uz
Feedback
5killo Jem'a official Channel

5killo Jem'a official Channel

Kanalga Telegram’da o‘tish

This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0

Ko'proq ko'rsatish
1 159
Obunachilar
-124 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kun
-130 kun
Postlar arxiv
✨ አብዛኛው ሰው በምን ያህል መከራ እያለፈ እንዳለ ስታውቅ በአስተውሎት በአንኩሮ የምታሰተውለው የታላቁ ነቢይ (ﷺ) ሐዲስ ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿مَنْ أصبَحَ منكمْ آمنًا في سِرْبِهِ، معافًى فِي جَسَدِهِ، عندَهُ، قوتُ يومِهِ، فكأنَّما حِيزَتْ لَهُ الدنيا بحذافِيرِها﴾ “በቤተሰቡ መሀል በሰላም ያደረ፣ ሰውነቱ በሙሉ ጤነኛ ሆኖ ያነጋ፣ የዕለት ጉርሱን ያገኘ፣ ዱንያን በሙሉ እሱ ዘንድ ሰብሰቧታል።” 📚 ሶሂህ አልጃሚ: 6042 📌 በርግጥም የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦ ﴿وَقَلِيلٞ مِّنۡ عِبَادِيَ ٱلشَّكُورُ﴾ “ከባሮቼ በጣም አመስጋኞቹም ጥቂቶች ናቸው፡፡” ቁርአን (ሰበእ: 34‐13)

📢ልዩ የሙሃደራ ፕሮግራም ለእህቶች🌸 አሰላሙ አለኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱህ ውድ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች እነሆ እንስቶችን የሚመለከቱ ጉዳዮችን ልናወጋ.... ዲናችንን ልንማ
📢ልዩ የሙሃደራ  ፕሮግራም ለእህቶች🌸 አሰላሙ አለኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱህ ውድ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች እነሆ እንስቶችን የሚመለከቱ ጉዳዮችን ልናወጋ.... ዲናችንን ልንማማር...ብሎም ልምድን እና የህይወት ስንቅን ልንቋጥር  በተከበረው የአላህ ቤት ቀጠሮ ይዘናል!!! ምን አለ...🤔 በአካዳሚክ ህይወታቸው፣ በዲናዊ እውቀታቸው........ ብቻ ምን አለፋችሁ በሁሉም የህይወት ዘርፍ ላይ አንቱ የተባሉ...... እንደ እናት፣ እንደ እህት፣ ሲያስፈልግም እንደ ሚስትና ተማሪ ሆነው ሊመክሩን፣ ልምደቸውን ሊያካፍሉን የፈቀዱ ከአንድ በላይ ኡስታዛዎችን ጋብዘን በውቡ  አቅሳ መስጂድ እንጠብቃችኋለን!! መች ይሆን? 📅ቀን፡- ቅዳሜ ፤ሚያዝያ 10 ⏰ሰአት፡-ከጠዋቱ 3፡00 📌ቦታ፡- አል አቅሷ መስጂድ Šqireat6k @fivekjemaa

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማህበር በመገኘት በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ስላለው የመብት ጥሰት አቤቱታ አሰሙ ! ! ! ሕግ ሲጣስ በቀዳሚነት ጠበቃ ሊሆን
+1
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች  ማህበር በመገኘት በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ስላለው የመብት ጥሰት አቤቱታ አሰሙ ! ! !   ሕግ ሲጣስ በቀዳሚነት ጠበቃ ሊሆን የሚገባው ሕግን የሚያውቀውና በሕግ ስም የተቋቋመው ተቋም ነው። ስለመብት ጥሰት ሁሉም የሚገደው ቢሆንም የሴቶች መብት ሲጣስ ደግሞ ስለሴቶች የተቋቋሙ ተቋማት በቀዳሚነት ሊረባረቡ ይገባል።   የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶችም በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ስላለው የመብት ጥሰት አቤት ለማለት ከኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማህበር ቢሮ በመገኘት አብራርተዋል። የሄዱበትን ርቀት በማስረዳትም ለሚመጣው ፍትሕ አስተዋፅዖ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! Šaaumsu @fivekjemaa

🌙 3-DAY SHORT COURSE A short and beneficial gathering to reconnect with the foundations of your din through a classical text
🌙 3-DAY SHORT COURSE A short and beneficial gathering to reconnect with the foundations of your din through a classical text. 📚 Kitab: Lamiyyah ✍️ Author: Ibn Taymiyyah 👤 Instructor: Ustadh Zenjebil 📍 Place: 4 Kilo Mosque 💻 Also Online: via 5 Kilo Qira’ah Channel 🗓 Date: Wednesday (April 15) – Friday (April 17) ⏰ Time: 11:00 – 12:30 LT ✨ What you will gain: • Better clarity in understanding your belief • A chance to learn in a simple and focused environment • Opportunity to ask questions and engage • Beneficial reminders that strengthen your iman 🎓 Open to all students ⚠️ Don’t miss these three days of beneficial knowledge 📝 Register using the Google Form below https://forms.gle/58hpV6yW6n2sdzZV6 🤝 Take this opportunity to sit with knowledge and grow in your din.

ሰበር ዜና! የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የሹራ ካውንስል ባካሄደው ወሳኝ ምክክር፣ የስራ ዘመናቸውን ያጠናቀቁ አመራሮችን በመተካት አዳዲስ አመራሮችን መርጧል። በህብረቱ መተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ 40 መሰረት በተካሄደው በዚህ ምርጫ፤ የአምስት ኪሎ ካምፓስ የዳዕዋና ቂርዓት ሴክተር አሚር የነበረው ወንድም አብዱልሀኪም ሀሰን ህብረቱን ለቀጣይ አንድ ዓመት ከአራት ወር በፕሬዝዳንትነት እንዲመራ በአብላጫ ድምፅ ተመርጧል። እንዲሁም በአምስት ኪሎ ካምፓስ የሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ የ3ኛ ዓመት ተማሪ እና በጀመዓው ማህበራዊ ዘርፍ አሚር ሆኖ በማገልገል ላይ የሚገኘው ወንድም መስዑድ ውበቱ የህብረቱ ምክትል ፕሬዝዳንት በመሆን ሲመረጥ፣ የልደታ ካምፓስ ጀመዓ ፀሀፊ እና የኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂና ማኔጅመንት (CoTM) የ4ኛ ዓመት ተማሪ የሆነው ወንድም ኹበይብ ሙሀመድ ደግሞ የህብረቱ ጸሐፊ በመሆን ተመርጧል። የካውንስሉ አባላት ለተመራጮቹ መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንላቸው ምኞታቸውን የገለጹ ሲሆን፣ የሽግግር ሂደቱን ውጤታማ ለማድረግ ሲባል የቆዩት አመራሮች ከአዲሶቹ ተመራጮች ጋር ለቀጣይ ሁለት ወራት በጋራ በመስራት ኃላፊነታቸውን ሙሉ በሙሉ የሚያስረክቡ ይሆናል። ©aaumsu @fivekjemaa

ቻለንጅ 10 _ በአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ማህበር የፌስቡክ ፔጅ ! የፌስቡክ ፔጁ ከ77 ሺህ በላይ ተከታዮች ያሉት ሲሆን በሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ የመብት ጥሰቶች ሲኖሩ በቀዳሚነት ድምፃቸውን በማ
ቻለንጅ 10 _ በአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ማህበር የፌስቡክ ፔጅ !   የፌስቡክ ፔጁ ከ77 ሺህ በላይ ተከታዮች ያሉት ሲሆን በሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ የመብት ጥሰቶች ሲኖሩ በቀዳሚነት ድምፃቸውን በማሰማት ይታወቃሉ። የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች እየደረሰባቸው ያለውን በመግለፅ ፍትሕ ይሰፍን ዘንድ ጠይቀዋል። ሀላፊነታቸውን ስለተወጡ እናመሠግናለን። በዘመቻችን፦ አስተያየታችንን በማስፈር ለሌሎች ማሠራጨት ትንሹ ግዴታችን ነው። ሊንኩ https://www.facebook.com/100063462439332/posts/1574436144681785/?app=fbl ነው። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! Šaaumsu @fivekjemaa

ቻለንጅ 9 _ ለAAU _ ከኡመር ልጆች ! ዩኒቨርሲቲያችን ከብዙ ዘመን ቡሃላ የሐሳብ መስጫ ሳጥኑን ክፍት አድርጓል። እናንተም ወደዚያው በመግባት ስለፍትሕ ጠይቁ። ጨቋኙ መመሪያ ይሻሻል ዘንድ ጠይቁ።
ቻለንጅ 9 _ ለAAU _ ከኡመር ልጆች ! ዩኒቨርሲቲያችን ከብዙ ዘመን ቡሃላ የሐሳብ መስጫ ሳጥኑን ክፍት አድርጓል። እናንተም ወደዚያው በመግባት ስለፍትሕ ጠይቁ። ጨቋኙ መመሪያ ይሻሻል ዘንድ ጠይቁ። ጥያቄ አለን በሏቸው። ሊንኩ https://www.facebook.com/100064311447035/posts/1386294146857620/?app=fbl ነው። ይህ ትንሹ ሀላፊነታችን ነው። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! ©aaumsu @fivekjemaa

ዘመቻ 8 _ በZhara Mustefa የቲክቶክ ገፅ ! በቲክቶክ ከ158 ሺህ በላይ ተከታይ አላት። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው የመብት ጥሰት ድምጿን አሰምታለች። ተማሪዎች ፍትሕን ለማግኘት የሄዱበትን ርቀት በመግለፅም ፍትሕ ይመጣ ዘንድ ጥሪ አቅርባለች። በዘመቻችን፦ ቪድዮውን ማየት፤ አስተያየት መስጠት እና ለሌሎች ማሠራጨት ትንሹ ሀላፊነታችን ነው። ሊንኩ https://vm.tiktok.com/ZS9LNyx9Eu6v6-854Aa ነው። ጥያቄ አለን _ ፍትሕ እስኪመጣ ! ! ! ©aaumsu @fivekjemaa

🗣🗣اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ‎👋 ✅ኢንሻአላህ ዛሬ (ሰኞ ) የሰሂህ አል-ቡኻሪ ሙኽተሰር የሆነውን التجريد الصريح لأحاديث الجامع الصحيح ደርስ ይኖረናል ።  5ኪሎ እና 6ኪሎ የምንገኝ ሙስሊም ተማሪዎች በጊዜ እንገኝ ሌሎችንም በማስከተል  ቡዙ እናተርፍለን። "مَنْ سَلَكَ طَرِيقًا يَلْتَمِسُ فِيهِ عِلْمًا، سَهَّلَ اللَّهُ لَهُ بِهِ طَرِيقًا إِلَى الْجَنَّةِ" «በሱ ውስጥ እውቀትን ለመፈለግ ብሎ መንገድ የጀመረ  áˆ°á‹ አላህ የጀነትን መንገድ ያገራለታል» ነብዩ  ሰዓት: ከመግሪብ - ኢሻ ቦታ፡ áŠ á‰…áˆł መስጅድ 📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ። https://t.me/durus_at_aqsa ⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻 https://t.me/durus_at_aqsa/4306/4934 @fivekjemaa

💥 ደርስ ማስታወሻ ::::::::::::::::::::::: 🗣🗣አሰላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ 👋👋👋 ✅ ኢንሻአላህ  ዛሬ ሙዳራቱ ናስ (በመልካም መኗኗር)የተሰኘው የአደብ ደርስ ይኖረናል :: 📌የቂርዐት ቦታ ፦ 4 ኪሎ የተማሪዎች መስጂድ ⏰የቂርዐት ሰዐት፦ ከመጝሪብ እስከ ዒሻ ⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻 https://t.me/Qirat4k/672 📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ። https://t.me/Qirat4k

በሰዎች መሃል እየኖረ የሰዎችን አስቸጋሪ የሆኑ ባህሪያትን ተቋቅሞ የሚኖር እሱንም ለማስተካከል የሚጥር ሙስሊም የተሻለና ምንዳውም የበዛ ነው ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿المسلِمُ إذا كانَ مخالطًا النّاسَ ويصبِرُ على أذاهم خيرٌ منَ المسلمِ الَّذي لا يخالطُ النّاسَ ولا يصبرُ على أذاهم﴾ “ሰዎችን ተቀላቅሎ የሚያደርሱበትን ችግር ተቋቅሞ (ታግሶ) የሚኖርና ችግራቸውን ለማስተካከል የሚሞክር ሙስሊም፤ ያ! ሰዎችን ሳይቀላቀል መከራቸው ሳያገኝው ከሚኖር ሙስሊም የተሻለ (በላጭ) ነው።” ቲርሚዚ ዘግበውታል አልባኒ ሶሂህ ብለውታል፡ 2507

ዘመቻ 7 _ በEsmail Ottoman የቲክቶክ ገፅ ! በቲክቶክ ከ176 ሺህ በላይ ተከታዮች አሉት። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን የመብት ጥሰት በመግለፅ፤ ተማሪዎቹ መብታቸውን ለመጠየቅ የሄዱበትን ርቀት በማስቀመጥ ፍትሕ ይሰፍን ዘንድ ጠይቋል። ሀላፊነቱን በአግባቡ ስለተወጣ እናመሠግናለን። በአላህ ፍቅድ በትብብር እና በቅንጅት በምናደርገው እንቅስቃሴ መፍትሔው ይቀርባል። በዘመቻችን፦ ቪድየውን መመልከት፤ በአስተያየት መስጫው ላይ ሀሳባችንን ማስፈር እንዲሁም ለሁሉም ሰው ማሰራጨት ከትንሹ ሀላፊነታችን ነው። ሊንኩ https://vt.tiktok.com/ZSHxFP1Uo/ ነው። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! ©aaumsu @fivekjemaa

ዘመቻ 6 _ በኡስታዝ አለላህ መሕዲ የቲክቶክ ገፅ ! ኡስታዞች የዲን መምህር እንደመሆናቸው በሙስሊሞች ላይ የሚደርስን ግፍ ከማንም ቀድመው በመልዕክቶቻቸው ውስጥ የማስተላለፍ ግዴታ አለባቸው። ይህንን ሀላፊነት በመወጣትም በቲክቶክ ከ375 ሺህ በላይ ተከታይ ያላቸው ኡስታዝ አለላህ መሕዲ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው የመብት ጥሰት ድምፅ በመሆን መልዕክት አስተላልፈዋል። ሀላፊነታቸውን ስለተወጡ እናመሰግናለን። አላህ ለመልካም ለውጥ ሰበብ ያድርጋቸውና። በዘመቻችን፦ ቪድዮውን እንመልከት። አስተያየታችንን እናስቀምጥ። መልዕክቱን ለሁሉም እናሰራጭ። ይህ ትንሹ ሀላፊነታችን ነው። ሊንኩ https://vt.tiktok.com/ZSHxYEBMq/ https://vt.tiktok.com/ZSHxFca1X/ ነው። ወደ ተግባር! ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! @aaumsu

ሶፊያን ቢን አብደላህ አሰቅፊ (ረ.ዐ) ተይዞ፡ እንዲህ ይላል፦ ﴿يا رسولَ اللَّهِ حدِّثْني بأمرٍ أعتصِمُ بِهِ قالَ قُلْ ربِّيَ اللَّهُ، ثمَّ استقِم قلتُ: يا رسولَ اللَّهِ ، ما أخوَفُ ما تخافُ عليَّ؟ فأخذَ بلسانِ نفسِهِ ثمَّ قالَ: هذا﴾ “አንቱ የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ‘አጥብቄ የሚይዘውን (ከተግባርም ከንግግርም የሆነ በዱኒያም በአኼራም የሚጠቅመኝ) የሆነን ነገር ይንገሩኝ’ ጌታዬ አላህ ነው በል! በዛም ላይ ፅና: አልኳቸው፦ አንቱ የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! በኔ ላይ ከሚፈሩት ነገር የቱ ነው ይበልጥ የሚፈሩልኝ? በነፍስህ ላይ ምላስህን (አንደበትህን) ጠብቅ (ተቆጣጠር)። በድጋሚ ወደ ምላሳቸው በመጠቆም ይህንን አሉኝ።” ቲርሚዚ ሶሂህ ብለውታል፡ 2410

ፕሮፋይል ቻለንጅ ! ! ! መብታችንን የሚጥስ መመሪያ አውጥተው ነፃነታችንን በመግፈፍ እምነታችንን በማስተው የእነርሱ አስተሳሰብ እስረኛ ሊያደርጉ የሞከሩ አካላትን "ጥያቄ አለን!" በማለት እምቢ ለባ
ፕሮፋይል ቻለንጅ ! ! ! መብታችንን የሚጥስ መመሪያ አውጥተው ነፃነታችንን በመግፈፍ እምነታችንን በማስተው የእነርሱ አስተሳሰብ እስረኛ ሊያደርጉ የሞከሩ አካላትን "ጥያቄ አለን!" በማለት እምቢ ለባርነት ማለት ከጀመርን አመት ከመንፈቅ አልፏል። አሁን "መመሪያውን ያወጣነው እነርሱን አስበን አይደለም። ለሁሉም ተማሪ ነው። እነርሱ ጥቂት ስለሆኑ ለጥቂቶች ብለን አንቀይርም።" - የሚልን ተስፋ የቆረጠ እና የሐሳባቸው ውጥን እየተበጣጠሰ መሆኑን የሚያሳይ ምላሽ እየሰጡ ነው። ስንጀምር እንዳልነው ድል ከእውነት እና ከፍትሕ ጎን ነው። ላንጨርስ አልጀመርንም። እምነታችን ተከብሮ፤ ነፃነታችን ፀንቶ መብቶቻችን እስኪረጋገጡ ድረስ ትግላችን ይቀጥላል። ጥቂቶች ናችሁ ለሚሉን "የአንድ ሙስሊም ተማሪ ዋጋ ስንት ነው?" - በሏቸው። ዋጋችንን ጠንቅቀን እናውቃለንና "ጥያቄ አለን!" - በሏቸውም። አዲሱን ምስል ፕሮፋይላችሁ አድርጉት! ሌሎች ያደርጉት ዘንድም አሰራጩ!! በአላህ ፈቃድ የፍትሕ ቀን ቅርብ ነው!!! ጥያቄ አለን! Gaaffii Qabna!! ©aaumsu @fivekjemaa

🌙 ONLINE QIRA'AT DARS Seeking Clarity in Your ‘Aqeedah Are you looking to strengthen your understanding of Islamic belief in a clear, authentic, and structured way? Here is a beautiful opportunity to learn a foundational text with guidance and clarity. 📚 Study: Al-Aqidah al-Tahawiyyah (A Foundational Text in Islamic Belief) 👤 Instructor: Ustaz Zanjabil 🗓 Start Date: Saturday, April 11 📅 Schedule: Every Saturday & Sunday ⏰ Time: After Fajr (12:00 AM) ✨ What you will gain: • Clear and structured explanation of core beliefs • Interactive Q&A sessions • Strengthening your understanding with authentic texts • Certificate awarded upon consistent qira’at attendance and passing the final examination. 💫 Special gifts for top 3 students✨ 🎓 Open to all students from any department and campus 📝 Register now using the Google Form below👇👇👇 https://forms.gle/mR3hBMJ42hoP4V996 📢 Join the 5K Qira’at channel where the qira’at sessions are delivered 🤝 Take this step to build a strong foundation in your din and grow in beneficial knowledge. @fivekjemaa

There’s a tafsir ders tonight at Aqsa Mosque with Sheikh Seid… it’s honestly something special. Not going to say much, but sometimes one ayah hits differently like you suddenly understand it and feel like it’s speaking directly to you. The Prophet ﷺ said: “The best of you are those who learn the Qur’an and teach it.” Maybe this is one of those steps… or maybe it’s just another missed chance. Up to you.

🌙 The Importance of Education in Islam 📚 صَبَاحُ الْخَيْرِ 🌅 Seeking knowledge is not just encouraged in Islam—it is an obligation upon every Muslim. The very first revelation to our beloved Prophet ﷺ began with the command: “Read!” This shows us how central education is in our deen. 📖 Allah سبحانه وتعالى raises the status of those who believe and those who are given knowledge. Knowledge brings us closer to Allah, strengthens our iman, and helps us distinguish between right and wrong. 🧠 Education in Islam is not limited to religious knowledge alone. It includes beneficial worldly knowledge that serves humanity, uplifts communities, and fulfills our responsibility as khalifah (stewards) on earth. ✨ The Prophet ﷺ said: "Seeking knowledge is an obligation upon every Muslim." This means: 1. We strive for excellence in our studies 2. We seek knowledge with sincere intention (niyyah) 3. We use what we learn to benefit others Whether you are studying engineering, medicine, or Islamic sciences—align your intention for the sake of Allah, and your education becomes an act of worship. 🤲 Let us renew our intentions, stay consistent, and support one another in our academic journeys. Your books, your lectures, your late-night studies—they are all خطوات toward Jannah when done for the sake of Allah. May Allah grant us beneficial knowledge and make us among those who act upon it. Ameen. ©Academic Sector

ወንድም ሙራድ ታደሰ --- ሴኩላሪዝምን እንደ ሽፋን ተጠቅሞ ሒጃብን በመመሪያ በከለከለ ማግስት ሴኩላሪዝምን የሚጥስ የበዓል መልዕክት ስላስተላለፈው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከላይ ያለውን ፅሁፍ አስፍሯ
+4
ወንድም ሙራድ ታደሰ --- ሴኩላሪዝምን እንደ ሽፋን ተጠቅሞ ሒጃብን በመመሪያ በከለከለ ማግስት ሴኩላሪዝምን የሚጥስ የበዓል መልዕክት ስላስተላለፈው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከላይ ያለውን ፅሁፍ አስፍሯል። የAAU ሙስሊም ተማሪዎች እየደረሰባቸው ስላለው የመብት ጥሰት ብዙዎች ዝም ባሉበት ከተማሪዎቹ እኩል ከመጀመሪያው ጀምሮ ድምፁን ሲያስተጋባም ነበር። ሀላፊነቱን በአግባቡ በመወጣት በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን በደል ስላስተጋባ፤ ፍትሕ ይመጣ ዘንድ ስለሞገተ እናመሠግናለን። አላህ ከመጥፎ ነገሮች ይጠብቀው! ጥረቶቹንም ለመልካም ለውጥ ሰበብ ያድርግ!! ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! ©aaumsu @fivekjemaa