮ ሲመለከተዉ እንደ ሀረግ ዉስብስቡ የበዛ ሆኖ ታየዉ። ....."ጠንካራ አልነበርክ'ዴ ዉዴ? ለምን በቀላሉ ትሸነፋለህ?" እያለች የዉስጧን ህመም ፤ የባሏን ጉዳትና ስቃይ በዉስጧ አምቃ ይዛ እሱን ለማበረታታት ተቀምጣ ከነበረበት እግርጌዉ ወደ ራስጌዉ ተጠጋች። ....."ትዕግስት ማድረግኮ አለብህ ሁቢ ... ደግሞስ አላህ የወሰነዉና እሱ የፈለገዉን የሚያደርግ የሚያደርግ ጌታ መሆኑን ዘንግተህዉ ነዉ?" በእጇቿ የሀቢብን አገጭ ይዛ ወደ'ሷ አዞረችዉ። ፊቱ ኩስምን ፤ ሰዉነቱ ምንምን ብሏል። "ሀቢቢ አናግረኛ!!... አላህ እንደሚወድህ ለምን ትረሳለህ? እሱ የወደደዉን ባሪያዉን ወንጀሉን ሊያብስለት ሲፈልግ አይደል የሚፈትነዉ። ያ የሚሆነዉ ደግሞ ተወዳጁ የአላህ ባሪያ በሚደርስበት ፈተና ላይ ሶብር ሲያደርግ ነዉ። ሶብር...!!።" ታወራለች እንጂ ከልቡ አልሰማትም ፤ ከዉስጡ አላዳመጣትም። እንደምታወራ እንጂ ምን እንደምታወራ ፤ ስለምን እንደምታወራና ለምን እንደምታወራ በዉል አያዉቀዉም። "ሀምዛ... ሀምዛ" አለችዉ። በተዳከመ ድምጽ "ወይ መኪ" አላት። እስኪ ለሀቢብ ደውልለት አለችው ምናልባት ይሄን ትካዜ ሀቢብ መጥቶ ቢያፅናናውና ስለሌላ ጉዳይ እያወራው የተወሰነ ቢረሳው ብላ በመመኘት ነው። ሀምዛ"እሺ"አላተና ወደ መስኮቱ አቅጣጫ አንቱን ቀለበስ አደረገ። .... "ደውልለታ ሀምዛ እሺ አባባሉ እሷን ላለመቃረን እንጂ ለመደወል እንዳልሆነ ገብቷታታል።.."እንደዉም እኔ እደዉልለታለሁ" ብላ የእጅ ቦርሳዋን ፍለጋ ተነሳች። እሱ ግን የምትናገረዉንና የምታዘዉን ከማዳመጥ ዉጭ ምንም አይነት ምላሽ አልሰጣትም። ስልኳን ከቦርሳዋ አወጣችና የሀቢብን ቁጥር ተጫነች 091471። የደወሉላለቸዉ ደንበኛ........ "ኤጭ ይቺ ደግሞ...." ብላ ብላ ስልኩን ዘጋችዉና እንደገና ደወለች። . . .... ሀቢብና ፎዚ የጦፈ ፍቅር ዉስጥ ናቸዉ። አንዳቸዉ አንዳቸዉ ላይ ተለጣጥፈዉ አንድ አካል ፤ አንድ አምሳል እስኪመስሉ ድረስ ተቃቅፈዋል። በመካከላቸዉ ማስቲሽ ያጣበቃቸዉ እስኪመስል ድረስ ሙቀቱ አቆራኝቷቸዋል። የፎዚ ትንፋሽ ቁርጥ ቁርጥ እያለ ስሙን በየመሀሉ ትጠራዋለች። የሀቢብ ስም በሙሉዉ ቢጠራም የተቆላመጠ ይመስላል። ሀቢብ... ሀቢቢ... ሁቢ የሀቢብ ወላጆች ለፎዚያ መጥራት እንዲመቻት ተመካክረዉ ያወጡለት እስኪመስል ድረስ ገርቶላታል። ሀቢብ ከዚህ በፊት ፎዚን የማያዉቃት መስሎ እስኪሰማዉ ድረስ ጣፍጭ ሆናለታለች። ፀጉሯን እየደባበሰ ፤ መላ አካላቶቿን በጣቹ እያመሰ የቱን ስሞ የቱን እንደሚተወዉ ግር አለዉ። ከናፍሮቿ....፤ ጉንጮቿ....፤ የአንገቷ ጠረን ... እያንዳንዱ ገላዋን ማር የተቀባችዉ ይመስል የሀቢብ ከናፍሮች ፎዚን አልጠግባት ብለዋል። አንዱን እየሳመ ፤ አንዱን እየላሰ እንደተቃቀፉ ከፎዚ ኃላ ከነበረዉ ሶፋ ላይ ተያይዘዉ ወደቁ።.... . . . ..... መኪያ የሀቢብ ስልክ ባለመስራቱ እንደመበሳጨት ብላለች። "ቆይ አሁን ስለኩን ለምን ዘጋዉ?" ብላ የሀምዛን አይኖች አየቻቸዉ። ሀምዛም "በፎዚያ ሞክሪ..." አላትና ያቋረጠዉ ህልም እንዳለ አይኖቹን ግጥም አደረጋቸዉ። ትእግስት በማጣትና ተስፋ በመቆረጥ መካከል እንዳለ ሁኔታዉን አይቶ መገመት አያዳግትም። ነገር ግን መኪያም ተመሳሳይ ስሜት ዉስጥ በመሆኗ የሀቢብን መምጣትና ሀምዛን እንዲያበረታዉ ተመኘች እንጂ የሀምዛን ሁኔታ ለመረዳት አቀበት ሆኖባታል። ከብዷታል። .... "የፎዚን ስልክ ቁጥርኮ አላዉቀዉም" አለችዉ። .... "09 23 " ብሎ ነገራት። መኪያም ወደ ፎዚ ስልክ ደወለች። . . . ..... "ሙሀመድ ነቢና ኡሙሁ አሚና አቡሁ አብደላህ....." እያለ የሚጠራዉ የፎዚያ ስልክ አቃጨለ። ነገር ግን ሀቢብም ፣ ፎዚያም አልሰሙትም። የጋለ ስሜት ዉስጥ ናቸዉ። እንኳን የስልክ ጥሪና አጠገባቸዉ ብየዳጠቤት ቢከፈት የግላይንደር ድምጽ የሚያነቃቸዉ አይመስሉም። ለሀቢብ ከዚህ ድምጽ በላይ በለሰለሰ ድምጿ 'ሁቢ' የምትለዉ የፎዚያ ጥሪ ገኖ ይሰማዋል። ይሳሳማሉ ... እ.... እ.... . . . ...."አትመልስም" አለችዉ። ...."ተይዉ በቃ ምልክቱንጨስታየዉ መልሳ ትደዉላለች" ...." ቆይ ደግሜ ልደዉል..." አለችና በድጋሜ ደወለች። . "ሙሀመድ ነቢና ኡሙሁ አሚና አቡሁ አብደላህ...." ይቀጥላል....
323
16
​🌿ጤዛው ፍቅሬ🌿 🌹ክፍል 11🌹 ✍✍እስማኤል መሀመድ .... "ወይዬ ሀቢቢ..." አለችዉ። በአይኖቿ አይኖቹን ስታይ የመጀመሪያዉን ሀቢብ ሆኖ አገኘችዉ። ፍቅርን እንጂ ጸብን የማያዉቀዉ ሀቢብ! - ፍፁም ተቀይሯል። ያን መጥፎ ባህሪ አስወግዶ ወደራሱ ማንነት ተመልሷል። ..ያን ጣፋጭ ጠረን ካገኘዉ ቆይቷል። ፍቅሯን ሁሌም ባትነፍገዉም በራሱ ሽሽት ግን ገላዋን ከማቀፍ ፤ ጸጉሯን እየደባበሰ ከንፈሯን ከመሳም ርቆ ኑሯል። ሁለቱም ተርበዋል። ከየት እንደሚጀምርና እንዴት ሊያስደስታት እንደሚችል ተደናግሮታል። ......"ታዉቂልሽ ማሬ?" አላት። ......"ምኑን ሀቢቢ?" ......"ልቤ ማፍቀር ከሚችለዉ በላይ እንደማፈቅርሽ!" ድምጹ ልስልስ ያለ ለጆሮ የማይጎረብጥ ፤ ሀሴትን የሚያፈናጥጥ በመሆኑ ዉስጧ በፌሽታ ተሞላ። አይታዉ የማታዉቀዉ አለም ዉስጥ የገባች መሰላት። ምንም ጠራራ ፀሐይ የወጣበት ከቀኑ ስምንት ሰአት ቢሆንም የቤቱ በርና መስኮቶች ተዘጋግተዉ ቤቱ ጨልሟል። እንደተከዘ ህፃን ልጅ ቡዝዝ ፍዝዝ ብላ የምትበራዉ መብራት ፎዚን በዉብት ላይ ዉበት አክሎላታል። .... እጆቿን አንገቱ ላይ ጣል አድርጋቸዉ እሱም ቀጭን ወገቧን በእጆቹ ይዞ ጣፋጭ ጠረኗን እየማገ አንገቷ ስር ዉትፍ ብሏል።.... . . .... ነርሶቹ ሀምዛን አይተዉት ከሄዱ በኃላ በመኪያና በሀምዛ መካከል የዝምታ አዋጅ የተጣለባቸዉ እስኪመስል ድረስ ተኮራርፈዉ ዝምታ በመካከላቸዉ ነግሷል። ቀደም ብሎ ዶክተሩ መኪያን አስጠርቷት የሀምዛ እግሮች ወደ ቀድሞ ሁኔታዉ መመለስ እንደማይችልና ቀሪ ህይወቱን ዊልቸር ላይ ሆኖ እንደሚያሳልፍ አርድቷታል። አላርፍ ያለች ነርስ ደግሞ በማያገባት ጥልቅ ብላ...."አይይ ይሄ እግር ቢቆረጥ እንጂ ከዚህ በኃላ እንኳ አያገለግልም።" ብላ በሁለቱም ፊት ላይ ጨለማ ጥላዉን እንዲያጣላ ፈረደችባቸዉ። ሁለቱም ተፈራርተዋል። መኪያ ቀና ብላ ሀምዛን ስታዬዉ ከአጠገቧ የሀምዛ ዛቱ እንጂ ሙሉ ሆኖ ከአጠገቧ እንደሌለ ፊቱ ላይ ተመለከተች። ..."ይሄዉልህ ዉዴ...." ብላ ጸጥታ የነገሰችበትን ክፍል ፈራ ተባ እያለች ምናልባት ከሰማኝ ብላ ንግግሯን ጀመረች። ነገር ግን ሀምዛ አልነቃም። የሚጓዝበት አለም የማይገፋ ፤ የሚሄድበት መንገድ የማያልቅ ፤ የሚቀዝፈዉ ዉቅያኖስ ክንድን የሚፈትን... ማዶን ተሻግሮ ሲመለከተዉ እንደ ሀረግ ዉስብስቡ የበዛ ሆኖ ታየዉ። ....."ጠንካራ አልነበርክ'ዴ ዉዴ? ለምን በቀላሉ ትሸነፋለህ?" እያለች የዉስጧን ህመም ፤ የባሏን ጉዳትና ስቃይ በዉስጧ አምቃ ይዛ እሱን ለማበረታታት ተቀምጣ ከነበረበት እግርጌዉ ወደ ራስጌዉ ተጠጋች። ....."ትዕግስት ማድረግኮ አለብህ ሁቢ ... ደግሞስ አላህ የወሰነዉና እሱ የፈለገዉን የሚያደርግ የሚያደርግ ጌታ መሆኑን ዘንግተህዉ ነዉ?" በእጇቿ የሀቢብን አገጭ ይዛ ወደ'ሷ አዞረችዉ። ፊቱ ኩስምን ፤ ሰዉነቱ ምንምን ብሏል። "ሀቢቢ አናግረኛ!!... አላህ እንደሚወድህ ለምን ትረሳለህ? እሱ የወደደዉን ባሪያዉን ወንጀሉን ሊያብስለት ሲፈልግ አይደል የሚፈትነዉ። ያ የሚሆነዉ ደግሞ ተወዳጁ የአላህ ባሪያ በሚደርስበት ፈተና ላይ ሶብር ሲያደርግ ነዉ። ሶብር...!!።" ታወራለች እንጂ ከልቡ አልሰማትም ፤ ከዉስጡ አላዳመጣትም። እንደምታወራ እንጂ ምን እንደምታወራ ፤ ስለምን እንደምታወራና ለምን እንደምታወራ በዉል አያዉቀዉም። "ሀምዛ... ሀምዛ" አለችዉ። በተዳከመ ድምጽ "ወይ መኪ" አላት። እስኪ ለሀቢብ ደውልለት አለችው ምናልባት ይሄን ትካዜ ሀቢብ መጥቶ ቢያፅናናውና ስለሌላ ጉዳይ እያወራው የተወሰነ ቢረሳው ብላ በመመኘት ነው። ሀምዛ"እሺ"አላተና ወደ መስኮቱ አቅጣጫ አንቱን ቀለበስ አደረገ። .... "ደውልለታ ሀምዛ እሺ አባባሉ እሷን ላለመቃረን እንጂ ለመደወል እንዳልሆነ ገብቷታታል።.."እንደዉም እኔ እደዉልለታለሁ" ብላ የእጅ ቦርሳዋን ፍለጋ ተነሳች። እሱ ግን የምትናገረዉንና የምታዘዉን ከማዳመጥ ዉጭ ምንም አይነት ምላሽ አልሰጣትም። ስልኳን ከቦርሳዋ አወጣችና የሀቢብን ቁጥር ተጫነች 091471። የደወሉላለቸዉ ደንበኛ........ "ኤጭ ይቺ ደግሞ...." ብላ ብላ ስልኩን ዘጋችዉና እንደገና ደወለች። . . .... ሀቢብና ፎዚ የጦፈ ፍቅር ዉስጥ ናቸዉ። አንዳቸዉ አንዳቸዉ ላይ ተለጣጥፈዉ አንድ አካል ፤ አንድ አምሳል እስኪመስሉ ድረስ ተቃቅፈዋል። በመካከላቸዉ ማስቲሽ ያጣበቃቸዉ እስኪመስል ድረስ ሙቀቱ አቆራኝቷቸዋል። የፎዚ ትንፋሽ ቁርጥ ቁርጥ እያለ ስሙን በየመሀሉ ትጠራዋለች። የሀቢብ ስም በሙሉዉ ቢጠራም የተቆላመጠ ይመስላል። ሀቢብ... ሀቢቢ... ሁቢ የሀቢብ ወላጆች ለፎዚያ መጥራት እንዲመቻት ተመካክረዉ ያወጡለት እስኪመስል ድረስ ገርቶላታል። ሀቢብ ከዚህ በፊት ፎዚን የማያዉቃት መስሎ እስኪሰማዉ ድረስ ጣፍጭ ሆናለታለች። ፀጉሯን እየደባበሰ ፤ መላ አካላቶቿን በጣቹ እያመሰ የቱን ስሞ የቱን እንደሚተወዉ ግር አለዉ። ከናፍሮቿ....፤ ጉንጮቿ....፤ የአንገቷ ጠረን ... እያንዳንዱ ገላዋን ማር የተቀባችዉ ይመስል የሀቢብ ከናፍሮች ፎዚን አልጠግባት ብለዋል። አንዱን እየሳመ ፤ አንዱን እየላሰ እንደተቃቀፉ ከፎዚ ኃላ ከነበረዉ ሶፋ ላይ ተያይዘዉ ወደቁ።.... . . . ..... መኪያ የሀቢብ ስልክ ባለመስራቱ እንደመበሳጨት ብላለች። "ቆይ አሁን ስለኩን ለምን ዘጋዉ?" ብላ የሀምዛን አይኖች አየቻቸዉ። ሀምዛም "በፎዚያ ሞክሪ..." አላትና ያቋረጠዉ ህልም እንዳለ አይኖቹን ግጥም አደረጋቸዉ። ትእግስት በማጣትና ተስፋ በመቆረጥ መካከል እንዳለ ሁኔታዉን አይቶ መገመት አያዳግትም። ነገር ግን መኪያም ተመሳሳይ ስሜት ዉስጥ በመሆኗ የሀቢብን መምጣትና ሀምዛን እንዲያበረታዉ ተመኘች እንጂ የሀምዛን ሁኔታ ለመረዳት አቀበት ሆኖባታል። ከብዷታል። .... "የፎዚን ስልክ ቁጥርኮ አላዉቀዉም" አለችዉ። .... "09 23 " ብሎ ነገራት። መኪያም ወደ ፎዚ ስልክ ደወለች። . . . ..... "ሙሀመድ ነቢና ኡሙሁ አሚና አቡሁ አብደላህ....." እያለ የሚጠራዉ የፎዚያ ስልክ አቃጨለ። ነገር ግን ሀቢብም ፣ ፎዚያም አልሰሙትም። የጋለ ስሜት ዉስጥ ናቸዉ። እንኳን የስልክ ጥሪና አጠገባቸዉ ብየዳጠቤት ቢከፈት የግላይንደር ድምጽ የሚያነቃቸዉ አይመስሉም። ለሀቢብ ከዚህ ድምጽ በላይ በለሰለሰ ድምጿ 'ሁቢ' የምትለዉ የፎዚያ ጥሪ ገኖ ይሰማዋል። ይሳሳማሉ ... እ.... እ.... . . . ...."አትመልስም" አለችዉ። ...."ተይዉ በቃ ምልክቱንጨስታየዉ መልሳ ትደዉላለች" ...." ቆይ ደግሜ ልደዉል..." አለችና በድጋሜ ደወለች። . . "ሙሀመድ ነቢና ኡሙሁ አሚና አቡሁ አብደላህ...." ╔═══❖•💕💕•❖═══╗ ይቀጥላል ከ 200 ❤️ like በኋላ ╚═══❖•💕💕•❖═══╝ ❥............🍃👑👑?..............❥ 🌹ቶሎ እንዲቀጥል Like🌹
1
17
እኔኮ ..... ስልኬ ጠፋ ብዬ . . የስልኬን መብራት አብርቼ😀 ስልኬን📱 ምፈልግ የዋህ ነኝ #እስኪ_አንዴ_ሳቁብኝ🤣🤣
272
18
😌😌 ሰበር ዜና 🤣🤣 አንዷ ቸከስ አሟት HOSPITAL ለ 2 ወር እየተመላለሰች ብትታከምም ምንም አልሻላት ሲል....... . . . በመጨረሻም ዶክተሮቹ ባደረጉት የአንድ ወር ጥናት መሰረት መርፌ ስትወጋ የነበረችው Artificial ቂጧ ላይ መሆኑን አረጋገጡ።🤣🤣🤣🤣🤣🤣🤣🤣🤣🤣🤣🤣
289
19
ለ ፍቅር ያለህ አመለካከት ግን እንዴት ደስ ይላል ለምን አንጋባም?ስትለው ምን አላት... አስቴር አወቀ እንኳን ያን ሁሉ የፍቅር ዘፈን ዘፍና ባል የላትም ሴቲዮ🤔🙄🏃
266
20
እናቴማ ጨዋ ልጅ ነበር ያሳደገችው... እኔ ነኝ እንጂ እናንተን አስቃለው ብዬ የባለኩት
287