ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።
Kanalga Telegram’da o‘tish
📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623
Ko'proq ko'rsatish3 303
Obunachilar
-224 soatlar
-107 kunlar
-3830 kunlar
Postlar arxiv
አሐቲ ድንግልን የተወሰነ ቅጅዎች አለን በመደብራችን ታገኛላችሁ።
ቅድስት ቤተ-ክርስቲያን አምጣ የወለደችው የመምህረ ወንጌል የዲ/ን ያረጋል አበጋዝ የተወሰኑ የመጽሐፍ
ቅጂዎች ስላሉን ማግኝት ትችላላችሁ።
በግዮን መጽሐፍ መደብር ደርዛቸውን የጠበቁ ነባርና አዳዲስ መጽሐፍቶችን ያገኛሉ። ለበለጠ መረጃ
በ0913083816/0931144330
"የክርስቶስ ቤዛነት ይህ ነው፦ እርሱ ስለተሸከማቸው ዘግናኝ ሕማሞች እና ኃጢኣቶች እስካሁን ድረስ ያለማቋረጥ ይናገራል። ኃጢኣት የማያውቀውን እርሱን እግዚአብሔር አብ ስለእኛ ሲል 'ኃጢኣት እንዲሆን' አደረገው። አመንዝራው፣ ስድ ሆኖ የሚበድለው፣ ቆሻሻ በሆኑ ተግባራት አረንቋ ውስጥ የሚዛቅጠው እና ኃፍረት አልባ በሆኑ ተግባራት የሚበላሸው ሁሉ ከክርስቶስ ሲሸሽ ድምጹ በኋላው ይከተለዋል። ይኸውም 'የተወደድህ ልጅ ሆይ፥ ና! ኃጢኣቶችህ ከእኔ ጋር ናቸው፤' እያለ የሚጣራ የእግዚአብሔር ልጅ ደም ነው! ገና የሠራሃቸው ዕለት ነው በምልዓት የተሸከምኳቸው። ካሣውን ከፍያለሁ፦ ሐፍረት ተጭኖብኛል፤ ተገርፌያለሁ፤ ደቅቄያለሁ፤ ተሰቅያለሁ፤ እንዲሁም መርገምን ተሸክሜያለሁ። ለአንተ የይቅርታ እና የንጽሕና ተግባራትን እንዲሁም ይገባኛል የምትልበትን ጸጋ አዘጋጅቼልሃለሁ። ና! ለአንተ መከራ የተቀበልኩትን ያህል በአንተ ደስ ይለኝ ዘንድ ና! የመዳንን ዘውድ እደፋልህ ዘንድ፣ ፍቅሬን እና መንፈስ ቅዱስን በአንተ ላይ አፈስስ ዘንድ፣ እንዲህ አድርጌ ወደ አባቴ አቀርብህ ዘንድ ና! አንተ ከበጎቼ ሁሉ እጅግ ውዱ ነህ፤ እኔ ደሜን እስከመክፈል ደርሼ ከፍ ያለ ዋጋ ሰጥቼሃለሁና።"
***
የክርስቶስ ስሞች፣ ገጽ 135-36።
የዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ የኤፌሶን ወንዝ መጽሐፍ
ነገ ቅዳሜ በግዮን መጻሕፍት ታገኙታላችሁ።
ሙሉ ገቢው ለግሸን ደብረ ከርቤ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስትያን ሕንፃ ቤተ መቅደስ እድሳት የሚውል።
በግዮን መጻሕፍት መደብር ነባር እና አዳዲስ መጽሐፍቶችን ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኛሉ።
እጻጻፋም እንደ ዮሐንሰ ስብከት ፊት ለፊት ነው፡፡ አለማወቅን ሲገስጽ እንደ ዮሐንስ ሰብከት ምሳሩን እያሳየ ነው ድንቁርና ጨለማን ሊያርቅም ዮሐንሰን ችቦ አድርጎ እያሰራ ነው። ከኃጢኦት አረገቋ ሲያጥብም በዮሐንስ የጥምቀትና የትምህርት ባሕር እየዘፈቀ ነው፡፡ ዮሐንሰን መውደድ ማን መውደድ መሆኑ ግልጽ ነው።ከእርሱ መጀከሮም በማን ለመጨረስ መሆኑ የታወቀ ነው ።በእርሱ መደነቅም በእርሱ ጌታ በክርስቶስ ቀርቶ በዮሐንስም ለመደመም እንኳ አቅመ ቢሰ መሆናችንን ለማሳየት መሆኑም የተገለጠ ነው ጌታ ስለዮሐንሰ እርሱ እውነት መስክሮአል እንዳለ ይህ መጽሐፍም፡- ቤተ ክርስቲያን ስለዮሓንስ የያዘችውን እውነት ግልጽ አድርጎ ያወጣ አዘጋጁን አባታችንም የእውነት መሰክር የሚያሰኝ ነው። እንዲያውም ቅዱስ ያሬድ ስለቅዱስ ዮሐንስ ውነቱ አነነ ኣብል በእንተ የተስሰ እና ከርስ እው እግዚኡ እእመረ፣ በዕለት ጥሉ አንደረት ነፍሱ ዲበ ምድር እንዳለው ስለዚህ መጽሐፍ ጠቀሜታ እኔም ብዙ ላለመናገር ብመርጥ መልካም ሳይሆን አይቀርም። በርግጥ መጽሐፉ አባታችንም የቅዱስ ያሬድ ልጅ መሆናቸውን የሚመሰከር ንዜኑ ንዜኑ የሚል መጽሐፍ መሆኑን ላለመመስከር ልላቀቅ አልችልም። ጌታን የሚያገኝ ዮሐንስ ቀድሞ ያስፈልገዋልና : አባታችንም ቀድመው ዮሐንሰ ይዘው ሰለመጡ የጌታን ነገር ሊያስከትሉ ነው ብዬ እንድገምት ማድረጉንም ልደብቅ እልችልም፡፡ እንግዲያውስ አንደ እነርሱ እመጣጥ ከስድስት ወር ልዩነት ሳያሰበልጡ ቶሎ ይዘውልን ይምጡ እያልኩ መማጸኔን ማሳወቅ ከፉ እልመሰለኝም።
ዲያቆን ብርሃኑ አድማሰ
ምስጢር ከሚፈስበት፣ከሚቀዳበት ከጉባኤ ቤት የተሰጠ የምስጢር መአድን አቅርብንላችኋል። "ከመዝ ነአምን" በመምህር የኔታ ገብረ መድኀን እንየው የተበረከተ። የጉባኤ ቤት ምስጢር የፈሰሰበት መጽሐፍ ነው።
መጽሐፍን እኛ ዘንድ በግዮን መጽሐፍት መደብር ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኙታል።ገቢው ሙሉ ለሙሉ ለምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት የሚውል ነው። አንድም ከበረከቱ እንሳተፍ አንድም ምስጢሩን ከየኔታ እንቅዳ።
አድራሻ:-መ/ገ/ጽ/ቅ/ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን
ለበለጠ መረጃ 0913083816 /0931144330
የዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ የኤፌሶን ወንዝ መጽሐፍ ቅዳሜ ለሁሉም መጽሐፍ መደብሮች ትሰራጫለች።
የሽፋን ዋጋ 400ብር
ሙሉ ገቢው ለግሸን ደብረ ከርቤ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስትያን ሕንፃ ቤተ መቅደስ እድሳት የሚውል።
ቅዳሜ በግዮን መጻሕፍት ያገኙታል።
+1
ይህ የዲያቆን ያረጋል አበጋዝ ድንቅ መጽሐፍት ፤ከሳይንስ፤ ጋር የተገናኙ፤ ፍልስፍናዊ ፤ጉዳዮች ፤ከክርስትናዊ ፤ በሰፊው የሚዳስስ ፤መጽሐፍ ነው።
እያለቀ ስለሆነ እንዳያመልጥዎት የተወሰነ ቅጂዎች አሉን ይጎብኙን ግዮን ፤መጻሕፍት፤ መደብር ፤ዘወትር በልዩ ቅናሽ እንጠብቃችኋለን።
አሐቲ ድንግል በመደብራችን እየተሸጠ ይገኛል ዘወትር ልዩ ቅናሹ እንደተጠበቀ ነው።
"እግዚአብሔር የሰው ልጅን ያዳነበት መንገድ በዕለተ ዐርብ በመሰቀሉና መከራን በመቀበሉ ብቻ የሚመስለውና ከነገረ መስቀሉ ውጪ ያለው ጉዳይ የሚጠቅም የማይመስለው ሰው ካለ ነገረ ድኅነትን ጨርሶ አልተረዳም፡፡
እንደዚያ ቢሆን ኖሮ እግዚአብሔር በድንግል ማርያም ተፀንሶ ተወልዶ ሠላሳ ዓመታትን መቆየት ሳያስፈልገው ልክ የመጀመሪያውን አዳም እንደፈጠረው የሠላሳ ዓመት የሆነ ሥጋንና ነፍስን ለራሱ ፈጥሮ መለኮቱን አዋሕዶ ሰው መሆን ይችል ነበር፡፡ ይህንን ቢያደርግም ሦስት ዓመታት በምድር ላይ አስተምሮ በጊዜው ተሰቅሎ የማዳን ሥራውን መፈጸም ይችል ነበር፡፡
እርሱ ግን ማዳኑን የጀመረው በማሕፀን ከመፀነስ ነበር፡፡
አረጋዊው ስምዖን ‘ዓይኖቼ ማዳንህን አይተዋል’ እንዳለ ማዳኑንም የጀመረው ሕፃን ሆኖ በመታቀፉ ነው፡፡ ሉቃ. ፪፥፴
አልፋና ኦሜጋ እኔ ነኝ ላለው ክርስቶስ በምድር ላይ በቆየበት መዋዕለ ሥጋዌው አልፋው ድንግል ማርያም ስትሆን ኦሜጋው መስቀል ነበር፡፡ የተሰቀለ ቀን ብቻ አይተህ ልታውቀው አትችልም፡፡ ሁለተኛ አዳምነቱ ዘልቆ የሚሰማህ ወደ ልደቱ ስትመለስ ነው፡፡ የሰው ልጅ ቁስልም የሻረው ጌታ ሊወለድ ካለበት ቅፅበት ጀምሮ ነው"
የብርሃን እናት ገጽ 97
በተደጋጋሚ የጠየቃችሁን ደንበኞቻችን ከገቢያ ላይ ጠፍቶ የነበረው የብርሃን እናትን መጽሐፍ የተወሰነ ቅጅዎች አግኝተናላችኋል።
በግዮን መጻሕፍት መደብር ነባርና አዳዲስ መጽሐፍቶችን ታገኛላችሁ።
አሐቲ ድንግልን ነገ እሁድ ሱቃችን ክፍት ስለሆነ ከ3 ሰዓት ጀምሮ እስከ 8 ሰዓት በግዮን መጻሕፍት ታገኙታላችሁ።
ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ፥ አፈ ወርቅ የተባለበት ድንቅ መጽሐፉ ለ4ኛ ጊዜ ታትሞ በገበያ ላይ ውሏል።
ደርዛቸውን የጠበቁ ነበርና አዳዲስ መጽሐፍቶችን በግዮን መጻሕፍት መደብር ዘወትር በልዩ ቅናሽ ታገኛላችሁ።
አሐቲ ድንግል ዛሬ ቅዳሜ ከስዓት በግዮን መጻሕፍት ታገኙታላችሁ።
ለረጅም ጊዜ ከገበያ ጠፍቶ የነበረውና ወደ ኦሎምፒያስ የተላከው የቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ መጽሐፍ በገበያ ላይ ዋለ።
በግዮን መጻሕፍት መደብር ታገኙታላችሁ
ለበለጠ መረጃ 0913083816
በጉጉት ሲጠበቁ የነበሩት የየኔታ ርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ መጻሕፍቶች በገቢያ ላይ
፩. ጸያሔ ፍኖት
፪. መጽሐፈ ወግሪስ
፫. እና መጽሐፈ ምዕዳን
ከገቢያ ላይ ጠፍተው የነበሩ በድጋሚ ታትመው ወተዋል
በግዮን መጻሕፍት መደብር ያገኙታል። _
አድራሻችን፦ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ በጀርባ ማህበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት።
ለበለጠ መረጃ 0913083816
#ስለ ስደቷ የሚያወሳ አዲስ መጻሕፍት
በገቢያ ላይ
በቅዱስ ቴዎፍሎስ ዘእስክንድርያ ተርጓሚ መምህር ቃለ ጽድቅ ሕግነህ በባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ጽርሐ ጽዮን ቅድስት ማርያም ገዳም የሐዲሳት ትርጓሚ መጻሕፍት መምህር የተዘጋጀ ሲሆን በ105 ገጾች በ195 ብር የሽፋን ዋጋ የቀረበ ነው።
በግዮን መጻሕፍት መደብር ታገኙታላችሁ።
ዮሐንስ አፈ ወርቅ ተወዳጅ ሥራ የኾነው የማቴዎስ ወንጌል ቅጽ ፪ መጽሐፍ በገቢያ ላይ ወቷል በግዮን መጻሕፍት መደብር በልዩ ቅናሽ ታገኙታላችሁ።
ትላንት ቦሌ መድኃኔዓለም የነበረው የአሐቲ ድንግል የመጽሐፍ ምረቃ መርሐግብር እጅግ አስደሳች ቢሆንም በሰው ብዛት እና በነበረው መጨናነቅ ምክንያት መጽሐፉን ማግኘት ያልቻላችሁ ህትመት ላይ ስለሆነ ከሰሞኑ በድጋሚ በገቢያ ላይ ይውላል።
አሐቲ ድንግል - በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
የሚያረካ የመጻሕፍት ፊት አውራሪ ፤ የነገረ ማርያም ጥም ቆራጭ ፤ የትርጓሜ ድግስ ፤ የምሥጢራት ዝናም ፣ ያለ ስስት በፍቅር የተጻፈ ቅኔ መወድስ ፤ እንደ ሊቅ በምሥጢር እየተራቀቁ እንደ መናኝ በፍቅር እሳት እየተማወቁ የጻፉት በጸዳለ ምሥጢር የተጽደለደለ መጽሐፍ ተከስቶአል:: እመቤታችንን የሚወድ ሁሉ በፍቅርዋ ባሕር ለመዋኘት የሚችልበት እጅግ እጅግ እጅግ ውብ መጽሐፍ ፤ በጸሎት መንፈስ ለብቻ ተኾኖ ካልሆነ ሊነበብ የማይችል በዕንባ የሚያሰጥም መጽሐፍ ፤ ሌላ ነገር አንብበህ በዚያው ዓይንህ ልታነበው የማይገባ ዓይኖች ጾመው ሌላ ከማየት አክፍለው ሊያነቡት የሚገባ የወላዲተ አምላክ የቀሚስዋን ዘርፍ በፍቅር የሚያስነካ መጽሐፍ እነሆ ከደጃችን ነው::
እንደ ቃና ሊቀ ምርፋቅ መልካም የወይን ጠጅ "አሐቲ ድንግል" እያለች በመናኛ መጻሕፍት ለምን ሰከርን የሚያሰኝ የመጽሐፍ ወይን ታዩ ዘንድ ኑ! !
ዛሬ ቅዳሜ ከሰዓት በቦሌ መድኃኔዓለም ካቴድራል
ሥዕል :- ሠዓሊ ዲ/ን ዮርዳኖስ ዘሪሁን (ገብረ ኪዳን) እንደሣለው
+1
# አቡሻክርና ፍካሬ ፊደል #
እንደ ዳይኖሰር ሊጠፉ
የተቃረቡ የቤ/ክርስቲያኗ ሀብቶች ናቸው።
መምህራችን መምህር ዘለዐለም ሐዲስ ፤
የ፬ጉባኤያት ምክትል መምህርና የደብሩ ስብከተ ወንጌል ኀላፊ ዳይኖሰራችን ከጥፋት ስለታደጉት ከልብ እናመሰግነዎታለን ።.........................።
በተመሳሳይ
ፋኖ አቋቋም ፤ ቤተ ማርያም አቋቋም ፤ ሰደድ ኲላ ቅዳሴ፤ አጫብር አቋቋም ፤ ተጉለቴ ፤ ቆሜ ድጓ ፤ ተክሌ አቋቋቋምን የመሳሰሉ ፤ ከቅኔ ወገን ደግሞ፤ ያ የቀደሙሞው ብሉይና ሐዲስን የሚያገናኘው ፣ የነ አድማሱ ጀምበሬ የድማዎቹ፤ የነ የኔታ ወልደ ሰንበት የወሎዎቹ፤ የነ የኔታ ክፍለ ዮሐንስ የጎንደሮቹ፤ የነ የኔታ ናሁ ሠናይ የመቀሌዎቹ፤ የነ የኔታ አካለ ወልድ የቦሩዎቹ፤ የነ እሜቴ ገላነሽ የጎጃሞቹ ቅኔ እየጠፋ በላ ጠጣ ፤ ሄደ መጣ ፤ አየሩ በረረ ፣ መኪናው ተሰበረ ወዘተ የሚል ቅኔ የምንቀኝ ኾነናል ። ይህም እየቀነሰ መሄዱ ነው።
ታድያ ይህ አቡሻክርም እንደ ዳይኖሰር ሊጠፋ ትንሽ ሊቀረው ሲል መኖሪያውንና አኗኗሩን በሚገባ ጠቁመው አሳይተዋልና በእጅጉ እናመሰግነዎታለን። ከአኹን በኋላ ጫካውን ካሳዩን አድኖ መያዝማ የኛ ድርሻ ነው። በግዮን መጻሕፍት መደብር ታገኙታላችሁ።
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
