uz
Feedback
5killo Jem'a official Channel

5killo Jem'a official Channel

Kanalga Telegram’da o‘tish

This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0

Ko'proq ko'rsatish
1 160
Obunachilar
-124 soatlar
+27 kun
-130 kun
Postlar arxiv
🔥ከሙተነቂቦች መንደር ~ 4🔥 بسم الله •• ከሙተነቂቦች መንደር እታደም ዘንድ በሩን ለከፈተልኝ  ጌታዬ ምስጋና ይገባው።   የዛሬ አንድ አመት በሰላም ለ3 አመት  ስትማር የነበረችውን ጓደኛዬን በየግቢ በሩ፣ በየክላሱ ሰላም መንሳት ሲጀምሩ ትዝ ይለኛል በጣም ነበር ምናደደው። የሆነ ኢስላም ሲነካ እኮ extremely on ሚሆን ነገር አለን አይደል ?? በጣም on እሆን ነበር። አብሬያት ከሆንኩ ለሷ ራሱ እድል ሳልሰጥ እሟገትላት ነበር ነገር ግን በሂወቴ ግቢ ውስጥ ሆኜ ሳልመረቅ ኒቃብ እንደማለብስ ለራሴ አስረግጬ ነግሬዋለው። መልበሱ ትዝ አይለኝም እንደው ያንን ብርቅዬ አለማቸውን✨ እንድቀላቀል የሚፈልጉ እህቶች ሲጠይቁኝ አሏህ ያለ ቀን ብዬ እመልስና መዝገቡ ይዘጋል!! ሰው እንደራሱ ሳይሆን እንደ አሏህ እቅድ እንደሚኖር ማረጋገጫ ልስጣቹ?? ያ ሳልመረቅ በፊት እንደማለብሰው ያሰብኩትን ኒቃብ ፍቅሩን አሏህ ውስጤ ላይ ቁጭ አረገው፣ ምልክቶችን ይሰጠኝ ይመስል ሰዉ ሁሉ ስለ ኒቃብ እንደሚያወራ ይሰማኝ ጀመር  ከጠበኩት ሳይሆን ካልጠበኩትም ሰው ጥያቄ እና ሚገርሙ ክስተቶች ይፈጠሩ ጀመር። እየቆየ የ24 ሰዕት ስራዬ ስለ ኒቃብ ማሰብ ሆነ፣ እረጋጋ እንደሆነ ብዬ ሪሳለቱል ሂጃብ የተባለውን ኪታብ መቅራት ስጀምር ቀን ከቀን ፍላጎቴ ጨመረ 😊 አልሃምዱሊላህ በመጨረሻም 3ኛ አመትን አገባድጄ የ4ኛ አመትን ልጀምር ስል ለበስኩት!! በመልበሴ ያገኘሁትን የማይነጥፍ ሰላም፣ ጸጋ.....የመሰሉትን ልተውና ወደ ግቢ ልምጣላቹ ለኒቃብ አዲስም ስለነበርኩኝ የገዛ ጓደኛዬ ራሱ ለባሽ መሆኗን ረስቻለው የግቢውም አካላት ይህ የመከልከሉ ነገር እንዳገረሸባቸው ስለሰማው ማስበው ምን እንደሚገጥመኝና እንዴት እንደምወጣው ብቻዬን እንደሆንኩ ነበር፣ ግን በሚገርም ሁኔታ በሰላም ስገባ እገባለው ካልሆነ ግን ባልተጠበቀ ሁኔታ ብዙ ጊዜ የሆነች እህት ወይም ወንድም አጠገቤ መተው ለኔ መብት ታግለው መልስ ሰጥተው 🗣 አብረን እንገባለን እስልምናን ይበልጥ ወደድኩት!!🤍 አንዱ ለአንዱ እስከተቆረቆረ ድረስ የአሸናፊዎች መንገድ ላይ እንዳለን አስቤ ፍርሃቴ ወቶ በሰላም መኖር ጀመርኩ ከጥበቃ ጋ ሚኖሩ ግብግቦች ለኔ ምንም ቦታ እስከማይኖራቸው ድረስ ሰላሜን አገኘው። እስከመች አትሉኝም??! . . Face Scanner እስኪገጠም ድረስ.... @aaumsu

🔖በ4ኪሎ የቂርዐትና ደዕዋ ክፍል የተዘጋጀ አዲስ የበጋ ደርስ 📚 ፊቅህ(ዲንን መገንዘብ )የተመለከተ ══━━━።◈።━━━━══ 📚ألفية الزبد في فقه الشافعي (ዙበድ) 📌የቂርዐት ቦታ ፦ 4 ኪሎ የተማሪዎች መስጂድ ⏰ሰዐት፦ቅዳሜ እና እሁድ ከጠዋቱ 12:20 ⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻 https://t.me/Qirat4k/668 📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ። https://t.me/+Hr-I7ertvO00ZDQ0 ✴️ይህንን ኪታብ ምን ለየት ያደርገዋል??? 🔴በሻፊኢያ መዝሀብ ደረጃ 3 ኪታብ(7ተኛ  ኪታብ) 🔴1000 ቤት ግጥም(ከዚህ በፊት የተቀራውን ለመሀፈዝ የተዘጋጀ) 🔵 ከዚህ በመቀጠል ያለው ኪታብ ሚንሀጅ የነወዊይ ነው። 💭ኪታቡ የሚጀመረው የፊታችን ቅዳሜ ነው።

ቻሌንጅ 6 --- የሙጃሂድ ጦልሓ ጀዕፈር ምትኮች ___ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ! ! ! የይፋቱ ሸይኽ ጦልሓ ጀዕፈር ከአፄ ዮሐንስ የቦሩ ሜዳ ጉባዔ እና ተከትሎ ከመጣው የጅምላ ጭፈጨፋ ፊትለፊት ቆ
+3
ቻሌንጅ 6 --- የሙጃሂድ ጦልሓ ጀዕፈር ምትኮች ___ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ! ! ! የይፋቱ ሸይኽ ጦልሓ ጀዕፈር ከአፄ ዮሐንስ የቦሩ ሜዳ ጉባዔ እና ተከትሎ ከመጣው የጅምላ ጭፈጨፋ ፊትለፊት ቆመው የታገሉ ብርቱ ሙጃሂድ ናቸው። በሰዓቱ ለነበረው የግዳጅ ጠመቃ ጓዶቻቸው "ደካሞች ነንና እስኪያልፍ እስልምናውን በልባችን ይዘን እንጠመቅ።" ቢሉም እርሳቸው ግን "ቁርዓን ምን እያለ እኛ ለጊዜው ብለን ይህን ሐሳብ እንላለን። ስለመብታችን እና ሐይማኖታችን እንታገላለን። ይህ ሲሆን ሞተንም ገድለንም ሊሆን ይችላል።" በማለት በ25 አመታቸው ወደ አፋር በረሐ ለትግል ገቡ። ባሳዩት ጀግንነትም ጠላት ጭምር፦ "ጠላት ማመስገን ይሆናል እንጅ ማንም አያህለው ጦልሃ ሐጂ ትንፋሹ አረር ያበርዳል ግንባሩ ኮርቦ ጋራ ይንዳል እንደ ጦልሃ ማን ይደለዳል?" ተባለላቸው። አላህ በጀነተል-ፊርደውስ ይቀበላቸውና። እኛም አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እየፈፀመብን ያለውን የመብት ጥሰት በመታገል ላይ ነን። ደካሞች ነን ለሚሉን እንደ አባቶቻችን አይ ቁርዓኑ የሚያዘው ሌላ ነው እያልን ለመንገዱ የሚከፈለውን ልንከፍል ተዘጋጅተናል። ዩኒቨርሲቲው የአንድ አመት ጉዞውን የሚያስዳስስ የፌስቡክ ፖስት አስቀምጧል። ተማሪዎችም በዚያ አንድ አመት ውስጥ የደረሰውን የመብት ጥሰት በመጥቀስ ማስተካከያ ያደርግ ዘንድ በአደባባይ ጠይቀዋል። https://www.facebook.com/100064311447035/posts/pfbid02vjW6EsUScwqSPbyPaSZtFZXPnN6c4GGhc889sjdu9yj3LioLELx2NRW2f3xEZxzNl/ መልዕክታችሁን አስቀምጡ። የፃፋችሁትን ስክሪን ሾት (screenshot) በቦታችን @Niqab_issueBot ላኩልን። ጥያቄ አለን! @aaumsu

የፈጅር ሰላት ሱና በሦስት ነገሮች ይለያል…… ☑️አንደኛው፦      ከሁሉም ሱንናዎች በላጭ ነው። ነብዩﷺ «ركعتا الفجر خير من الدنيا وما فيها» «የፈጅር ሁለት ረካዓዎች ከዱንያና በውስጧ ካለው ነገር ሁሉ በላጭ ናቸው።» ብለዋል። ☑️ሁለተኛው፦      ጉዞም ላይ ይሁን ሀገር ላይ ተኩኖ ይሰገዳሉ። በተቃራኒው የሌላ ሰላት ሱናዎች ጉዞ ላይ ተኩኖ አይሰገዱም። ☑️ሦስተኛው፦        የተለየ የተገደበ የሆነ ሱራ ይቀራባቸዋል። እሱም በመጀመሪያው ረከዓ 📖 "قل يا أيها الكافرون" እና: በሁለተኛው ረከዓ 📖"قل هو الله أحد" ነው።    /ሸይኽ ኢብኑ ዑሰይሚን አላህ ይዘንላቸው/ (شرح بلوغ المرام / ج4 / ص151). 🔻 ለፈጅር የምትሞላው አላርም ላይ 4 ደቂቃ ብቻ አሻሽለህ ብትሞላ «ከዱንያ እና ከያዘችው ነገር በአጠቃላይ የሚበልጥ» ኸይር ማግኘት ትችላለህ ምናልባትም በጊዜ ተኝተን ከፈጅር 20-30 ደቂቃ በፊት ተነስተን ረካተይን የሰገድን እንደሆነ ደግሞ ምንዳው ከፍ ያለ ነው። @fivekjemaa

📢Grand Dawah Program As we navigate our journey as students and prepare for the spiritual transition following the holy mont
📢Grand Dawah Program As we navigate our journey as students and prepare for the spiritual transition following the holy month, the 5 Killo Jamma’ah is honored to invite you to a special afternoon of enlightenment and growth. This program is designed to ground us in our purpose and provide the spiritual stamina needed to maintain our faith throughout the year. 🎙Sessions & Speakers Topic I: Our Mission as a Muslim StudentSpeaker: Ustaz Hussein Yousef   • An exploration of how to balance academic excellence with Islamic identity and our responsibility to the Ummah on campus. Topic II: Istiqamah (Steadfastness) After RamadanSpeaker :- Ustaz zanjabil • Practical steps to keep the spirit of Ramadan alive in our hearts and actions long after the month has passed. 🪧 Event Details 📅 Date : March 28 🕔 Time : After zuhur prayer 📍Venue : Al Aqsa Masjid 🤝 All brothers and sisters are expected to attend. 🤲 May Allah grant us beneficial knowledge and the strength to remain steadfast.

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿اقْرَؤُوا القُرْآنَ فإنَّه يَأْتي يَومَ القِيامَةِ شَفِيعًا لأَصْحابِهِ،﴾ “ ቁርዓንን አንብቡ ፤ እርሱ በቂያማ ቀን ለባልደረቦቹ አማላጅ ሆኖ ይመጣል ። ” [ሙስሊም ዘግበውታል : 80]

መብታችንን ለማስከበር በምናደርገው ጉዞ ውስጥ ተግዳሮቶች ቢገጥሙንም፣ በአንድነት ቆመን ድምፃችንን ከፍ ማድረግ ይኖርብናል። በወጣቶች መካከል ያለው ትብብርና በሀሳብ መጎልበት፣ ለማንነታችንና ለነጻነታችን የምናደርገውን ጥረት ያጠናክረዋል። እያንዳንዱ እንቅስቃሴያችን ለተሻለ ለውጥ መሠረት እንደመሆኑ መጠን፣ በተስፋና በቁርጠኝነት ወደፊት እንገስግስ! የእኛ ድምፅ የነገው ብርሃን ነው! https://www.tiktok.com/@aaumsu/video/7620690047368613138 ቪዲዮዎቻችን ተደራሽነት እንዲኖራቸው የተለመደው ትብብራችሁ ይፈለጋል በተጨማሪ በፌስቡክ ገፆቻችንም ያለንን ተደራሽነት ለማስፋፋት እንተባበር የህብረቱ ይፋዊ የፌስቡክ ገፅ 👇 https://www.facebook.com/share/18ZxvspkBR/ @aaumsu

ዘመቻ 5 --- የጋዚው ኢማም አሕመድ ኢብን ኢብራሒም ወራሾች __ ለBBC: DW: Aljezeera: አናዶሉ: TRT እና መሠል አለምአቀፍ ሚዲያዎች ! ! !   የአዳሉ ኢማም አሕመድ ለእኛ ለወጣቶች ትልቅ ተምሳሌት ናቸው። የልብነድንግል ጦር ከ200 ሺህ በላይ ሆኖ ለወረራ ሲመጣ የእድሜ ማጠር ወይንም የሰራዊት ማነስ አልገታቸውም። በ23 አመታቸው 12ሺህ ሆነው እውነትን ይዘው ግዙፉን ጦር አሸነፉ፤ ለሕዝባቸውም ነፃነትን ሰጡ። የእርሳቸው ልጆች እንደመሆናችን እድሜ ለነፃነት ከመታገል እንደማያግድ እንዲሁም እውነትን ከያዙ ጥቂት ሆኖ ትልቅ የሚመስልን ድል ማድረግ እንደሚቻል በመማር አድገናል። አላህ በጀነተል- ፊርደውስ ይንከባከባቸውና።    በእርሳቸው ስም በሰየምነው ቻሌንጅ ድምፃችንን ለአለምአቀፍ ሚዲያዎች ለማድረስ መንገድ ጀምረናል። በአሁኑ ዙር ለBBC: DW: አልጀዚራ: አናዶሉ እና TRT የምናደርስ ይሆናል። እየደረሰብን ያለውን በመግለፅ እያደረሱት ስላለው ግፍ የዩኒቨርሲቲውን አመራሮች እንዲጠይቁልን እንወተውታለን። ከቃላት በላይ ተግባራት ይናገራሉና ወደ ተግባር የምንገባ ይሆናል። እስከዚያው እስካሁን ያሉትን ቻሌንጆች በማጠናቀቅ ጠብቁን። ዝግጁ ናችሁ? ዝግጁ ነህ? ዝግጁ ነሽ? @aaumsu

To participate in the polls, please first join the 5K Qirat Channel The polls are posted there, so make sure you are a member before voting. Join the channel and take part!

Repost from 5k Qira'at Channel
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته We are preparing an online course that will be streamed on this channel. It is designed to help you gain authentic Islamic knowledge, strengthen your connection with Allah, and explore the depths of Islamic teachings in a way that fits your schedule. The course will be held from Saturday & Sunday each week (exact time according to your preference). مَنْ سَلَكَ طَرِيقًا يَلْتَمِسُ فِيهِ عِلْمًا، سَهَّلَ اللَّهُ لَهُ بِهِ طَرِيقًا إِلَى الْجَنَّةِ "Whoever travels a path in search of knowledge, Allah will make easy for him a path to Paradise." Please let us know which areas of Islamic knowledge you are interested in (such as ʿAqidah, Fiqh, Sirah, etc.), your preferred time, and any other details by voting in the polls below. @qirat_channel_5k

ዲና አብደላህ 3.96፤ ሒክማ ኸድር 3.95 ከራዲዮሎጂ ዲፖርትመንት በማምጣት ከሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች 1ኛ እና 2ኛ ከአጠቃላይ ተማሪዎች ደግሞ 3ኛ በማምጣት በዛሬው እለት ተመርቀዋል። እንግዲህ ዩኒ
ዲና አብደላህ 3.96፤ ሒክማ ኸድር 3.95 ከራዲዮሎጂ ዲፖርትመንት በማምጣት ከሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች 1ኛ እና 2ኛ ከአጠቃላይ ተማሪዎች ደግሞ 3ኛ በማምጣት በዛሬው እለት ተመርቀዋል። እንግዲህ ዩኒቨርሲቲያችን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መሠል ኒቃቢስት ተማሪዎችን ከስኬት አደናቅፎ በጅህልና ለመቅጣት ነው ኒቃብ ለብሶ መማርን በመመሪያ ክልክል ያደረገው። ሆኖም እህቶቻችን ከሁሉም ልቆ በመገኘት በተግባር ተቃውሟቸውን እያሰሙ ነው። ተምረው ከፍ ያሉትን በጥላቻ ዝቅ ማድረግ አይቻልም። በአላህም ፈቃድ መብታቸው ሙሉ ለሙሉ በመመሪያ ደረጃ እውቅና ተሰጥቶት ይማራሉ። እስከዚያም ድረስ መታገል የዚህ ትውልድ ሀላፊነት ሆኗል። ለእህቶቻችን ስኬት እንኳን ደስ አለን! እህቶቻችን እንኳን ደስ አላችሁ!! በተጨማሪም እነርሱም የሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጀመዓም "ፍትሕ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች!" በማለት መልዕክታቸውን አድርሰዋል። እናመሰግናለን!!! @aaumsu

ድምፃችን እያስተጋባ ነው! ትግሉ ይቀጥላል! ይህ የሱመያ ልጆች ፅናትና ወኔ ነው! የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሆይ! ለፍትሕ እና ለማንነታችሁ መከበር እያደረጋችሁት ያለው ተጋድሎ እጅግ የሚደነቅ ነው። ቀደም ባሉት ቻሌንጆች ድምፃችንን ከፍ አድርገን በቅንጅት ስንሰራ የሚኖረንን ተፅዕኖ በተግባር አይተናል። በፌስቡክ እና በቴሌግራም ለዩኒቨርሲቲው ያስተላለፍነው መልዕክት አስተዳደሩ የኮሜንት ሳጥኑን እስኪዘጋ ድረስ አስጨንቆታል። ለሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር፣ ለቲክቫህ እና ለ ATC News ድምፃችንን በሚገባ አድርሰናል። አሁን ደግሞ ተራው የሕዝብ ድምፅ ተብለው የተቋቋሙት የሚዲያ ተቋማት ነው! የላካችሁልን ስክሪንሾቶች (Screenshots) እንደሚያሳዩት ለኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (EBC) እና ለአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ (AMN) ድምፃችሁን እያደረሳችሁ ትገኛላችሁ። እነዚህ ተቋማት የእኛው ናቸው፤ የእኛን ሐቅ ደግሞ እንዲያስተጋቡ የመጠየቅ ሙሉ መብት አለን። መብት እየተገፋ፣ የውይይት በሮች ተዘግተው ግፍ እየተፈጸመ ዝምታን መምረጥ አይቻልም! ገና ያልላካችሁ ተማሪዎች፣ የጓደኞቻችሁን ቁርጠኝነት ተመልከቱ! አሁኑኑ ኒቃብን የሚከለክለው መመሪያ እያደረሰ ያለውን በደል በዝርዝር ፃፉላቸው። መብት በዝምታ አይከበርም! ድምፃችን በአለምአቀፍ ደረጃ ተሰምቶ ፍትሕ እስኪመጣ ድረስ የእኛ ስለሆነው ነገር ሁሉንም መስዋዕትነት እንከፍላለን። እንዴት እንሳተፍ? ለEBC፦ https://www.facebook.com/EBCzena በመግባት "Message" የሚለው ላይ መልዕክታችሁን አስፍሩ። ለAMN፦ https://www.facebook.com/Amnaddistv በመግባት "Message" የሚለው ላይ ድምፃችሁን አሰሙ። የፃፋችሁትን ስክሪን ሾት (screenshot) በቦታችን @Niqab_issueBot ላኩልን። ድል ለፍትሕ! #ፍትሕ_ለአአዩ_ተማሪዎች #መብቴን_አስከብራለሁ #ቻሌንጅ4 #የሱመያ_ልጆች #AAUMSU @aaumsu

ለEBC እና Addis Media Network መልዕክታችንን ማድረስ ጀምረናል። ደርሶናልም የሚል ምላሽ ሰጥተዋል። ዝም ይሉ ይሆን? ዘገባ ይሰሩ ይሆን? ድምፅ ይሆኑ ይሆን? ምላሹን በጋራ የምናይ ይሆና
+3
ለEBC እና Addis Media Network መልዕክታችንን ማድረስ ጀምረናል። ደርሶናልም የሚል ምላሽ ሰጥተዋል። ዝም ይሉ ይሆን? ዘገባ ይሰሩ ይሆን? ድምፅ ይሆኑ ይሆን? ምላሹን በጋራ የምናይ ይሆናል። ቻሌንጃችንን በሱመያ እንደሰየምነው እንደርሷው በትዕግስት በፅናት እንጠይቅ፤ እናድርስ፤ እንሞግት። በአላህ ፈቃድ ድሉ ይመጣል። ማስታዎሻ፦ መልዕክቱን የምታደርሱላቸው ወደ ፔጃቸው እንደገባችሁ ከላይ በኩል የሚታየውን ሜሴጅ የሚለውን መልዕክት ማድረሻ ተጭናችሁ በሚመጣላችሁ በኩል ነው። ጥያቄ አለን: ዛሬም ነገም! ጥያቄ አለን: ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ!! ጥያቄ አለን: ቢሮ ውስጥም በአደባባይም! @aaumsu

ቻሌንጅ 4 --- የሱመያ ልጆች __ ለEBC እና አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ! ! ! በጀመርናቸው ቻሌንጆች ድምፃችንን ከፍ አድርገን በቅንጅት ስንሰራ የሚኖረንን ተፅዕኖ አይተናል። በፌስቡክ እና ቴሌግራም
ቻሌንጅ 4 --- የሱመያ ልጆች __ ለEBC እና አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ! ! ! በጀመርናቸው ቻሌንጆች ድምፃችንን ከፍ አድርገን በቅንጅት ስንሰራ የሚኖረንን ተፅዕኖ አይተናል። በፌስቡክ እና ቴሌግራም ለAAU መልዕክት ስናስተላልፍ ኮሜንት ሳጥኑን እስከመዝጋት ደርሷል።ለሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር የመጀመሪያውን ዙር መልዕክት አድርሰናል።ቲክቫህ እና ATC News ድምፅ እንዲሆኑን ከእኛ ያለውን በሚገባ አድርሰናል። ድምፃችን በአለምአቀፍ ደረጃ ተሰምቶ ፍትሕ እስኪመጣ ድረስ የእኛ ስለሆነው ከእኛ ያለውን ሁሉ እንሰጣለን። ቻሌንጁን በመጀመሪያዋ የኢስላም ሰማዕት በሆነችው ሱመያ (ረዲየላሁ ዐንሃ) ሰይመነዋል።ታሪኳን እየሰማ እንዳደገ ኡማ ለእስልምና ክብር ተብሎ ስለሚደረግ ትዕግስት እና ፅናት፣ ስለሚካሄድ ትግል ብሎም ስለሚከፈል መስዋዕትነት ተምረናል።እዚህጋ በሒጃብ ጉዳይ ስለተነካ ክብር ለሚደረግ የድምፅ ማሰማት ቻሌንጅ ጊዜያችንን እንሰጥ ዘንድ ተጠርተናል። የአሁኑ በእኛው ከተቋቋሙት የሚድያ ተቋማት መካከል ነው።ሚዲያዎቹ የሕዝብን ድምፅ በፍትሐዊነት ያስተጋቡ ዘንድ የተቋቋሙ ናቸው።የእኛው ናቸውና የእኛን ድምፅ ያስተጋቡ ዘንድ ንገሯቸው።ከሐቃችን ናቸውና ሐቃችን እየተየካ ሳለ ዝም ማለት እንደሌለባቸው አስታውሷቸው። ለEBC እና AMN ማለት ነው። ኮሌጃችሁን እና የትምህርት አመታችሁን በመጥቀስ ሒጃብን (ኒቃብን) የሚከለክለው መመሪያ ከወጣ ቡሃላ እየደረሰ ስላለው ነገር፤ዩኒቨርሲቲው የውይይት በርን ዘግቶ እየፈፀመ ስላለው ግፍ ፃፉላቸው። ለEBC https://www.facebook.com/EBCzena ፤ ለAMN https://www.facebook.com/Amnaddistv ሚሴጅ የሚለው ላይ ፃፉላቸው። የፃፋችሁትን screenshot @Niqab_issueBot ላኩልን። @aaumsu

ድምፃችን እያስተጋባ ነው! ትግሉ ይቀጥላል! ይህ የኡመር (ረ.ዐ) ልጆች ወኔ ነው! የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች፣ ለፍትሕ እና ለመብታችሁ መከበር እያደረጋችሁት ያለው ተጋድሎ የሚደነቅ
+8
ድምፃችን እያስተጋባ ነው! ትግሉ ይቀጥላል! ይህ የኡመር (ረ.ዐ) ልጆች ወኔ ነው! የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች፣ ለፍትሕ እና ለመብታችሁ መከበር እያደረጋችሁት ያለው ተጋድሎ የሚደነቅ ነው፡፡ በ"ቻሌንጅ 3" መሰረት ለቲክቫህ (Tikvah) እና ATC News እያደረሳችሁት ያለው ድምፅ፣ በዩኒቨርሲቲው አስተዳደር የተዘጋውን የውይይት በር ለመስበር የመጀመሪያው እርምጃ ነው፡፡ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ለምን የተማሪዎችን ሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብት መጣስ እንደመረጡ ምላሽ እስኪሰጡ ድረስ አንታክትም፡፡ ለATC New፦ @mujaabot ላኩላቸው። ለቲክቫህ፦ @tikvahethiopiaDM ላኩላቸው። ይህ የላካችሁት ስክሪን ሾት (screenshot) የቁርጠኝነታችሁ ማረጋገጫ ነው፡፡ ገና ያልላካችሁ ተማሪዎች፣ አሁኑኑ ድምፃችሁን አሰሙ! መብት በዝምታ አይከበርም! ያሰፈራችሁትን መልዕክት screenshot አድርጋችሁ @Niqab_issueBot ላኩልን። #ፍትሕ_ለአአዩ_ተማሪዎች #መብቴን_አስከብራለሁ #ቻሌንጅ3 #AAUMSU @aaumsu

ኢዳችንን ስለመብታችን እየጠየቅን በብርታት አሳልፈናል። ከተለያየ ቦታ ያሉ ሕፃናት ጭምር ድምፃችንን እያሰሙ፤ እኛም ስለ ጥያቄያችን ለሚዲያዎች አቤት እያልን በስኬት ተወጥተናል። ሆኖም የትላንቱ ጅማሮ እንጂ መጨረሻ አይደለም፤ መነሻ እንጂ መድረሻም አይደለም። እየደረሰብን ስላለው መላው አለም ያውቅ ዘንድ እንሰራለን። እየደረሰብን ያለው ቆሞ ፍትሕ እስኪሰፍን ድረስ በትብብር፣ በቅንጅት፣ በአንድነት እንሰራለን። ከትውልድ ተረክበን፤ ለትውልድ ስለምናስተላልፍው አደራ በትጋት እንንቀሳቀስ ዘንድ ግድ ሆኗል። ዝግጁ ናችሁ ያኡመተ ሙሐመድ _ ድምፃችሁን ለማሰማት ! ዝግጁ ነህ ወንድሜ ___ ስለመብትህ ለመጠየቅ !! ዝግጁ ነሽ እህቴ ___ ስለነፃነትሽ ለመሞገት !!! @aaumsu

السلام عليكم ورحمت الله وبركاته ነገ የሸዋል ፆም ይጀመራል። የሸዋል ፆም ማለት ለፈርድ ሰላት ሱና እንደምንሰግደው ከፈርድ ፆም በኋላ ያለ ሱና ፆም ነው። ❇️የሸዋልን ፆም መፆም የፈለገ መጀመሪያ የረመዷን ቀዷዕን መጨረስ አለበት።(ይወደዳል) 💥 ምክንያቱም ሀዲሱ የሚለው من صام رمضان ثم اتبع ست من شوال(ረመዷንን የፆመ ከዛ የሸዋልን 6 ቀን የፆመ) ነው የሚለው 🌐ስለዚህ ቀዷ ያለበት ሰው ረመዷንን ስላልፆመ ቀዷን ይጨርስ 💠 ምንዳው ደግሞ ረመዷንን ፁሞ የሸዋልን 6 ቀን ያስከተለ አመቱን ሙሉ እንደፆመ ነው። ምክንያቱም ይህ ሰው 36 ቀን ፁሟል 1 ሀሰና ደግሞ በ10 ነው ሚባዛው ስለዚህ 360 ቀን እንደፆመ ይቆጠራል። ❇️ ሰውየው 6ቀን ፆም ከፈለገ አከታትሎ ከፈለገ ለያይቶ በሸዋል ወር ብቻ ይፁመው ፤ ነገር ግን በላጩ አከታትሎ ከኢድ በኋላ ቢፆመው በላጭ ነው። ⚜️ ከዛ በተረፈ ፆሙን ሁሉም ነው የሚፆመው አንዳንድ ቦታ 40 አመት ካልሞላ አይፆምም የሚባለው መሰረተ ቢስ ወሬ ነው። ❇️ ከዛ በተረፈ ሸወሊድ(የሸዋል ኢድ) ወይም ትንሹ ኢድ የሚባል ቅራቅንቦ እስልምናን አይወክልም። (ኢብን አቢ ዱንያ ፡ ሸዋል 1/1447)