uz
Feedback
ስልክ መግዣና መሸጫ

ስልክ መግዣና መሸጫ

Kanalga Telegram’da o‘tish

ማንኛውም መሸጥ የምትፈልጉትን ስልክ እንገዛለን በ #0909255008 ወይም #0912739699 ላይ ያናግሩኝ @Abd_phone

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali ስልክ መግዣና መሸጫ analitikasi

ስልክ መግዣና መሸጫ (@jijiphone) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 51 986 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 2 546-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 606-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 51 986 obunachiga ega bo‘ldi.

03 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -1 624 ga, so‘nggi 24 soatda esa -32 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 0.57% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 0.18% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 298 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 96 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 1 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
ማንኛውም መሸጥ የምትፈልጉትን ስልክ እንገዛለን በ #0909255008 ወይም #0912739699 ላይ ያናግሩኝ @Abd_phone

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 04 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

51 986
Obunachilar
-3224 soatlar
-3207 kunlar
-1 62430 kunlar
Postlar arxiv
#ከደሀ_ልጅ_ፍቅር_እዉነተኛ_የከድሬ_ታሪክ ምን ትምህርት እንወስዳለን?? እስኪ የእኔ አስተያየት ነዉ፡፡የእናንተን ደሞ እቀበላለሁ፡፡ 🔷እንደ ከድር ያለ ታማኝ ወንዶች መንራቸዉን እንድታቁ ነዉ ብዙ ጊዜ ታሪክ ላይ ወንድ ልጅ ሲበድል ነዉ የማቀርበዉ ይሄ ግን ይለያል ከድር ማለት ባጃጅ ኑሮት አላህን ፈሪ አንድ ቀን ዚና ሊሰራ እንኳን ጉንጯን ስሟት የማያቅ ሀላል ብቻ የሚመኝ ..ከትዳር በፊት ዚና አልሰራም ብሎ በስደት የተሰቃየ ከዛም እሷ ቃሏን አጥፋ አግብታ ብዙ ነገር እንደሆነ አይተናል፡፡ እንደ ከድርም ተቅይ አላህን ፈሪ ወንዶች እንዳሉ ሴቶች ልትረዱ መቻል አለባችሁ፡፡ 🔷 በአሁኑ ወቅት ሴቶች እህቶቻችን የባጃጅ እና የተለያየ መኪና ሹፌር ጋር ያላቸዉ ግንኙነቶች በጣም ከልክ ያለፈ ነዉ፡፡ ምን እንደምል አላቅም አንዳንድ ባለ ትዳሮች ጋር እንኳ ይታያል ግን ለምን ??? አንቺ እኮ በባጃጅ ወይም በታክሲ ስትሄጅ አይ ልሸኝሽ ይልሻል ግን ለአንቺ ክብር እንዳይመስልሽ አንቺም ደስ ብሎሽ እሺ ትያለሽ ግን የተወልሽ ብር እኮ ብዙ አይደለም ከ 3 ብር አይበልጥም እንዴት አንቺ እንደዉለታ ትይዥዋለሽ ??? እንደ ከድር ያሉ ሹፌሮችን ግን አይጨምርም 🔷 እህቴ አንዳንድ ታክሲ ላይ የተለያዩ ጥቅሶች አሉ ለምሳሌ #ሹፌሩን በፍቅር እንጂ በጠብ መቅረብ ክልክል ነዉ ..ፍቅርን እና መሸኘትን ከሹፌር ተማሩ ወ.ዘ.ተ ብዙ ባጃጆች የፃፉት ጥቅስ #ከትርፉ #ላይፉ የሚል ብዙ ባጃጆች አሉ... አየሽዉ ምን ማለት ነዉ??? ላይፍ እያልሽ የሴት ወዝሽን እርግፍ እንዳታረጊ አንቺ መንቃት አለብሽ፡፡ ♠በአሁኑ ሰአት በባጃጅ እና የታክሲ ሹፌሮች ስንት ሴት እህቶቻችን ሂወት ተበላሽ?? እኔ ወላሂ ብዙ አዉቃለሁ ስለሆነም አንቺ ኮስታራ ልትሆኝ ይገባል በባጃጅ ሸኘሽ ቢባል ከ10 ብር አይበልጥም ስለሆነም ልትጠነቀቂ ይገባል ☞በአሁኑ ሰአት ሴቶች እህቶቻችን በሀራም መንገድ ድንግልናቸዉን ከሚያስወስዱት 60%ሹፌር ይይዘዋል፡፡ ሀራሙን እየፈቀድኩ ሳይሆን ያዉ እየተሰራ ያለዉን ለማስረዳት ነዉ 🔷አንቺ ድንግልናሽን ለሀላል ባልሽ ልታረጊ ምን ያህል ዝግጁ ነሽ ?? ከአገባሽ ቡሀላ ችግር ያመጣብሻል አንቺስ ለምን ተሳቀሽ ትኖሪያለሽ ??ለ 15 ደቂቃ ስሜት የ40 ወይ የ50 አመት ፕላንሽን እንዳታበላሺ ፡፡ 🔷ደሞ አንተ ምንድን ነዉ ባጃጅ (ታክሲ) አለኝ እኔ ግን ጨዋ ነኝ እያልክ ነዉ ፡፡ እኔ አንተን አይደለም ወንድሜ እንደ ከድር ያሉ ሹፌሮችን አይጨምርም ...ግን ሌሎች ስላሉ በዛዉም ለማስተማር ነዉ፡፡ ከ100 ዉ 80 ፐርሰንት ግን ሴቶች እህቶቻችንን እያበላሹ ነዉ ያሉት፡፡ አንተም ታቀዋለህ ባጃጅ እና ታክሲ የቤት መኪና ያለዉ ሀራም ሲሰራ መዝናኛ ለመዝናኛ ሻይ ቤት ትምህርት ቤት ቁመዉ ታያለህ፡፡ ስንት ሰዉ መክረህ እንዲተዉ አርገሀል ??? ☞እህቴ መቼም ከትምህርት ስትሄጅ ወይ ስትመለሽ ልሸኝሽ እያለ ሊያስቸግርሽ ይችላል፡፡ አንቺ የዛን ጊዜ እሺ ብለሽ ከገባሽ አለቀልሽ ሁሌም በተመሳሳይ ሰአት ማመላለስ ያስለምድሻል.... ደሞ ሴት ከወደደች ወደደች ነዉ፡፡ የማይመለሰዉን ድንግልናሽን እንዳታስረከቢ ☞ግን የሚገርመኝ ጃፓን መኪና ስሰራ ሹፌር የሚያስወድድ መሪዉ ጋር የቀበረችበት ያለ ነዉ የሚመስለዉ የአሁን ሴቶች ለሹፌር ያለዉ አመለካከታቸዉ ፡፡ ታክሲ ሲገቡም ..በመኪና ሲሄዱ የሚገቡት ጋቤና ነዉ የሹፌሩ ወሬ ናፍቋቸዉ ይሆን ወይስ ጋቢና ከሆኑ ቶሎ ይደርሱ ይሆን.....    ስንት ነጋዴ ዲን ያለዉ ጥሩ አህላቅ ያለዉ ለጋብቻ እየጠየቃቸዉ አናገባም ብለዉ ከጋብቻ በፊት ከሹፌር ጋር ባላቸዉ ግንኙነት እነሱን አምነዉ የተቀመጡ ..ድንግልናቸዉን ያጡ,,,.አግብተዉ የፈቱ የስንቱ ሂወት ተበላሸ እናንተ ታቃላችሁ እኔም የማቀዉ አለ፡፡ 🔷 #እህቴ ይቅርታ እኔ ጋር አታፍጭ እኔን እንዴት ይህን ይፅፋል ብለሽ የተቆጣሽ መሰለኝ እኔ እኮ አንቺን አይደለም እየተናገርኩ ያለሁት እነ እሱን ነዉ ስነ ስርአት ከሌላቸዉ ሹፌሮች ጋር ግንኙነት ያላቸዉን ነዉ ፡፡ ደሞ እነሱ እህቶቼን ጠልቼ ሳይሆን ያለፈዉ አልፏል ለወደፊት ከእንደዚህ አይነት ግንኙነት እራቂ ነዉ እያልኩ ያለሁት ☞አንቺስ ጓደኛሽ ከእንደዚህ አይነት ሀራም ግንኙነት እንዳታረግ ለዲን እህትሽ ምን እየሰራሽ ነዉ ??? 🔷 #አንተስ ወንድሜ ለምን በእህትህ ላይ ሲፈፀም የማወደዉን በሰዉ እህት እንዲፈፀም ትወዳለህ?? አንተ የሌላን ሰዉ እህት ይዘህ መዝናኛ ወደ ጎጆ ስታሳልፍ የአንተን እህት እዛ ሌላ ሰዉ ጋር ብታያት ምን ትላለህ?? በሰፈሩት ቁና መሰፈር አይቀርም ፡፡ 🔷 #እኛ #ሙስሊሞች ከለያዩ ብዙ መጥፎ ቻናሎች ስሜትን የሚቀሰቅሱ የፍቅር የሚወራባቸዉ እና የባለጌ Video ከሚለቀቅባቸዉ ቻናሎች መራቅ አለብን ከዛሬ ጀምረን መዉጣት አለብን፡፡ 🔷 #School #life ትምህርቤት ላይ መጠንቀቅ አለብን ብዙ ተማሪዎች አስረኛ ክፍል ማትሪክ ከመፈተናቸዉ ወይም ከተፈተኑ ቡሃላ ጓደኞች ነን ብለዉ ከቆዩት ጋር program በማዘጋጀት የተለያዩ መዝናኛ ቦታ በመሄድ ወንጀል ሰርተዉ ይመለሳሉ፡፡ ተማሪዎች ጥንቃቄ አድርጉ ይህ program እንደ ፋሽን የተያዘ ሁኗል፡፡ ብዙ ሴቶች እህቶቻችን በዚህ አይነት program የደስታ ቀናችን ነዉ እየተባለ ብዙ እህቶቻችን ወንጀል እየሰሩ የማይመለሰዉን ድንግልናቸዉን እያስወሰዱ ነዉ፡፡ ከባድ ጥንቃቄ ትምህርቤት ላይ እስኪ ለፈገግታ😂 መኪና ያለው የሃበሻ ወንድ ፦ ታክሲ ተራ ከብዙ ሰው መሃል ሴቷን ለይቶ ልሸኝሽ ፤ መኪናው ስትበላሽበት ከብዙ ሴቶች መሃል ወንድ ፈልጎ "ብራዘር ተባበረኝ!" ይላል!😂 ነገሩ አሁን ላይ እንደዚህ ነዉ ፡፡ ሽማግሌ አቅመ ደካማ ቁመዉ ግን መርጠዉ የሚወስዱት ሴቶችን ነዉ ይህ ሀቅ ነዉ ከአንዳንድ ሹፌሮች ግን አሉ እነዛን አያካትትም... ✅እስኪ ወደ ታሪኩ ዙሪያ ስመለስ ከድር ይህን ሁሉ መሰወአትነት ከፍሏል፡፡ አንድ ነገር ማሰብ ያለባችሁ ለአንዳንድ ባለጊዜ የሀብታም ልጆች ካልሆነ በቀር ሕይወት አልጋ በአልጋ አይሆንም ብዙ ዉጣ ዉረድ እንዳለዉ መረዳት መቻል አለብን...ደግሞም ዱአ ማድረግ ያለብን ከድር ይሳካል ብሎ በአላህ ቀድር እና በአባቷ መጥመም ምክንያት ሳይሳካ ቀርቷል አላህ ከእንደዚህ አይነት ይጠብቀን ከፍቅር ስቃይ ያዉጣን ዱአ ያስፈልጋል፡፡ ✅በተጨማሪም ከድሬ ያሳለፈዉ ስለ ስደት ስለበሀር ጉዞ አንድ ባንድ ምንም ሳናስቀር በባህር የሚሔዱ ሰዎች መንገላታት እና ስቃይ አይተናል፡፡ ምንም ዉሸት የለዉም ለምን ቦታዉን ሳይቀረን ከጅቡቲ ጀምሮ በየመን አልፎ እስከ ሳዉዲ አረብያ ያለዉን የስቃይ የባህር ጉዞ ዳሰናል፡፡ ወላሂ ያለፈበት የሄደበት ይሄን ታሪክ ሲያነብ እዉነቱን ነዉ ይላል ያለፈዉ ትዝ ሲል እምባ ይተናነቀዋል....ስለሆነም ምርጥ የኢስላም ወንድም እና እህቶቼ ስደትን አደራ አትሞክሩ በበሀር ሂዳችሁ ስቃዩ ብዙ ነዉ እዚሁ ኢትዮ ተከባብረን ተካፍለን እንበላለን ፡፡ ስደትን በባህር መሔድ ያሰባችሁ በከድር ያለፈዉን ፈተና እንደሚገጥማችሁ እወቁ ስለሆነም ከተቻለ በህጋዊ ሒዱ ካልሆነ ግን ማረኝ ሀገሬ ብለን አድበን ብንቀመጥ ይሻላል፡፡ ✅በታሪኩ አህባሽ የሙስሊም ኡማዉን እንዴት እንደጎዳዉ ተካቷል..ታሪኩ ምንም የተቀነሰ የተጨመረ የለዉም፡፡ ሁላችንም በአስር ጣታችን የምንፈርመዉ እዉነታ አለዉ አህባሽ ማለት ጭንብል ለብሶ ሙስሊሙን ለማዳከም የመጣ ኢስላምን መስሎ ግን ከሌሎች ሀይማኖቶች በላይ ኢስላምን የሚጎዳ ..ትዉልዱን አደንዝዞ ስራ ሰሪ ቁርአን ቀሪ ..ሀፊዝ የሆኑትን ለማዳከም የመጣ ከመጣም ቡሀላ ትዉልዱን👇👇👇

በቀን ውስጥ ብዙ ዶላሮችን በቴሌግራም ማግኘት የምትችሉበት የተረጋገጠ ነው🎊 ያልጀመራቹ ለመጀመር የምትፈልጉ 👇#Major በዚህ ሳምንት ወደ token convert እንደሚደረግ አሳወቀዋል ፤ Focus አድርጋችሁ ስሩ 👇👇 https://t.me/major/start?startapp=1753715732 https://t.me/major/start?startapp=1753715732

እኔ በሰአዳ ፍቅር ዝሙት አልሰራም ሶላት አልተውኩም እንጅ በጣም ከዲኔም ወርጀ ነበር ለጥቅም ሳይሆን ለአላህ ብሎ የሚወደን የምንወደዉ ጓደኛ ይስጠን.....ከአንጃችሁ አሚን በሉ.....ለእኔም ከአንጀታችሁ ልጅ እንድወልድ ዱአ አድርጉልኝ፡፡         የተንዛዛው ታሪኬ ይህን ይመስላል፡፡ ከእኔ ትክክለኛ የህይወት ታሪክ አካፈልኳችሁ... ቁም ነገር ካገኛችሁበት ለሰወች አስተላልፉት ፡፡ የማይጨበጥ ፍቅር ዉስጥ ያላችሁ ከእኔ ታሪክ ተማሩ ...እኔ ፍቅርን እስከ ጥግ ድረስ ሒጃለሁ.....በፍቅር መሰወአትነት ቢሆን ሰአዳን አላጣትም ነበር ...ግን ፍቅርም ቢሆን ግድ አላህ ፈጣሪ ጋር ካልተፃፈ የእኔ ይሆናል ብለህ ያሰብከዉ እንደማይሆን ከታሪኬ ትምህርት ዉሰዱ    ታሪኩ ላይ ስሜም አልተቀየረም  ከድር ሙሀመድ አህመድ ነኝ ከወሎ ከሀርቡ ከተማ  አመሰግናለሁ ፡፡ ወሰላሙ አለይኩም ወረህመቱሏሂ ወበረካትሁ    #ተ......... #ፈ............ #ፀ.............. #መ....

🎁〰〰〰እዉነተኛ ታሪክ〰〰〰🎁   የታሪኩ ርዕስ 😢 #ፍቅር_እንዲህ_ነዉ_ወይ??❓      #የመጨረሻዉ_ክፍል ✍ ፀሀፊ #አሚር_ሰይድ ............የደሀ ልጅ ፍቅር.............    መፅሀፉን ገዛሁት ስገልጠው ላይመራንስ ወይንም ወህመል ሁብ ይላል በአማረኛብውም፡ #የማይጨበጥ_ፍቅር እንደማለት ነው በባዶ ሲደክሙ መኖር  ማለት ነዉ፡፡    መፅሀፉን ተረጋግቼ አነበብኩት የእኔን ሙሉ ህይወት ታሪክ ስቃየን የፃፈው ነው የሚመስለው..ገረመኝ ...... የእኔ በሽታ መፅሀፉ ላይ አለ፡፡ መፀሀፉን አንብቤ እንደጨረስኩ... ምነው እንዲህ ሳልጎዳ በፍቅር ሳልሰቃይ አንብቤው ቢሆን ???? እላለሁ፡፡    እንደ እኔ በፍቅር የተጎዳችሁ #ፍቅር_በኢስላም የሚለዉን መፅሀፍ አንብቡት ወላሂ እኔ መፅሀፉ በጣም ጠቅሞኛል እራሴን እንድፈትሽ አድርጎኛል.....የማይጨበጥ የፍቅር  ስሜቴን በጣም ቀንሶልኛል፡፡ መፅሀፉን ካነበብኩ ቡሀላ የተሻለ ህይወትን ለማግኝት መጣጣር ይዣለሁ......የተሻለ ስራ ለመስራት ልጅ ለመዉለድ ምኞት ላይ ነኝ፡፡  መሃመድ ሞባይሌ ውስጥ ያለውን ካዕባ ዘንድ ይተነሳሁትን ፎቶና ዱባይ ቡርጅ ከሊፋ ከአለም አንደኛው ህንጻ ላይ ቡሃይራት ባህር ዳርቻወች የተለያዩ መዝናኛ ቦታ የተነሳሁትን ፎቶ ሲያይ አንተኮ ያየን የለምንጅ ያላየነ የለም ነህ ይለኛል ..... እውነቱን ነው ብዙ ነገር አይቻለሁ ግን ባለዚህ ያለኝ የለም ፡፡ ስለ ኑሮው ዘይቤ ስለ ነገራቱ ሁሉ ያስረዳኛል .....የሕይወት ግብ አላማ እንዲኖረኝ ይጎተጉተኛል        ሙሀመድ እና አሁን ያገባኋት ሚስቴ ራውዳ አላህ ለኔ የላከልኝ መስሎ ነው የሚታየኝ ልብሴን ከመቅደድ ነው የታደጉኝ ፡፡ መሀመድም ደግሞ  ቡኻሪ ኪታብ እንጀምር ብሎ ኪታብ መቅራት ጀመርን፡፡ ከቀራን ቡሀላ ስንከርር  ስለሁሉም ነገር ይመክረኛል .፡፡ አልሀምዱሊላህ ያ ሁሉ ቅዥት ለቆኛል ......ሰአዳ ለኔ እንዳልተፈጠረች አመንኩኝ ከሰአዳ ተስፋ ቆረጥኩ፡፡     ላይመራንስ ራሱን የቻለ እንደሌሎች በሽታወች ህመም ያለውና የራሱ ህክምና ያለው የፍቅር በሽታ ነው መነጫነጭ ግትርነት አለመግባባት ምግብ መቀነስ ስራ ጠልነት ተስፋ የመቁረጥ ስሜት ብሎም እስከ አዕምሮ ዘገምተኝነት ጭንቀትና እብደት እራስን ማጥፋት ሞት የሚያደርስ የፍቅር በሽታ ነው ፡፡በዚህ የፍቅር በሽታ የተጠቁ ሰወች ያጧትን ልጅ ደግመው ቢያገኟት እንኳን ተስማምተው የመኖር ችሎታው አይኖራቸውም ምክንያቱም አፍቃሪው ለተፈቃሪው የሚሰጠው ትልቅ ግምትና ሲገናኙ የሚያገኝው አናሳ ነገር ስለሚሆን.... ለዚህ ነው የደከምኩት ራሴን የጎዳሁት የሚል ፀፀትና ብስጭት ውስጥ መልሶ ይገባል     ይህ በሽታ ከፈጣሪም ጋር የሚያራርቅ ነው የፈለጉትን ነገር ሲያጡ ፈጣሪን ማማረር ኢባዳን መቀነስ ሙሉ ለሙሉም ከፈጣሪ ያለውን ግንኙነት የሚተውና... ነርቨስ ሆነው ከጥቅም ውጭ የሚሆኑ ለአልጋ ቁራኛ የሚዳረጉ ራሳቸውን የሚያጠፉ ሁሉ አሉ ሰው መሃል ሆነው ባልታሰበ የሃሳብ ነውጥ ውስጥ ገብተው ቢጠሯቸው የማይሰሙ ቢቆነጥጧቸው በሃስብ ተውጠው በቶሎ የማይነቁ በለቅሶ የሚንሰቀሰቁ ብቻቸውን ሆነው የሚያወሩ ብዙ ናቸው አደገኛ ነገር ነው፡፡     ከዚህ የፍቅር ስቃይ ለመላቀቅ መድሃኒቱና ብቸኛው መፍትሄ የሳይኮሎጅ ባለሙያወችን ማማከርና በንፁህ ልብ ወደ አላህ መመለስ ብቻ ነው ብቻ በጥቂቱም ቢሆን ይህ በሽታ የሞከራችሁ ካላችሁ ፍቅር በኢስላም እይታ የሚለውን መጽሃፍ ብታነቡ የበለጠ ተጠቃሚ ትሆናላችሁ፡፡ እኔን ምርጥ ጓደኞቸ ሳይኮውን አክመውኛል በአላህ ፈቃድ ተፈውሻለሁ አልሃምዱሊላህ! ! አሁን በጣም ደስተኛ ነኝ፡፡ ሰአዳ አሁን ትዝም አትለኝም፡፡  ✍ #የከድሬ አስተያየትን ፅፌ የላከልኝ አንብቡት  ይሄን ታሪክ የፖሰትንላቹ ለእኔ ከንፈራችሁን እየመጠጣቹ እንድታዝኑ ሰአዳንና ቤተሰቧን እንድትወቅሱ አይደለም ማዘንም መውቀስም ይቻላል  የሰው ልጅ ባህሪ ነውና፡፡ ግን ለራሳችሁ የወደፊት ህይወት ትምህርት እንዲሆናችሁ ነው በዚህ ታሪክ ትልቁ ተወቃሽና ጥፋተኛው እኔው ባለታሪኩ ከድር ነኝ፡፡ ለምን ጥፋተኛ ሆንክ ብትሉኝ _እኔ ባልሳሳት ኖሮ ሌሎቹም አይወቀሱም ነበርና ይሄን ሁሉ መዘዝ ያመጣብኝ መጀመሪያ ቀን በአይኔ ጠቅሻት ያመጣሁት የአይን ክህደት ነው ከዚያም አልፎ ተርፎ የሚታመነው ሰዉ ቢረሳህ የማይረሳው አላህ እያለ ሰውን ከአላህ በላይ አምኜ ነው ስህተት ውስጥ የገባሁት ካዕባ ላይ ሁሉ ሁኜ  ዱአ  ሳደርግ ምንአለ  ሷልህ ሚስት ጥሩ ዝርያ ስጠኝ ብየ ብለምን ኑሮ አንዲትን ለእኔ መጻፏን እርግጠኛ ያልሆንኩባትንና ለአንተ ጥሩ አይደለችም ብሎ እያራቀልኝ ያለን  ልጅ ስሟን እየጠራሁ ስሟገት ራሴን በራሴ ስሸውድ ነው የቆየሁት ፡፡ ይሄ ሁሉ ጣጣ በራሴ ያደረኩት ስለሆነ ስቃዩም ሁሉም ነገር እንኳን የሆነ ይገባኛል ___ አሁንም ጥፋተኛው እኔ ነኝ ስለአላህ በመጠኑም ቢሆን የሚያውቅ ሰው በሴት ፍቅር ከተለከፈ ለምንም የማይጠቅም ነው የሚሆነው ስለዚህ ይህን ታሪክ ያነበባችሁ ሙስሊሞች ሁሉ ከአላህ ውጭ ማንንም አታስቀድሙ ማለቴ ሸሪዐውን ለመከተል ሞክሩ ከኒካህ በፊት ፍቅር የባዶ እብደት ነው እዚህ ላይ ማንንም መውቀስ አያስፈልግም፡፡ ለናንንተ ባልነግራችሁም አላህ በጣም ፍሃዊ ነው ማካካስ ይችልበታል ፡፡ ሁሉንም በአይን በህይወት እያየነው ነው ከናንተ የሚጠበቀው ለራስ መመከር ብቻ ነው      እኔ ብዙ ጓደኞች አሉኝ በጣም አላህንም የሚፈሩ እና ሌሎች ደግሞ ከብዙ ሴቶችም ጋር የሚንጋጉ ሴት ለነሱ ምንም የማይመስላቸው ቀን በቀን የሚቀያይሩ ላንዱ ከባድ የሆነችን እንስት በእጃቸው አስገብተው የሚጎዱ ስለምንም የማይጨነቁ እንደውም እኔ ባሳለፍኩት ታሪክ በእኔ የሚበሳጩ እንደዚህ መሆንህን ያኔ ብናውቅ ኖሮ እኛው ጉድ ሰርተንህ ተስፋ እናስቆርጥህ ነበር ብለው የሚበሳጩ አሉ ግን ዋናው ቁም ነገሩ ግን አላህን መጠንቀቁ ነው፡፡  ረሱል እንዲህ ይሉናል" የትም ቦታ ሆነህ አላህን ፍራው" " ሃራም ለመስራት አላህን ካላፈርከው ግን የፈለከውን ስራ ትመነዳዋለህ" የሰው ልጅ ዋናው መካሪው ህሊናው ነው  ስለዚህ ስትፈልገው ያጣሃውን እንዲፈልግህ ከፈለክ መጀመሪያ የሚቀድመውን አስቀድም ለፍቅሩም ለትዳሩም ልጅ ለመውለዱም ትደርስበታለህ    ቢያንስ ይሄ ታሪክ ለእኔ ጥቅም ባይኖረውም ለእናንተ ግን ትመከሩበታላችሁ ብየ አስባለሁ ይህን ታሪክ እንድነግራችሁ ያስገደደኝ የህይወት መሰናክል በሚል ርዕስ የቀረበዉ እዉነተኛ ታሪክ የደሴዎቹ ልጆች የነሳዳም ታሪክ ነበር የልጅቷ አባት ያለው ቀናነት የስምንት መቶ ሺህ ብር ቤት ገዝቶ የሰራተኛየ ልጅ ነው ሳይል አላህን ፈርቶ የሚወዳትን ሴት ልጁን ለሳዳም የሰጠበት መንገድ በጣም ስላስደሰተኝና ከእኔ ታሪክ ተቃራኒ ሆኖ ስላገኝሁት ያ ታሪክ የኔን ታሪክ እንዳወጣውና እንድነግራችሁ አስገደደኝ ዉድ የዚህ ቻናል አባሎቼ ታሪኬን አነበባችሁት መውለድ ፈልጋለሁ አላህ ያድርግልህ በሉኝ.... አላህ አሪፍ ነገር የተሻለ ነገርን  ይፈጥርልኝ ዘንድ ምኞቴ ነው፡፡   ከአላህ ቀደር ጋር ያን ሁሉ ነገር ያሳጣኝ  ገንዘብ ነውና የወንድ ልጅ አቅሙ ገንዘብ ነው፡፡ አላህ ሀላል የሆነ ገንዘብ ሰጥቶን የምንሰድቅበት የቲም የምንከባከብበት ያድርገን   ....ከዛ ሁሉ ስቃይ ስደት ጠብቆ እዚሁ አገራችን ሰርተን የምንለወጥ ያድርገን ...አላህ የወደድ ነዉን አያሳጣን .. አላህ ጥሩ ጓደኛ ይስጠን ለምን ብትሉ ሒወቴ ከተበላሸ ቡሀላ የተስተካከለዉ በጓደኛየ ጥረት ነዉ.👇👇

በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተው የፍቅር ታሪክ ዛሬ የመጨረሻው ክፍል ይለቀቅ የምትሉ ብቻ #Start የሚለውን ይጫኑ 100 ሲገባ ይለቀቃል ወዲያው👇👇👇
በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተው የፍቅር ታሪክ ዛሬ የመጨረሻው ክፍል ይለቀቅ የምትሉ ብቻ #Start የሚለውን ይጫኑ 100 ሲገባ ይለቀቃል ወዲያው👇👇👇

በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተው የፍቅር ታሪክ ዛሬ የመጨረሻው ክፍል ይለቀቅ የምትሉ ብቻ #Start የሚለውን ይጫኑ👇👇👇
በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተው የፍቅር ታሪክ ዛሬ የመጨረሻው ክፍል ይለቀቅ የምትሉ ብቻ #Start የሚለውን ይጫኑ👇👇👇

በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተው የፍቅር ታሪክ ዛሬ የመጨረሻው ክፍል ይለቀቅ የምትሉ ብቻ #Start የሚለውን ይጫኑ 100 ሲገባ ይለቀቃል ወዲያው👇👇👇
በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተው የፍቅር ታሪክ ዛሬ የመጨረሻው ክፍል ይለቀቅ የምትሉ ብቻ #Start የሚለውን ይጫኑ 100 ሲገባ ይለቀቃል ወዲያው👇👇👇

14k subscribers yalew channel megzat mifelg bezih yanagregn @sami_fam @junior2127

በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተው የፍቅር ታሪክ ዛሬ የመጨረሻው ክፍል ይለቀቅ የምትሉ ብቻ #Start የሚለውን ይጫኑ👇👇👇
በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተው የፍቅር ታሪክ ዛሬ የመጨረሻው ክፍል ይለቀቅ የምትሉ ብቻ #Start የሚለውን ይጫኑ👇👇👇

  🎁〰〰〰እዉነተኛ ታሪክ〰〰〰🎁   የታሪኩ ርዕስ 😢 #ፍቅር_እንዲህ_ነዉ_ወይ??❓       🌀 #Part 3⃣2⃣ ✍ ፀሀፊ #አሚር_ሰይድ ............የደሀ ልጅ ፍቅር.............   ዱባይ ህይወት በጣም ከባድ ነው አብሶ ሳውዲጋር በጣም ልዩነት አለው ሳውዲ ለሚስኪኖች በጣም የሚመች አገር ነው የነፃ ምግብ ቤት ሁሉ ያለበት አገር ነው፡፡ ዱባይ ግን ህይወት ይከብዳል በቀን 10 ሰአት ያሰሩናል ደመወዝ በወር 1000 ይከፍሉናል የምትመገበዉ ምግብ ከራስህ ነው በጣም ከባዱ ደግሞ የምትሰራው ቆመህ ስለሆነ ኩላሊታቸው ከጥቅም ውጭ እየሆነ አገራቸው የሚመለሱ ሰወች አሉ.. አብሮህ እየሰራ እንደቀልድ መሬት ላይ ፌንት በልቶ የሚዘረርማ የተለመደ ነገር ነው በዚያ ላይ ዱባይ ቤት ኪራይ በጣም ውድ ነው ላንድ ክላስ ከ 1700-2000 ድርሃም ትከፍላለህ ሳውዲ ግን አንድ ክላስ 200-300 ነው በጣም ርካሽ ነው ታክሲውስ ብትል ሎኬሽን ስለሆነ ሳውዲ በ 10 ሪያል የምትሄደው ከመካ ጅዳ ከ 80-100 ኪሎ ሜትር ዱባይ ግን ከ 1000-700 ድርሃም ይወስዳል እኔም የተሻለ ቢገኝ ብየ ሰባቱንም እስቴት አዳረስኩት ፡፡ በነገራችን ላይ ዱባይ ሰባት መንግስት ያላት አገር ነች እኔ የምሰራው ቻርጃ የሚባለው ቦታ ላይ ነው ኢማራት የተባለችው ሰባቶቹ ባንድ ተጣምረው ነው ዋናው መንግስታቸው አቡዳቢ ያለው ነው  ፡፡      እናም የተሻለ ነገር የለም እስከ 2000 የሚከፈላቸውም የምግብ የቤት ወጭ ሲደመር ትርፉ ባዶ ነዉ፡፡ 10 አመት የኖሩት ሁሉ አዲስ ከመጣነው 100 ድርሃም አበድረኝ ይሉሃል ዱባይ ማምታታት በጣም ይበዛል ከወጭ ቀሪ 500 ለማይኖርህ ደሞዝ ሃበሻው ደላላ ሆኖ ከ 1000-3000 ብር ይቀበልሃል ፡፡ ስራ ለማስገባት መንጃ ፈቃድ ለማውጣት ፈልጌ ሳጠያይቅ ባጠቃላይ እስከ 15 ሺህ ድርሃም ይወስዳል ይሄን ድርሃም ኢትዮ ቢኖረኝ እዚህ ምን አለፋኝ ብቻ ዱባይ በጣም ለኑሮም ለስራም የሚከብድ አገር ነው    ሳውዲ ስትሄድ መንገዱ በጣም ያለፋሀል ከሞት ከተረፍክ ብሎልህ ሳዉዲ ከገባህ አገሩ ይመችሃል ዱባይ ደግሞ መንገዱ በፕሌን በሰላም ገብተህ ኑሮው ግን በጣም ይከብዳል ሳውዲ ህንጻወች ቀለም ቅብ ለምጀ ነበርና በቀን ቁርስ ምሳ ችለው 120 ሪያል ይከፍሉሃል overtime ደግሞ ሳውዲ በ ሰአት 60 ሪያል ነው ዱባይ ግን በወር 1000 ምግብ ከራስህ overtime በሰአት 10 ድርሃም በጣም ያስገርማል ፡፡ አብሶ ሳውዲ ኖረው የሚያውቁ ሰወች ዱባይ አትመቻቸውም ወይ ወደ አገር ይመለሳሉ አለበለዚያ ድንበር ስለሆኑ በዚያው ወደ ሳውዲ ይገባሉ  ፡፡ ዱባይ  ውሃው ፀጉርን ይመልጣል በተጨማሪም ኑሮዉ ጥርስንና የመንቀል ባህሪ አለዉ በአመታት የኖሩ ሰወች ሶስት አራት ጥርስ ያረግፋሉ፡፡      እኔ ሳውዲ ህገ ወጥ ሆኜ መኖር ስለማልፈልግ ያለኝ አማራጭ ወደ አገር መመለስ እና ትምህርቴን ከዲፕሎማ ወደ ድግሪ ማሳደግ ነበረና ወደ አገር ቤት ተመለስኩ ፡፡ አሁን ድግሪየን በማኔጅመን እየተማርኩ ልጨስ አንድ አመት ቀርቶኛል አልሃምዱሊላህ ቢያንስ ያለ አግባብ ያቃጠልኩትን ጊዜ እንዳይፀፀተኝ የሞራል ካሳ ይሆነኛል    የአሁኗ ሚስቴ በጣም ለእኔ ልዩ ነች፡፡  በብዙ ነገር ከጎኔ ነች፡፡ ...... ......  ለህይወቴ መፍትሄ የማታደርገው ነገር የላትም ድህነቴም አያሳስባትም በእኔ ደስተኛ እንደሆነች ሁሌ ትነግረኛለች.....አብሽር ከድሬ  ገንዘብ አላህ ካለው ይመጣል፡፡ አንተ እኮ  ገና 28 አመትህ ነው ብዙ ነገር ይጠብቅሃል እያለች ታፅናናኛለች፡፡ ሁሌ ከልቤ የማይጠፋ ንግግሯ ይታወሰኛል አላህ ካንተ አንተን የሚመሳስሉ ልጆች እንዲሰጠኝ ምኞቴ ነው የምትለኝ ቃላት ለኔ ልዩ ቦታ አለው አላህም ያሳካልን ዱዐየ ነው ፡፡     ብዙ ጓደኞች አሉኝ ሁሉም ለኔ ህይወት መስተካከል የሚመኙ... አብሶ ሰአዳን እንድረሳ የግላቸውን ምክር አበርክተውልኛል ከጥሩ ጓደኛ የሚጠበቅ ነገር አድርገውልኛል ኡስማን ማለት የአንድ ሳንቲም ገፅታ ነን ..እንዲህ ይለኛል...ከድር አፍቅረናቸው ከድተውን ከሚያሰቃዩን ወደውን አፍቅረውን የሚመጡ ለኛ የተሻሉ ናቸው፡፡ እስኪ እኛ የወደድናቸው ጎዱን እንጅ ምን ጠቀሙን ???ይለኛል _መሃመድ ጀማል ደግሞ አብሶ ከዚህ የሰአዳ አዝግ ፍቅር ጋር ተያይዞ የኢማኔን መንኪታኮት ያመጣብኝ ጣጣ የፀጉር እስታይሌን መቀያየር ያበሳጨዋልና አምርሮ ተቆጥቶ ይመክረኛል ዳአዋም ሲያደር አልቅሶ የሚያስለቅስ ልጅ ነው ፡፡ ------መሃመድ ሰኢድ ደግሞ እሱጋር ጅልም ሁን እብድ ከመከረህ ትድናለህ ትቀየራለህ አንዳንዴ ድካሜን ያስበውና ግን እኔ አላውቅህም ልበል ሌላ ከድር መሰልከኝ ይለኛል አንተን እኮ ያየን የለምንጅ ያላየነው የለም የሚል ምክር ይናገረኛል ፡፡አብሶ ሰአዳን ለሰከንድ እንዳስባት አይፈልግም እየደጋገመ ግን ረስተሀታል ይለኛል ፡፡ _ይማም ሀሰን ደግሞ ከትምህርት ቤት ጀምሮ ጓደኛ የነበርን ልጆች ነን ከዲፕሎማእስከድግሪ አሁንም አብረን እየተማርን ነው የተጨናነቀውን አምሮየን አብረን ዘና እያደረግን ችግራችንን እንረሳዋለን ፡፡ ይማም ማለት በአቅሙ ለህዝቡ የሚጠቅም ሰው ነው በችግርህ የትም ታገኝዋለህ   ....ሙሀመድ የሚባል በጣም የምወጀዉ ጓደኛየ ታሪኬን ያቃል....ሰአዳ የምረሳበትን ነገር እስኪ ንገረኝ ለመርሳት አልቻልኩም ብየ  አማከርኩት ........እሱም  ኢስላማዊ መፅሀፍ አንብብ ብሎ ጠቆመኝ..... ፍቅር በኢስላም የሚል መፅሀፍ  እንዳነበዉ ነገረኝ......ሙሀመድ ባለትዳር ነዉ ያገባው ሳያፈቅር እንደ እኔ በፍቅር ሳይንገላታ በቤተሰብ ነው ሁለት ልጆች ወልዷል፡፡ ከኔ የተሻለ ህይወት አለው...ለካ በቤተሰብ የመጣ ማግባት ወላሂ እንዴት ጥሩ መፍትሄ ነዉ... እኔ አለሁ እንጂ ፍቅር ያሸንፋል ሲሉ ሰምቼ  ሰአዳን አገኛለሁ ብየ የተንገላታሁ.....      ጊዜ ሳልፈጅ  መፅሀፉን ገዛሁት ስገልጠው ላይመራንስ ወይንም ወህመል ሁብ ይላል በአማረኛው #የማይጨበጥ_ፍቅር እንደማለት ነው በባዶ ሲደክሙ መኖር  ማለት ነዉ፡፡    መፅሀፉን ተረጋግቼ አነበብኩት የእኔን ሙሉ ህይወት ታሪክ ስቃየን የጻፈው ነው የሚመስለው..ገረመኝ ...... #የመጨረሻዉ_ክፍል_ ነገ እንዲለቀቅ 5 ሰው ብቻ በፈቃደኝነት 🫵👇👇Start በሉት ከዛ ነገ ይለቀቃል #ይቀጥላል.... https://t.me/major/start?startapp=1753715732 ⚪️⚪️⚪️⚪️⚪️⚪️⚪️⚪️ https://t.me/major/start?startapp=1753715732

Binance Telegram ላይ የራሱን Mine app Launch አድርጎዋል ። ለመጀመር ➡️https://t.me/Binance_Moonbix_bot/start?startapp=ref_1753715732&star
Binance Telegram ላይ የራሱን Mine app Launch አድርጎዋል ። ለመጀመር ➡️https://t.me/Binance_Moonbix_bot/start?startapp=ref_1753715732&startApp=ref_1753715732

🎁〰〰〰እዉነተኛ ታሪክ〰〰〰🎁   የታሪኩ ርዕስ 😢 #ፍቅር_እንዲህ_ነዉ_ወይ??❓       🌀 #Part 3⃣1⃣ ✍ ፀሀፊ #አሚር_ሰይድ የደሀ ልጅ ፍቅር  ከአሁን ቡሀላ ብደዉይ ..... የባለተቤትሽ ስልኩን ወይም አድራሻዉን አፈላልጌ እነግርልሻለሁ.......አልኳት... ......ሰአዳም እሺ ብላ ጊዜ ሳፈጅ ስልኩን ዘጋችው >>>>>>> ሳላስበው ነበር ይህን ሃሳብ የተናገርኳት እንዴት እንደዚህ እንዳልኳት ይገርመኛል...ከኔ አፍ ነዉ የወጣዉ ወይስ ሌላ ተናገር የሚል ሀይል ያለ ይመስለኛል፡፡   .   ሰአዳ ይሄን ከተናገርኳት ቡሀላ በዚያው ቀረች..መደዋወል አቆምን እሷም አደዉል እኔም አልደዉልም.......   የሚገርም ነገር ነዉ በሒደት ጓደኞቼ ሲነግሩኝ.. አንዱ እንዲህ አለኝ አንተ ዉጭ ሁነህ የፍቅር ግንኙነት እንዳላችሁ አላቅም  እኔ ሰአዳን ለማግባት ተስማምተን  ከከተማ ወጣ ብለን ከሰአዳ ጋር እየተዝናኑ የተነሱትን ፎቶ አሳየኝ፡፡ ፎቷቸዉን ስመለከት ገረመኝ...ደግሞ በሌላ ቀን ይባስ ብሎ አንዱ ሰይድ የሚባል ልጅ ስለፍቅር እንደሚያወሩና ከከተማ ወጣ እያሉ እየተገናኙ በፕሮግራም እንደሚያወሩ ነገረኝ፡፡     ያአላህ የኔ ጅልነት የሰአዳ አልታመን ባይነት አላህን ሳማርር የነበረው ሁሉ ከፊቴ መጣብኝ ምን ይባላል አስተግፊሩሏህ ብቻ ነው ፡፡ አቤት የኔ ሰው ማመን ስንቱን ወንድ ስለትዳር አውርታዋለች የኔን ጓደኛ ሳይቀር ልታገባው ጨርሳ እንደነበር ወላሂ ነገሩኝ፡፡     ሌሎች ሴቶች ቃላቸውን በፅናት ሲጠብቁ አባቶቻቸው እንገላለን ብለው ሴቶቹ አብረህ ግደለን ብለው ወላጆቻቸውን አሸንፈው ያሳመኑት ሁሉ ታሪካቸው ፊቴ ላይ መጣብኝ፡፡ ከዚያን ቀን በኋላ በሰአዳ ቤተሰቦች ላይ ያለኝ መጥፎ አመለካከት ተስተካከለ ጥፋተኛዋ ራሷ ሰአዳ መሆኗ ገባኝ ፡፡እኔን የምታስታውሰኝ ትዝ የምላት የማትፈልጋቸው ሰወች ሲጠይቋት ለመከላከል የምወደዉ ከድር አለኝ እያለች፡፡ የምትፈልጋቸው ብር ያለዉ ሰዉ ሲመጡ እሽ ፈቃደኛ ነኝ የምትል አይነት ሰው እንደሆነች ገባኝ፡፡ በጣም የሚገርመኝ እንደምትወደኝ የምታስመስለው ነገር እንባ ለማምጣት ስትሞክር እኔም አምኜ መሸወዴ ነገሩ ደግ የሆንኩ የራሴ ሞኝነት ነው፡፡ ከዚያ .እኔም በግል ዲፕሎማ ትምህርት ጀመርኩ ሶስት አመት ጨርሸ  በLevel 4 ተመረኩኝ፡፡       የሰአዳ ፍቅር ብዙ መዘዝ አምጥቶብኛል ስራ ጠልነት..የምግብ ፍላጎት መቀነስ ...የሰውነት ድርቀት  .....ከሰወች ጋር ተቃራኒ መሆን ....ገንዘብ ማባከን ሆነ ስራየ ...>>የሚገርመኝ እንደዚህ ተናግሪያት የሷን መጥፎ ጎን ሰምቼ ለራሱ ልረሳት አልቻልኩም.....ስራ መስራት አልቻልኩም   ሌላ ሴት ለማግባት የሰአዳ ፍቅር አልወጣልኝ አለ .......የሰአዳን ነገር  ለኔ የዱንያ የሞት ሞት ሆነብኝ፡፡        ........በሰአዳ የተነሳ ማንንም ሴት ማመን መቅረብ እፈራለሁ ሁሉም ሴቶች እንደ ሰአዳ ከዳተኛ ናቸዉ እያልኩ ሴት ሳስብ ሰአዳ ትዝ ትለኛለች....ለሴት ያለኝ አመለካከት ወረደ........ጨካኝ ሁን ጨካኝ ሁን ይለኛል ግን እንዴት ልጨክን ሴት ማለት እህት ናት እኔም እህት አለኝ....ሴት ማለት እናት ናት የእኔ እናቴ ለኔ ብላ ከልጅነት ጀምራ የከፈለችዉ መስዋትነት አይኔ ላይ ድቅን ያላል፡፡ ሰአዳ ከዳችኝ ብየ የሌላ ሴት ሂወት ማበላሸት በእህቴ በእናቴ የማልፈቅደዉን የማልወደዉን ለሌሎች ሴቶች ማሸከም የለቅሷቸዉ ምክንያት መሆን አልፈልግም፡፡ ግን የሚገርመኝ ነገር አለ የሰዉ ልጅ ለሀላል እንደዚህ ይደክማል፡፡ ለፍቅርም ይሁን ገንዘብ ለማግኘትም ይሁን ..ለማግባት ለትዳር እንደዚህ መሰቃየት ግን ለዚና ለወንጀል ቀላል የሆነ ዘመን ሰአዳን በጊዜዉ ዚና እንስራ ብንል በጣም ቀላሌ ነበር ግን አላህ የከለከለኝን ለመከልከል ይሄ ሁሉ ግፍ አለፈብኝ ..በሀላል ለመክበር ብር ለማግኘት በጣም የከበደ ግን አምታቶ ሸዉዶ ለመክበር ቀላል የሆነበት ዘመን ያሳዝናል፡፡ ምን ይታወቃል ሰአዳ በዚህ አይነት ሌሎች ጋር የፈጠረችው ነገር ካለ በእኔ ማሳበቧ አልቀረም ከኔ አልፌ ላገባት ባሏ ሙሉነቷን(ቢክራነቿን) አግኝቶት ይሆን ብየ ማሰብ ሁሉ ጀመርኩ ..ወይንስ እኔው ጅሉ ከድር ላይ ከድር ነው የወሰደዉ ብላ አሳባብኝ ይሆን አላህ ከሪም ...ህይወት ይቀጥላልና    ከሀራም ከምወድቅ ብየ በቤተሰብ የመጣችልኝን ፀባይተኛ የሆነች ልጅ ተዋወኩኝ የምትኖረው ዱባይ ነው ...... ተስማምተን ቀለል ባለ ድግስ ሳይበዛ ኒካህ አደረግን ፡፡    አሁን የአገባሆት ሚስቴ አልሀምዱሊላህ ፀባዋ  ለኔ በጣም አሪፍ ነው ስሜቴን ትረዳኛለች ....ያለዉን ሒወቴን የተወሰነም ቢሆን ታቃለች.... እኔም የምፈልገዉ የዉስጤን የምትረዳኝ ነዉ...... አቤት አላህ ሲክስ ለኔ ህይወት መሳካት የሷ ውበት ረገፈ ለኔ የማትሆነው የላትም     አስቡት አሁን እድሚየ 28 ደርሻለሁ መረጋጋት መጨነቅ ማልቀስ ከጀመርኩ ሰአዳን ከአጣሁ ጀምሬ ስምንት አመታት አሳለፍኩኝ፡፡      አንዳንድ የሰፈር ሴቶች ያልበላቸዉን የሚያኩ ወሬ ወሬ የሚላቸዉ ይሄ ደግሞ አድቦ አግብቶ አይኖር ..አንዷ ጋር እረግቶ  ልጅ አይወልድምና ገና በማግቢያው አግብቶ ፈታ ቤተሰብ አሰዳቢ ይሉኛል ..     .....ግን የኔን ስቃይ ምክንያት የሚያቀዉ እኔ እና አንድ አላህ ነን...ለሰዉ ወሬ አልጨነቅም ..ግን የአሁን ሰዉ ወሬ ከሚያወራ ቀርቦ ቢረዳ ወይም የሰዉ እንደዚህ መሆን ለሱ አይጠቅመዉ አይጎዳዉ ለምን በሰዉ ሒወት ወሬ ያላምጣሉ??? የአሁን ሰዉ ስራ ከሚሰራ ወሬ ቢያላምጥ ይቀለዋል፡፡ እኔ ግን ለእንደዚህ አይነት ወሬ አልጨነቅም የኔ ጭንቀቴ ሰአዳን እንዴት አድርጌ ልርሳት??? አሁን ያገባኋት ሚስቴ ለኔ ልዩ ነች ጸባዩዋ ታማኝነቷ  አሳቢነቷ በምንም ቃላት ልግለፅላችሁ አልችልም ከገንዘቧ ጀምሮ በሁሉም ነገር ለኔ ያልሆነችው ነገር የላትም ..እኔም የደስታ ቀን እየመጣልኝ እንደሆን ይሰማኛል      ትምህርቴን ስጨርስ ለምን አላዝናናህም አለችኝ?   እንዴት አልኳት? ? የቪዚት ቪዛ ልላክልህና ዱባይ መጥተህ ዘና በል አለችኝ እሽ አልኳት ዲፕሎማ ስይዝ ዱባይ ከተዝናናሁ ድግሪ ብይዝማ አትጠይቁኝ ለሶስት ወር ዱባይ ሄድኩኝ ከሚስቴ ጋር ተገናኝን ፡፡ዛሬ ሌላ መዝናኛ ቦታ ነገ የአለም አንደኛዉ ህንፃ ቡርጅ ከሊፋ ሂጃለሁ፡፡ ኧረ ምኑን ላውራው እልፍ ቢሉት ሌላ ይገኛል ደጋ ሚስኪኑ ሞቱን ይመኛል እንደተባለው ያን ሁሉ ጭንቀት አስረሳችኝ ሁለት ወር ሙሉ ዘና ስል ቆየሁ    መቸም ደሃ ሆኖ ልዝናና ብቻ ማለት ራስን መሸወድ እንዳይሆን ለምን ስራ አልሞክርም ብየ ስራ ማፈላለግ ጀመርኩ ስራ ለመግባት ደላላወቹ ከ አንድ ሺህ እስከ ሶስት ሺህ ድርሃም ይጠይቃሉ እንደምንም የሆነ የልብስ ካምፓኒ ስራ አግኝቸ  ቻርጃ የሚባለው ቦታ ስራ ገባሁ ስራው በጣም ይከብዳል ግን የጉብኝት ቪዛው እስከሚቀየር ነው አቅማችሁን ለማየት ነው አሉን እንደምንም ብቃቴን አስመሰከርኩና የቪዚት ቪዛውን ወደ ሰራተኛ ቪዛ( ኢቃማ) ተቀየረልኝ ዱባይስ ምን ትመስላለችበቀጣዩ እናየዋለን part 3⃣2⃣ ይ....ቀ.....ጥ.......ላ........ል

እንኳን ደስ አላቹ ደስ አለን ለቴሌግራም ተጠቃሚዎች በሙሉ 🎊🎊🎊🎊🎊 #MAJOR በዶላር ጭማሪ ምክንያት በአለም ላይ ተቀባይነቱ እጀግ በጣም እየጨመረ ነው። #Major በቀጣይ ሳምንት ወደ to
እንኳን ደስ አላቹ ደስ አለን ለቴሌግራም ተጠቃሚዎች በሙሉ 🎊🎊🎊🎊🎊 #MAJOR በዶላር ጭማሪ ምክንያት በአለም ላይ ተቀባይነቱ እጀግ በጣም እየጨመረ ነው። #Major በቀጣይ ሳምንት ወደ token convert እንደሚደረግ አሳወቀዋል ፤ Focus አድርጋችሁ ስሩ ያልጀመራችሁ፦👇👇👇 https://t.me/major/start?startapp=1753715732 https://t.me/major/start?startapp=1753715732

🎁〰〰〰እዉነተኛ ታሪክ〰〰〰🎁   የታሪኩ ርዕስ 😢 #ፍቅር_እንዲህ_ነዉ_ወይ??❓       🌀 #Part 3⃣0⃣ ✍ ፀሀፊ #አሚር_ሰይድ ............የደሀ ልጅ ፍቅር............. ስልኩን ሳነሳዉ ሁሌም በልቤ ያለች አግብታ ትዝታዋ ያለቀቀኝ ሰአዳ ናት የደወለችዉ ....... የማላቀዉ ደስታ ከየት እንደመጣ አላቅም በጣም ደስ አለኝ ....ከድሬ እንዴት ነህ ጠፋህ እኮ አለችኝ........ አለሁ አንቺ ነሽ የጠፋሽዉ አልኳት..... .....እኔማ አለሁ ከሳዉዲ እንደመጣህ ትደዉልልኛለህ ብየ ጠብቄህ ነበር .. ???ብላ ወቀሰችኝ...... እሷ ብሎ ወቃሽ እኔ ስንት ሆኜ ተሳቅይቼ ያልወቀስኩትን እሷ እንደቀልድ ትወቅሰኛለች..በሆዴ እየገረመኝ...እንደዚህ አልኳት >>>>>>>>>>  ለምን  ማረሚያ ቤት ታስሬ ብዙ ሰዉ የማቀዉ የማላቀዉ እየመጣ ሲጠይቀኝ አንቺ እኮ አልመጣሽም ብየ ወቀስኳት ...    ብዙ ነገር አወራን... የሚገርም ነዉ እንደበፊቱ ከማግባቷ በፊት እንደምናወራዉ ዳግም ተግባብተን ያለፈዉን ረስተን  ማውራት ጀመርን ፡፡  ግን ሰአዳ ባለትዳር ነች፡፡ ግን የምናወራዉ ወሬ እሷ ትዳር ላይ ያለች አይመስልም..በጣም ወጣ ያለ ወሬ እናወራ ነበር...      የፍቅር ወሬ ሁሉ እናወራለን    በስልክ ማዉራታችንን ተያይዘንዋል  አንድ ቀን እንደዚህ አለችኝ.....ከድሬ እስኪ ዱአ አድርግ አላህ በመካከላችን የሆነ ነገር ፈጥሮ እንዲያገናኝን ከአላህ ተስፋ አንቁረጥ  ትለኛለች ......ሰአዳ ካገባችም ቡሀላ እንደ አዲስ በተስፋ በነፍስ ስጋየ ተጫወተችብኝ፡፡ ልብሱን ያልጣለ እብድ ሆንኩኝ ........... አንድ ቀን እንገናኝ እና እናዉራ  ብላ ደወለችልኝ ........እኔም ላስብበት አልኳት....  እሷን በአካል መገናኝት ፈልጊያለሁ ግን በአካል ብንገናኝ  ዝሙት ከመስራት እና   እስከዛሬ ያጣሁትን በበቀል ከመጨረስ ዉጭ ልላ የሚፈጠር ነገር እንደማይኖር እርግጠኛ ነኝ እሷ ባትስማማም እኔ ግን በሃይል እንደማደርገው ውስጤይ ይነግረኛል    ...ሰአዳን እንኳን ዚና ልንሰራ  አንድ ቀን ስሚያት አላዉቅም  ..በአይን ፍቅር ብቻ እሷን ላለማጣት ብየ ስንት በርሀ ተሰቃየሁኝ ምን ይደረጋል አላህ ያለዉ ሆነ፡፡          ጠዋት አስፓልት ዳር ቆሜ ከሩቁ እያለፈች ደወለችልኝ .......ስልኩን አነሳሁት እንዴት ነኝ አምሮብኛል???አለችኝ .......አዎ አምሮብሻል አልኳት ............ብታየኝ ያው ነኝ ምንም አልተቀየርኩ ዉበቴ እንዳለ ነዉ አለችኝ    ውስጤ ኧረ ተይእንጂ አልቀረብሽም ገና ድንግል ነኝ ባትይኝ ይላል ....ለአፌ ከአንገት በላይ ልክ ነሽ ውበት ጨምረሻል አልኳት       .... ድሮ ፊቷን የማብስላት ትውስታው እየታወሰኝ ....አሁንም ደግሜ በውስጤ ደግሞ ከዚህ በኋላ በኮስሞቲክስ ለሚጠበቅ ውበት እላለሁ ........ ከድሬ ስንገናኝ ብዙ የምነግርህ ነገር አለኝ አለችኝ .... እኔም እሽ ነገ እንገናኝ?? አልኳት .....እሺ  አለችኝ ..........የምንገናኝበትን  ቦታ እኔ ነግርሻለህ አልኳት ....... እሺ አለች ስልኩን ዘጋነው ፡፡   እንደነገ ልንገናኝ ዛሬ ማታ መልሳ ደወለች፡፡ እንደ ደወለች ስልኩን አላነሳሁትም...  የምሰራዉ ስራ በጣም ቆጨኝ...በዚህ የማይጨበጥ ፍቅር ውስጥ ከጌታየ መስመር እየለቀኩ እንደሆነ ተሰማኝ ..... እንዴት ባለትዳር ሴት ጋር አወራለሁ ??? ብንገናኝስ ካላገባኋት ሸይጧንስ ቢያሳስተኝ ???  አላህ ይቅር ይበለኝ አልኩኝ      ከዛም  ልፈትናት እና የልቧን ትርታ ለማዳመጥ ፈልጌ እኔ መልሼ ደወልኩላት  ...    ሰላምታ ከተለዋወጥን ቡሀላ ..... ሰአዳ ትዳር እንዴት ነው ተመችቶሻል ??? አልኳት ........ አሪፍ ነው ተመችቶኛል...አለችኝ ሳይኮ የምታወራውን መከታተል ይዣለሁ ......... በጣም ግራ ገባኝ ቀጠልኩና ሰአዲ ባልሽን ትወጅዋለሽ ???አልኳት ............. እሷም አዎ እወደዋለሁ  አለችኝ ሳቅ እያለች ..... እኔንስ ትወጅኛለሽ አትወጂኝም  ???አልኳት መቼም አንዴ ደፋር ሁኜ የለ .....ሰአዳም መልስ ሳመልስ የፈተና ምርጫ ላይ መልስ የለም የተባለ ይመስል ..  ዝም አለች ...መልሽልኝ እንጂ እያልኩ ብጠይቃት ..ዝም አይነቅዝም የተባለ ይመስል ብዙ ስታወራኝ የነበረችዉ ሰአዲ ዝም አለች፡፡    ____ ከዛም በመቀጠል እንደዚህ አልኳት ሰአዳ ግን ለምን ልጅ አትወልጅም ???  ...እሷም. ..ሞክረን ነበር ግን አልሆነም አንዴ ተበላሸብን ግን አሁንም እየሞከርኩ ነው አለችኝ    እና እኔን እየተጫወትሽብኝ ማለት ነዉ ?? አልኳት እንዴት አለችኝ  >>>ሰአዳ እስኪ አንድ ነገር ንገሪኝ.በጣም አሳፋሪ ነሽ እኔስ በአንቺ የተሰቃየሁት የሆንኩትን እኔ እና አላህ ነን የምናቀዉ.....ባል አለሽ ግን ???በባልሽ ላይ እኔን ታወሪያለሽ ?? ባልሽን ባፈሪ የሚያይሽን የፈጠረሽን አላህን አፈሪም ??? >>>>>>>እኔ ከድር ቆልፈሽና አሽገሽ  ያስቀመጥሽኝ እቃ አይደለሁም ስትፈልጊ ከፍተሽ የምትጠቀሚብኝ<<<<<<<<<<< .አልኳት  .....መልስ አልመለሰችም ፀጥ አለች ቀጠልኩ...  አንች ማለት ጥቅም አባራሪ ለራስሽ ምቾት ብቻ የምትኖሪ የጥቅም ሰው ነሽ ......እኔም ሞቅ ሞቅ ተናገር ተናገር የሚል የሚገፋፋ ነገር እንዳለ ይሰማኛል፡፡ ከዛም ጨመርኩላት >>>>>ከአሁን ቡሀላ እኔን ከፈለግሽ ከባልሽ ጣጣሽን ጨርሰሽ ነይ፡፡  ካልሆነ ግን አትደውይልኝ በራሴ ላይ የደረሰው የሀሳብ የሞራል ውድቀት ሳያንሰኝ ሌላ አትጨምሪልኝ፡፡ አሁን ለራሱ ያለሁበትን ሁኔታ መሸከም አልቻልኩም፡፡     እራሴን ላገግም እያልኩ..ሒወቴን ገና አሀዱ ብየ እጀምራለሁ ስል ከአንቺ ሀሳብ ለመገላገል ሒወት እንደ ህፃን ልጅ ዳዴ እየሄድኩ ነገ ከነገ ወዲያ እነሳለሁ እያልኩ ...የራሴ ሒወት ልጀምር ስል ደዉለሽ የማይሆን ተስፋ እየሰጠሽ ዳግም ሁለተኛ ሒወቴን እያበላሸሽብኝ ነዉ ፡፡....    አንቺን ላለማጣት ብየ በስደት ስንት በርሀ አቋርጬ በሒወት እና በሞት መካከል ሁኜ ፈተና በዝቶብኝ..ዛሬ ወይ ነገ ኢዝሯኤል ሒወቴን እስከሚወስደዉ ተመኝቼ ከአሉት በታች ከሞቱ በላይ ሁኜ ያንን ሁሉ ፍቅር ያሸንፋል ብየ የተጎዳሁ አሁን ድረስ ጠባሳዉ ያለቀቀኝ የፍቅር ጅል ነኝ፡፡  ለፍቅር መስዋት ይከፈላል ለእንዳንች አይነቱ ግን ያሳፍራል ይሄን የነገርኩሽንም መልሰሽ ትረሽዋለሽ አንች ማለት እንዲህ ነሽ።     እኔ እኮ ነገን አስቤ ጥሩ ቀን ይመጣል ብየ በአንቺ ፍቅር የተጎዳሁ የፍቅር ማዕበል የወሰደኝ....ወስዶ ያልመለሰኝ ከድር ነኝ አንች ግን እንደሞኝ ነው የምታስቢኝ የወደደ ሰው መልሶ የሚጠላ አይመስላቹም ከንግዲ በኋላ  ግን  የህይወቴ መጥፎ ሰው አንች ነሽ ፡፡መቼም ቢሆንከአንቺ ሌላ መጥፎ ሰዉ አያገኘኝም ............ከአሁን ቡሀላ ብትደዉይ ..... ለባልተቤትሽ ስልኩን ፈልጌ ወይም አድራሻዉን አፈላልጌ ለባልሽ እነግርልሻለሁ.......አልኳት ከድር ለባሏ ይናገር ይሆን ?? በሚቀጥለዉ ክፍል እናያዋለን #Part 3⃣1⃣ ይ........ቀ........ .......ጥ.......ላ........ል 👇👇Start👇👇 https://t.me/major/start?startapp=1753715732 https://t.me/major/start?startapp=1753715732

🧕:እሱ ደግሞ የኮምቦልቻ ልጅ ነዉ ስሙም ጀማል ይባላል...  ሀርቡ ሹፌር ነዉ የታሰረዉ ሰዉ በመኪና ገጭቶ ነዉ .........በወሬ በወሬ ሀርቡ ቆንጆ ልጅ አለች ለትዳር ጠይቂያት እንደ አንተ ስሙ ከድር የሆነ  ልጅ እንደምትወድ ነግራኝ እምቢ አለችኝ  እኔም እስኪ ይሄን ታሪክ ንገረኝ ጀማል እኔን ሊሆን ይችላል አልኩት .....,አንተ ሳዉዲ ነበርክ እንዴ ??? አለኝ ...........አዎ ሳዉዲ ነበርኩ መጥቼ ነዉ አልኩት ... .......ሰአዳ የምትባል ልጅ ታውቃለህ ???አለኝ . .........አወን አልኩት አንተን ነበር ማለት ነዉ እወደዋለሁ እጠብቀዋለሁ ስትል የነበረችዉ??? አለኝ .......እኔም እንዴት ???አልኩት ........ሹፌር ነኝ ሀርቡ ስደርስ እነ ሰአዳ ካፌ አላቸው.... እሷም ካሸሪ ናት ሳንቲም ትቀበላለች፡፡  ቆንጅየ እናም ስነስርአት ያላት ልጅ ነበረች ፡፡ እናም ባገባት የትዳር አጋሬ ብትሆን ብየ ተመኘሁ ወደድኳት ... ቀርብ ብየ ሰአዳን ሳወራት የምትወደው ልጅ  ከድር እንደሚባል እና ከ የማገባዉ እሱን ነዉ እጠብቀዋለሁ ሳውዲ እንደሚኖር ነግራኛለች አለኝ     ....... ይህን ሲነግረኝ በጣም ገረመኝ  በወሬ ወሬ እሱም ሰአዳን ተመኝቶ እምቢ እንዳለችዉ ነገረኝ....ወይ መገጣጠም አጃኢብ ነዉ   ፡.ብቻ የማረሚያ ቤት ህይወት ቢያወሩት አያልቅም እናም ብዙ ሳንቆይ ወደ ደሴ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የላክነው ይግባኝ ተወስኖ መጣ ......... ውሳኔውም ይሄ ወንጀል አመት ማሳሰር ስለማይችል በ 600 ብር ቅጣት ይቀየር እነሱም ይፈቱ ይላል፡፡       በጣም ደስ አለን በአጠቃላይ እስር ከጀመርንበት ቀን ጀምሮ ተቆጥሮ 40 ቀን ቆይተን ከእስር ቤት እኔ እና ሙሀመድ ወጣን፡፡ ከስር ቤት ስወጣ ከታሳሪዎቹ ጋር በጣም ተግባብተን ስለነበር ለመለያየት እስኪያቅተን ተሰናበትኳቸዉ፡፡     የሀርቡ ህዝብ የተወሰነ በእኔ ያለው ግምት ተስተካከለ ፡፡        ከእስር ቤት እንደወጣሁ  ስልኬ ጠራ... አዲስ ስልክ ቁጥር ነበር ........ስልኬን አንስቼ ሀሎዉ ስል የሰማሁትን ድመፅ ማመን አቃተኝ... እዉነት እዉነት አልመሰለኝም ልቤ ቀጥ አለ... ሁሌም በልቤ ያለች አግብታ ትዝታዋ ያለቀቀኝ ሰአዳ ናት የደወለችዉ ....... የማላቀዉ ደስታ ከየት እንደመጣ አላቅም በጣም ደስ አለኝ ....ከድሬ እንዴት ነህ ጠፋህ እኮ አለችኝ የምናፍቃት የምወዳት ሰአዲ........ ሰአዳ ለምን ይሆን የደወለችዉ አዲስ ነገር በሰአዳ እና ከድሬ መካከል ይኖር ይሆን? ...ሰአዳ ለምን ደወለች?????? በሚቀጥለዉ ክፍል እናያለን Part3⃣0⃣ ይ..........ቀ............ .......ጥ............ላ................ል  ......... 👇👇Start👇👇 https://t.me/major/start?startapp=1753715732 https://t.me/major/start?startapp=1753715732

🎁〰〰〰እዉነተኛ ታሪክ〰〰〰🎁   የታሪኩ ርዕስ 😢 #ፍቅር_እንዲህ_ነዉ_ወይ??❓       🌀 #Part 2⃣9⃣ ✍ ፀሀፊ #አሚር_ሰይድ በIslamic university channal ............የደሀ ልጅ ፍቅር.............   ሳናስበው  ማረሚያ ቤት ገባን፡፡ ሰዉ ባልሰራዉ ወንጀል በፍትህ ችግር እስር ቤት ተወረወርን..... እስር ቤት የፍርደኛ አንድ አልጋና ፍራሽ ቤተሰብ አመጣልን  .....   እኛ የታሰርነዉ በሀይማኖት ኬዝ ስለሆነ ወህኒ ቤት ያሉት ታሳሪዎች ያከብሩናል ይወዱናል፡፡ በሃይማኖት የታሰረ እንደአሸባሪ ነው የሚታየው         አሸባሪ እና ከ 4 ሰው በላይ የገደለ እና እንደ ኤድስ በሽተኛ ያለ ሰው የሚታሰረው በአንድ ክፍል ውስጥ ነው በጣም ያስፈራል...ወደ እዛ ማታሰሪያ ክፍል ዉስጥ አስገቡን .....     የምናድረዉ በአንድ ላይ ነዉ....ፍራሻችንን  አነጠፍን..... አዲስ የገባንበት ክፍል ያሉት ታሳሪዎች.....አብሽሩ እንኳን እናተ እኛም አላህ ባልፈቀደዉ  ወንጀል ሰርተን ገብተን ለምደነዋል፡፡ ......... ለሀይማኖትማ ብትሞቱስ ምነው??? ከናተ ጋር ሆነን በሀይማኖታችን ታስረን በነበር እያሉ ያፅናኑናል......... እናም እዚያ ክፍል ያለው ሁሉ ስለገባበት ስለታሰረበት ምክንያት ለአዲስ ገቢዎች ይነግራሉ....... ........ ከኔ ጎን ያለው ሰው እንዲህ አለኝ>>>>>>>> እኔ እዚህ ወህኒ ቤት የገባሁት ሁለት ሰው ገድየ ብዙዎቹን አቁስየ ነው አለኝ <<<<እኔም በሆዴ ሰዉ መግደል ብርቅ አይደለም... እኔም ባስጨናቂው ባህር እና ጭር ባለ በርሀ ስደት ሳዉዲ ለመግባት ስጓዝ ተርፌ የሞቱ ሬሳወች አፅሞች በብዛት  እያየሁ የተጓዝኩ ልጅ ነኝ እላለሁ ለብቻየ፡፡  አንዱ ደግሞ ቀጠል አደረገና ....እኔ ደግሞ የኤድስ በሽተኛ ነኝ እያለ ይስቃል ........ ብድግ አልኩኝ ከተኛሁበት እንደምንም ሌሎቹ አረጋጉኝ፡፡  ግን በሂደት ያ ሰው ጋር ተግባባን      ከተወሰኑ ቀናቶች በኋላ የይግባኝ ደብዳቤ  ለከፍተኛ ፍርድ ቤት ደሴ ከተማ  ፅፈን ላክን፡፡ ...... ውሳኔውን ለመከታተል ከደሴ ከተማ እስከሚመጣ የተወሰኑ ቀናቶችን መጠበቅ ጀመርን፡፡መሃመድ አሚን በሃይለኛ ዱአ ያደርጋል ሌሊት ተኝቸ በመሀል ስባንን አይተኛም ዱአ ያደርጋል ይሰግዳል፡፡ አረፍ በል ተኛ ስለው ይሄ የሚታረፍበት ቦታ አይደለም አላህ በቶሎ ከዚህ ያውጣት እያለ ያለቅሳል ....... ማረሚያ ቤት ያስገርማል ራሱን የቻለ ሌላ ኢትዮጵያ  ነው የሚመስለው ስርዐቱ ከአንድ ለአንድ ጀምሮ እስከ አንድ ለአምስት ተደራጅቷል፡፡ ....... ጧት 12 ሰአት ከሆነ መተኛት አትችልም እዚያው ጊቢው ውስጥ ስራ ፍጠር ትባላለህ ሽመና የሚሰራ ቆሎ የሚሽጥ ሁሉ አለ፡፡  ታሳሪው ለምግብ ማብሰያ እንጨት መፍለጥ ግድ ነዉ... ይህን ማድረግ የማንችለው ብር እየከፈልን እናስፈልጣለን፡፡ ለአንድ እንጨት ዋጋው 2 ብር ነው እናም ከብዙ ሰወች ጋር እንተዋወቃለን     ከማረሳው የእስር ቤት ገጠመኝ  እዚያው ታራሚ ሁነዉ አትክልት የሚሸጡ አሉ ከሸዋሮቢት ቤተ ክርስቲያን የታሰሩ ሰው ናቸው ......አትክልት ቲማቲም ሽንኩርት ቃሪያ ይሸጣሉ ወጥ ስንሰራ መክተፊያም አብሮ አላቸው፡፡ እናም ለሙስሊም ሰው መስጠት አይፈልጉም በጣም ነው ዘና ነው የሚያደርጉኝ ......ለምን አትሰጡንም??? ስላቸው ........እናተ ስጋ አታጡም ይሉኛል፡፡ እንደምንም አባብየ ለምኜ ይሰጡኛል እከትፋለሁ     አንድ ቀን በምን ታስራችሁ ነው??? አልኳቸው  እነሱም የሃይማኖት ኬዝ ነው በናንተ በሙስሊሙ ብቻ አይደለም በእኛም በሀይማኖት ችግር አለ አሉኝ .......እንዴት ???አልኳቸው ........,መንግስት ትእዛዝ አምጥቶ ልክ እንደ ሀይማኖት አድርጋችሁ አስተምሩ ይለናል እናንተ ሙስሊሞች እምቢ ትላላችሁ ያስሯችሆል...... እኛ ደግሞ እሺ ብለን ስለምንቀበል አይነኩንም ......... ይሄው እኔም አልቀበልም ብየ አስረውኝ ነው አለኝ ፡፡ በጣም ይገርማል ፡፡     ሌላው ማረሚያ ቤት እያለሁ መቼም የማረሳቸዉ  በጣም የሚያስቁ ሽማግሌ ሰዉየ ነበሩ እድሜያቸው 80-90 የሚገመት ሽማግሌ ናቸዉ፡፡ በጣም ደስተኛና ጠንካራ ናቸው መሳቅ መጫወት ይወዳሉ ...... አንድ ቀን ፋዘር በምን ታስራችሁ ነው ???አልኳቸው .... ....አንድ ሚስት ነበረችኝ እርሷ ስትደክምብኝ ሌላ ሁለተኛ ድንግል ሴት አገባሁ፡፡ የመጀመሪያይቱ ሚስቴ ሁለተኛ አገባብኝ ብላ ከሰሰችኝ፡፡  ፍርድ ቤት ቁሜ ዳኛዋ ሴት ነበረች ለምን ሁለተኛ አገባህ ??? ብላ ዳኛዋ ጠየከችኝ..... ....እኔም ለዳኛዉ  እንዲህ አልኳት >>>>>>>እስኪ እሱ የምፅፊበት  እስክርቢቶ ካለቀ መፃፉን ካቆመ ምን ታደርጊዋለሽ ???አልኳት .......ዳኛዋም  እቀይረዋለሁ አለችኝ ........ እኔም እንደ አለቀዉ እስክርቢቶ የመጀመሪያዋ ሚስቴ ደከመች ሌላ አገባሁ አልኳት 😆😆አሉኝ የሚያስቁ ሰዉየ ......ከዚያስ??? አልኳቸዉ ...........ዳኛይቱ  በጣም ስቃ 6 አመት ፈረደችብኝ አሉኝ ፡፡ ይህንን ሲያወሩኝ ዘና ብለው ነው ጥርስ ጨርሰዋል አሳሳቃቸው ሳይቀር ያስቃል ፡፡     አንዴ ሌሊት ተኝተን  ይሄዉ ሰዉየ የደረጀ ደገፋዉን ሙዚቃን ያዜማሉ.....        የፍቅርሽን ተራራ ወጣሁት ተክዠ         በእጀ ምናምኑን በልቤ አንችን ይዠ፡፡ ይላሉ .....እኔም ተው አባት ሙዚቃ ሀራም ነው ስላቸው .. .......እሳቸዉም በሀገሬ ወጉ ምርቃን መሰል ስድብ ምናገባህ ዘረበዳ ውሀብያ ይሉኛል፡፡ ደግሞ አንዳንዴ ሲዘፍኑ        አየሁት አየሁት ሁሉንም አየሁት        አየሁት አየሁት ሁሉንም አየሁት        እንደ ሁለተኛ ሚስቴ የሚስማማኝ         የለም ያገኘሁት ሁሉንም አየሁት እያሉ ይዘፍኑና ብቻቸዉን ይስቃሉ ብቻ በጣም ነው ዘና የሚያደርጉኝ      ማታ ማታ ፊልም ለማየት ታሳሪው ሁሉ ሳንቲም ሲያዋጣ ቆመው ይሰበስባሉ....እኔም  ለምን አንቱ ትልቅ አይደለሁ እንዴ??? ፊልም ለምን ታያለሁ ???ስላቸው .....ለወህኒ ቤት ሀላፊዉ ይሄ አሸባሪ ነው ለፊልም አላዋጣም እያለ ነው ብለው ጮከው ይነግሩትና ከት ብለው በድዳቸው ይስቃሉ፡፡     እኔን የሚያስቀኝ አሳሳቃቸው ነው ፡፡ በባዶ ጥርሳቸዉ ሲስቁ እኔን ያስቁኛል..ይሄን ሽምግልና ይዘዉ ሁለተኛ ማግባታቸዉ በጣም ነዉ የሚገርመኝ፡፡   ብቻ የማረሚያ ቤት ታሪክ ቢወራ አያልቅም ..እኚህን ሽማግሌ ግን ከሁሉም አልረሳቸውም .........አብሶ ታማኝ እስረኛ አድርገዋቸው የማረሚያ ቤቱን እርሻና ከብቶች እንዲጠብቁ ሌላ ቦታ ወስደዋቸው የአገራቸው ሰው መሞቱን ሰምተው አገሬ ሄጀ ካልቀበርኩ ብለው ጋቢና ቀርቃሃቸውን ይዘው መናሃሪያ ሲደርሱ ፖሊሶች ይዘው የመለሷቸውን ነገር ሲያወሩ ያስቃሉ ለምን ሄድኩ ሲሏቸው ወዳጀንማ ሳልቀብር አልቀመጥም ያደረጉትን ያድርጉኝ ብየ ነው😆 ይሉና ይስቃሉ...      መቸም የማወራው ስለፍቅር መሆን ነበረበት ግን በእስርቤት  ያጋጠመኝ የህይወት ውጣ ውረድ ልንገራችሁ ብየ ነዉ..የሀርቡ ሰዉ ከድር አህባሽ ነዉ ሰላይ ነዉ ሲሉኝ የነበሩት ሁሉ እየመጡ ይጠይቁኛል...... አማንህ ወነጀልንህ ስምህን ያለስራህ አጠፋነዉ  አዉፍ በለን አሉኝ ......እኔም አብሽሩ አዉፍ ብያለሁ እላቸዋለሁ እየመጡ አጫዉተዉኝ ይሄዳሉ.....የሚዘይረኝ ሰዉ የሚጠይቀኝ በጣም ብዙ ነበር.....እኔ በባህሪያ ከማንም ጋር እግባባለሁ ፡፡    ደግሞ ከሌላ ልጅ ጋር ተዋወኩኝ የሀርቡ ልጅ መሆኔን አብሬ ስሜን ነገርኩት👇