የጋዜጠኛው ማጮለቂያ
Kanalga Telegram’da o‘tish
465
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-27 kun
-930 kun
Postlar arxiv
465
ለጥንቃቄ ተጠቀሙበት‼
ዘመኑ የቴክኖሎጅ ሆነና ኪስ አውላቂዎች ስርቆቱን እና ማጭበርበሩን ማህበራዊ ሚዲያ ላይ አድርጓል።ይህ ደግሞ አለማቀፍ ልምድ ነው።
በመሆኑም ከሰሞኑ ደግሞ ብዙ እህቶች እና ወንድሞች WhatsApp ፣ Telegram እና Facebook አካውንቶቻችን ከቅጥጥር ውጭ ሆነዋል ፣ ተቀማን [Hacker ] በማለት ሲጠይቁኝ እንድሁም ሚድያ ላይ ሲያገሩ ተመልክቻለሁ።
ወገኖቸ ዘራፊው ስራው ቅርፁን ከቴክኖሎጅ ጋር እያዘመነ የኛን ስንፍና እና ስግብግብነት እየተጠቀመ መዝረፍ ሆኗል።
ስለሆነም አሁን ላይ ስለችግሩ ሳይሆን ችግሩ እንዳይገጥመን ቅድመ መከላከል እና የግንዛቤ ማስጨበጫ መረጃወችን የማጋራችሁ ይሆናል።
👉 ምንም አይነት Link ከምታቁትም ይሁን ከማታቁት ግለሰብም ሆነ ተቋም በማህበራዊ ሚድያ ሲላክላችሁ በቀጥታ በፍፁም እንዳትከፍቱት። እጅግ ጠቃሚ ነው ብላችሁ ካሰባችሁ ሊንኩን ኮፒ አድርጋችሁ Mozilla or Chrome ላይ ክፈቱት። በዚህም ሂደት Username and password ከጠየቃችሁ ምንም እንዳታስገቡ።
👉 በስህተት ከነካችሁት እና ከከፈተባችሁ በፍፁም Username and password እንዳታስገቡ።
👉 በ WhatsApp and Telegram ከተቋሞቻቸው Official የሚላክላችሁን Confirmation Code ለሌላ ሰው even ለምታቁት ቤተሰብም ቢሆን እንዳትልኩ።
❎ ይህ ችግር በሆነ አጋጣሚ አካውንታችን ሊጠለፍ ፣ ሊወሰድ ስለሚችል
1-Recovery Email or ስልክ ቁጥር ሊኖራችሁ ይገባል። ከሌላችሁ ዛሬ ነገ ሳትሉ በመጠየቅ አስተካክሉ።
2- አብዝሀኛው ሰው የራሱን Password ረስቶታል save ባደረገው ነው Default የሚጠቀመው እናም Password ቢበዛ በየ 6ወር ቀያይሩ።
አካውንታችን ቢጠለፍ የሚያጋጥመን ቀውስ 👇
1- WhatsApp እና ቴሌግራም አካውንታችሁን በመውሰድ ግላዊ መረጃችሁን በመበርበር አስፈላጊ መረጃዎቻችሁን በመውሰድ[ለምሳሌ እርቃን ምስል] ሊሆን ይችላል ወይም ትላልቅ መረጃን በመያዝ (Black Mail) በትልቅ ገንዘብ ይደራደሯችኋል።
2- በእናንተ ስም ሌሎችን በማታለል ብድር በማጭበርበር ይበደሩበታል።
3- የወንጀል ተግባር ይፈፅሙበታል
ስለዚህ ይህን አይነት በዋትሳፕ እና በቴሌግራም የሚላኩላችሁን link በፍፁም አትክፈቱ። የላከላችሁ ግለሰብ ምንም የምታውቁት ቢሆንም ራሱ።
⚠️ የሚላኩላችሁ:-👇
👉 "የአላሙዲ የልደት በአል ".......
👉"የፕረዝዳንት ታየ ልደት"......
👉 "ከዚህ ቪድዮ ያለችው የአንተ እናት ትመስላለች" የሚሉ ናቸው። ስለሆነም ራስዎን ከዚህ መሰል መጭበርበር ይጠብቁ‼
(ኢንጅነር አብዱ ሙሃመድ)
465
3ቱም ተይዘዋል‼
በመቐለ ከተማ፣ ዓዲሽምድሑን በተባለ ሰፈር፣ ከአርባምንጭ የመጣ አንድ የሙዝ ነጋዴን አግተው በባጃጅ ለማምለጥ የሞከሩ 3 ግለሰቦች በህዝብ እና በፀጥታ አካላት ትብብር ተይዘዋል።
465
ሕገ-ወጥ ተግባራት ቁጥጥርን ይመለከታል
መንግስት የሠራተኛውን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል ከመስከረም 2018 ዓ.ም ጀምሮ የደሞዝ ማሻሻያ ለማድረግ ያስተላለፈው ውሳኔ የሠራተኛውን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል የሚያግዝ በጎ ተግባርና አዎንታዊ እርምጃ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ የደሞዝ ማሻሻያው ከሀገራችን ጠቅላላ ህዝብ ቁጥር ከ2% የማይበልጠውን የመንግስት ሠራተኛ የኑሮ ሁኔታ በማሻሻል መንግስት ለህብረተሰቡ የሚሰጠው አገልግሎት ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆን ታስቦ የተደረገ መሆኑ ይታወቃል ከዚህ በፊት ካለው ልምድ ለመገንዘብ እንደሚቻለው አብዛኛው የንግዱ ማህበረሰብ ሕግና ስርዓትን ጠብቆ የሚሠራ መሆኑ የሚያስመሰግን ቢሆንም የተወሰኑ በአፍቅሮተ-ነዋይ የታወሩ ነጋዴዎች ለሠራተኛው ኑሮ ማሻሻያ የሚደረገውን የደሞዝ ጭማሪ ምክንያት በማድረግ ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት መሯሯጥ ተስተውለዋል
እንደዚህ አይነት ኢ-ሞራላዊ ያልተገባ ጥቅም ማግኛ ሩጫ ከንግድ ሥነ-ምግባርና ሞራል አኳያ ሲታይ አሳፋሪ ተግባር መሆኑ ታውቆ በአዋጅ ቁጥር 980/2008 እና 813 /2006 እንዲሁም በወንጀል ሕግ 1996 ተላልፎ ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ በመድረግ በማንኛውም የንግድ እቃ እና አገልግሎት ግብይት ላይ ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ ወይም ሰው ሰራሽ እጥረት ለመፍጠር ምርት የሚሰውሩ እና አላግባብ የሚያከማቹ ሕገ-ወጥ ነጋዴዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ከወዲሁ ለማሳሰብ እንወዳለን፡፡
በተጨማሪም በየደረጃው የሚገኝ የንግድ መዋቅር ከሚመለከታቸው የፍትህ እና ፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት የተጠናከረ የገበያ ማረጋጋት፣ የክትትልና ቁጥጥር ሥራ በማጠናከር በአጥፊዎች ላይ አስተማሪ እርምጃ እየተወሰደ የግብይት ሂደቱ በተረጋጋ ሁኔታ እንዲቀጥል እንዲደረግ የኢፌድሪ ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አሳውቋል።
465
የደመወዝ ጭማሪ‼️
መንግስት ከመስከረም 2018 ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ ወሰነ‼️
ከሚወሰዱ ሌሎች ማሻሻያዎች በተጨማሪ፣ ከመስከረም 2018 ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወስኗል፡፡
በዚህ ማሻሻያ፦
1. ዝቅተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 4760 ወደ ብር 6,ዐዐዐ እንዲያድግ ይደረጋል፡፡
2. ከፍተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 21,492 ወደ ብር 39,000 እንዲያድግ ይደረጋል፡፡
3. የዲግሪ ተመራቂ መነሻ ደመወዝ ከብር 6,940 ወደ ብር 11, 500 ይሻሻላል።
4. ከሲቪል ሰርቪስ ውጭ በተለያዩ ዘርፎች የተሠማሩ የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝም ማሻሻያ ይደረግበታል፡፡
465
የሁለቱ ታላላቅ የአፍሪካ አየር መንገዶች የ18 ዓመታት ንጽጽር
ልዩነቱ አስደናቂ ነው!!
2006
___
* የተጓዦች ብዛት
ኬንያ ኤርዌይስ ~ 2.6 ሚሊዮን
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ~ 2.1 ሚሊዮን
* የሚበሩባቸው ቦታዎች ብዛት
ኬንያ ኤርዌይስ ~ 42
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ~ 49
* የአውሮፕላኖች ብዛት
ኬንያ ኤርዌይስ ~ 21
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ~ 33
* የሰራተኞች ብዛት
ኬንያ ኤርዌይስ ~ 4,154
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ~ 4,837
2024
_____
* የተጓዦች ብዛት
ኬንያ ኤርዌይስ ~ 5.2 ሚሊዮን
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ~ 17.1 ሚሊዮን
* የሚበሩባቸው ቦታዎች ብዛት
ኬንያ ኤርዌይስ ~ 44
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ~ 135
* የአውሮፕላኖች ብዛት
ኬንያ ኤርዌይስ ~ 34
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ~ 145
* የሰራተኞች ብዛት
ኬንያ ኤርዌይስ ~ 4,154
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ~ 24,758
ምንጭ: ዘ አፍሪካን ታይምስ
465
አስገራሚ መረጃ‼️
በሆድዋ ውስጥ ሌላ ፅንስ የያዘች ህጻን ተወለደች‼️
በህንድ ሃገር በሆድዋ ውስጥ ሌላ ጽንስ የያዘች ህጻን መወለዷ እየተዘገበ ነው።
በሆድዋ ውስጥ ሌላ ሕፃን ይዛ ተወለደች የሚለው ያልተለመደ ክስተት እውነት መሆኑን የጤና ባለሙያዎች አስታውቀዋል።
ይህ ክስተት fetus in fetu በመባል የሚታወቅ ሲሆን፣ በአለም ላይ እጅግ በጣም አልፎ አልፎ የሚከሰት ነው ተብሏል።
በህንድ ሃገር ግን ከሌሎች ሃገራቶች በበለጠ እየተከሰተ ነው ተብሏል።
ይህ ሁኔታ አንድ ፅንስ ገና በማህፀን ውስጥ ሳለ በሌላው መንታ ፅንስ ሆድ ውስጥ ሲፈጠር ሊከሰት የሚችል ነው ተብሏል።
በህክምና ታሪክ ውስጥ እስካሁን የተመዘገቡት የዚህ አይነት ክስተቶች ከ200 እንደማይበልጡም ተጠቁሟል።
ይህንን ዘገባ ያሰራጨው ዘ ታይምስ ኦፍ ኢንዲያ ሲሆን የህክምና ባለሙያዎች ይህ ሁኔታ እውነት መሆኑን እና ከዚህ በፊትም ተመዝግቦ እንደነበር አስገንዝበዋል ነው የተባለው።
ይህ አይነቱ ክስተት ከተከሰተ በኋላ በቀዶ ጥገና አማካኝነት በሆድ ውስጥ ያለው ፅንስ እንዲወጣ እንደሚደረግ ተመላክቷል።
465
በ72 ሰዓታት ውስጥ ውጡ‼️
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የሶማሊያ ወታደሮች ስትራቴጂክ ጠቀሜታ ካላት የሶማሊያ ከተማ ለቀው እንዲወጡ ትዕዛዝ ሰጡ።
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ጦር አዛዦች የሶማሊያ ፌደራል መከላከያ ሠራዊት በጌዶ ክልል በሌድ ሀዎ ከተማ ለቀው እንዳወጡ ትዕዛዝ መስጠታቸው ተሰምቷል።
የኢትዮጵያ ሠራዊት አመራሮች ቁልፍ ወታደራዊ ጠቀሜታ ካላት ኢትዮጵያን ከኬኒያ ከምትዋሰነው በደቡባዊ ሶማሊያ ከምትገኘው በሌድ ሀዎ ከተማ በ72 ሰዓት ውስጥ የሶማሊያ ፌደራል ኃይሎች ለቀው እንዲወጡ ትዕዛዝ መስጡትን ከሶማሊያ ምንጮች ተሰምቷል።
በኢትዮጵያ በኩል በከተማዋ የግብጽ ወታደሮች ለመስፈር እየመጢ ናቸው የሚል ሰበብ መቅረቡን ምንጭች ጨምረው ገልጸዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ዛሬ ጧት ከተማዋን ከፌደራል መንግሥት ጋር ግጭት ውስጥ የገባው የጁባ ላንድ አስተዳደር ከባድ መሳሪያዎችን በማስገባት በከተማዋ ዙሪያ መስፈሩ ተገልጿል።
465
ልዩ መረጃ‼️
የሱዳን ጦር በሱዳን ዳርፉር በኒያላ አየር ማረፊያ ሲያርፍ የነበረ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ አይሮፕላን ላይ ጥቃት መሰንዘሩ ተሰማ።
የሱዳን ጦር የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች አውሮፕላን በዳርፉር ግዛት ስትራቴጅካዊቷ ኒያላ ከተማ ሲያርፍ ኢላማ አድርጓል ሲል የሱዳን ቴሌቪዥን ዘግቧል።
አውሮፕላኑ የኮሎምቢያ ቅጠረኛ ተዋጊዎችን ይዞ እንደነበር እና ሲያርፍ በትናንትናው ዕለት August 6/2025 በሱዳን ጦር ጥቃት እንደደረሰበት ዘገባው ጠቅሷል። በጥቃቱ ከ40 በላይ የኮሎምቢያ ቅጥረኛ ወታደሮች/Colombian mercenaries/ መሞታቸውን ዘገባው ጠቅሷል።
ኒያላ አየር ማረፊያ በጄኔራል ሀምዳን ደጋሎ በሚመራው የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር ቁጥጥር ስር ይገኛል።
የሱዳን ጦር አረብ ኢምሬትስ ለሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር ድጋፍ ታደርጋለች ብሎ ያምናል።
465
ጆርዲ ዛሬ ጠዋት ከሀገር ወጥታለች።
አፍሪካ ውስጥ የግብ ፣ረ ሰdoም እንቅስቃሴዎችን ለማስፋፋት የሚደረጉ ስራዎችን በሽፋን የሚመራው "FEMNET " የተሰኘው ድርጅት አግዟት ጆርዲን ከሀገር እንድትወጣ አድርጓታል።
ዛሬ ሶሻል ሚዲያ ላይ በስፋት የተሰራጩት ይህ እና መሰል ፎቶዎችም ጆርዲ በ FEMNET ጋባዥነት #African girls & young women's festival ላይ እንድትሳተፍ በተደረገችበት ስልጠና ላይ ከተዋወቀቻት አፍሪካዊት ፌሚኒስት ጋር እንደሆነ አረጋግጫለሁ።
ይህ ተቋም ጆርዲ የተለያዩ ወጣቶችን እንድትመለምል እና አላማቸውን እንድታሳካ በኢትዮጵያ ወኪሉ አድርጎ የመረጣት እንደሆነና ጥሩ በጀት ተመድቦላትም ስትሰራ እንደነበር ሰምቻለሁ።
465
የቀይ ባህር ዋና ጠቀሜታዎች መካከል !
አለም ያፋጠጠው ቀይ ባህር 4 ዋና ዋና አለም አቀፋዊ ጠቀሜታዎች አሉት እነሱም:-
🔴 የአለም ንግድ 20% ዋንኛ መተላለፊያ አብሯ ጎዳና በመሆኑ ማንም የሰፈር ጉልበተኛ ይሄንን ንግድና ጉዞ እንዲያስተጓጉል ስለሚፈለግ!
🔴 ከእስያ ወደ አውሮፓ የሚደረግ የመርከቦች ጉዞን በማሳጠሩ!
(ከቻይና አውሮፓ በቀይ ባህር ጉዞ 25 ቀናት ብቻ የሚወስድ ሲሆን ይሄው ጉዞ በደቡብ አፍሪካ ቢሆን ተጨማሪ 10 ቀናት ይጨምራል)
🔴 የአለም የነዳጅ ጫኝ መርከቦች መተላለፊያና የትልልቅ ነዳጅ አምራች አገሮች የሚጋሩት ባህር መሆኑ::
🔴 አውሮፓን ከመካከለኛው ምስራቅ እና ከእስያ የሚያገናኘው የኢንተርኔት ፋይበር ኦብቲክስ በቀይ ባህር ውስጥ የተቀበረ በመሆኑ::
465
አስቸኳይ ስብሰባ ተጠርቷል
ገዥው ብልጽግና ፓርቲ፣ የሥራ አስፈጻሚ እና የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላቱን በሙሉ "ወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች" ላይ ለመምከር ለአስቸኳይ ስብሰባ ወደ አዲስ አበባ መጥራቱ ታወቀ።
በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ጉዳይ ላይ፣ በፀጥታው እንዲሁም በቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት እንደሚደረግ እና ቀጣይ አቅጣጫዎች እንደሚቀመጡ ተሰምቷል።
ስብሰባው በነገው ዕለት ይካሄዳል ተብሏል።
465
በቡሬ አቅጣጫ ኤርትራ ከባድ ጦሯን እያስጠጋች ነው ተባለ
ከፍተኛ ቁጥር ያለው የኤርትራ ጦርና ከባድ መሳሪያ ወደ ኢትዮጵያ ድንበር እየተጠጋ ነው ተባለ፡፡
ሻቢያን ከስልጣን ለማስወገድ የሚንቀሳቀሰው የኤርትራ አፋር ብሔራዊ ጉባኤ፣ ስለ ኤርትራ ጦር አደገኛ እንቅስቃሴ አዲስ መረጃን አጋርቷል፡፡
ኤርትራ የጦር ሠራዊቷን ወደ ኢትዮጵያ ድንበር እያስጠጋች ነው ብሏል፤ ጉባኤው፡፡
የጉባኤው የሥራ አስፈጻሚ አባልና ቃል ዐቀባይ አሊ መሐመድ ዑመር ለጀርመን ድምጽ እንደገለጹጽ፤ ‹‹የኤርትራ መንግስት ድንበር ላይ በከባድ መሣሪያ የታገዘ ሠራዊት አቅርቧል፤ ቡሬ አካባቢ። ስለዚህ አሁንም ወደ ጦርነት የመግባትና ኢትዮጵያን ሰላም የመንሳት ፍላጎቱ እንደቀጠለ ነው›› ብለዋል፡፡
465
+2
ሙሉ ቤተሰብ ላይ ቦንብ 😭
በራያ አላማጣ አቶ ሰለሞን የተባለ ግለሰብን ከለሊቱ 7:00 ላይ ታጣቂዎች አፍነው ለመውሰድ ወደ መኖሪያ ቤቱ በማቅናት አቶ ሰለሞን ቤታቸውን ለመክፈት ፈቃደኛ ባለመሆናቸውና ተኩስ መተኮስ መጀመራቸውን ተከትሎ ታጣቂዎቹ በመላው ቤተሰቡ ላይ ቦንብ በመወርወር አንድ የ17 አመት ሴት ልጁ እና የ 7 አመት ወንድ ልጁ ህይወታቸው ሲያልፍ አቶ ሰለሞን እና ባለቤቱ ወደ መቀሌ ሪፈር ተልከዋል።
ነፍስ ይማር።
465
ጦርነት
ታይላንድ እና ካምቦዲያ ከፍተኛ የተባለ የተኩስ ልውውጥ እያደረጉ ይገኛሉ።
በሁለቱ ሀገራት ድንበር ላይ ተኩሱ ዛሬ የቀጠለ ሲሆን እስካሁን ከ15 በላይ ሰዎች መሞታቸውን ተዘግቧል።
ሁለቱ ሀገራት ተኩስ እንዲያቆሙ የተለያዩ ሀገራት ጥሪ እያቀረቡ ይገኛሉ።
ካምቦዲያ ሆስፒታሎች እና የህዝብ መገልገያ ተቋማትን መምታቷ ታይላንድን የካምቦዲያ ጦር በወሰን አካባቢ በታይላንድ ተይዞብኝ የቆየውን ግዛት መልሼ በእጄ አስገብቻለሁ ብሏል።
465
በኤርትራ ላይ አስቸኳይ እርምጃ እንዲወሰድ ተጠየቀ‼️
የኤርትራ መንግሥት በአፋር ህዝብ ላይ የሚፈፅመው ርህራሄ የለሽ ጥቃት አለም አቀፉ ማህበረሰብ እንዲያስቆም የቀይባህር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ጠየቀ።
የቀይ ባህር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት የኤርትራ መንግስት በዳንካሊያ ክልል በአፋር ህዝብ ላይ እያደረሰ ያለውን መንግስታዊ የሽብር ዘመቻ እንዲከላከል ለአለምአቀፉ ማህበረሰብ አስቸኳይ ጥሪ አቅርቧል።
በአቶ ኢሳያስ አፈወርቂ ፈላጭ ቆራጭ አገዛዝ ኤርትራ ወታደራዊ የጦር ሰራዊት ሆናለች-በጭቆና፣ በስደት እና በወንጀል የተጠመቀ አምባገነን ስርዓት “የአለም አቀፍ ህግጋትና የሞራል ሳይንስን የጣሳ ነው ብሏል።
ከ1993 ዓ.ም ጀምሮ በኤርትራ የሚኖሩ የአፋር ህዝቦች ላይ ስልታዊ፣ የተቀናጀ እና የዘር ማጥፋት ፖሊሲ -ይፋዊ በሆነ መልኩ ዘርንና ባህልና የማጥፋት አደጋ ተጋርጦባቸዋል ብሏል።
የኢሳይያስ መንግሥት:-
🎯በአፋር ሰላማዊ ዜጎች ላይ ግድያ እንዲፈፀም ስፖንሰር አድርጓል።
🎯በግዳጅ መሰወር፣ የጅምላ እስራት እና ለረጅም ጊዜ በማይታወቅ ቦታ እስራት መፈፀም።
🎯ለሀገር አቀፍ አገልግሎት በሚል በግዳጅ ወደ ወታደራዊ ካምፕ መውሰድ።
🎯ሆን ተብሎ በቀይ ባህር አካባቢ የሚገኙ የአፋር ክልል እስትራቴጂካዊ ግዛቶችን ህዝብ እንዳይኖርባቸው ለማራቆት በርካታ ሰዎችን አፈናቅሏል።
🎯ማሰቃየት፣ አስገድዶ መድፈር እና ሌሎች ኢሰብአዊ ድርጊቶች ፈፅሟል ብሏል።
ፓርቲው ሰኔ 4 ቀን 2025 RSADO በአፍሪካ ቻርተር አንቀፅ 55 ስር ለአፍሪካ የሰብአዊ እና ህዝቦች መብት ኮሚሽን (ACHPR) ይህን አስመልክቶ ደብዳቤ መፃፉን እና ምላሽ እየጠበቀ መሆኑን ገልጿል።
የኤርትራ መንግሥት በአፋር ህዝብ ላይ እየፈፀመ ላለው ወንጀል አለምአቀፉ ማህበረሰብ ነገ ሳይሆን ዛሬ፣ቀጣይ አመት ሳይሆን በዚህ አመት በአስቸኳይ በኤርትራ መንግሥት ላይ ወታደራዊ ማዕቀብን ጨምሮ ሌሎች እርምጃዎች እንዲወስዱ በአስቸኳይ ጥሪ አቅርቧል።
465
ፀድቋል
ብዙ ሲያከራክር የቆየው አዲሱ የፌደራል ገቢ ግብር አዋጅ በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ፀደቀ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌደራል ገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል በቀረበ ረቂቅ አዋጅ ላይ ተወያይቶ አጸደቀ።
ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው ሁለተኛ አስቸኳይ ስብሰባ ላይ ነው በሁለት ተቃውሞ እና በአራት ድምፀ ታቅቦ የተሻሻውን አዋጅ ያጸደቀው።
ይህ አዋጅ ከሀምሌ 2017 ዓ.ም ጀምሮ በስራ ላይ የሚውል ይሆናል።
465
ኤርትራ
ኤርትራ ከአሰብ ወደብ 80 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው በአፋር ቡሬ የኢትዮጵያ ክፍል ከባድ መሳሪያ ዛሬ ማምሻውን መተኮሱ ተዘግቧል
465
ድብድብ አውሮፕላኑን እንዲያርፍ አስገደደ!
ከሜክሲኮ ካንኩን ከተማ ወደ ለንደን ሲበር የነበረ አውሮፕላን፣ ሁለት ተሳፋሪዎቹ ድብድብ መጀመራቸውን ተከትሎ፣በረራውን ወደ አሜሪካዋ ሜይን ግዛት አዙሮ ለማረፍ ተገደደ።
አውሮፕላኑ ባለፈው ማክሰኞ አቅጣጫውን ቀይሮ በአስቸኳይ በማረፉ በውስጡ የነበሩት 267 ተሳፋሪዎች በሙሉ ምሽቱን በሜይን ግዛት ባንጎር ከተማ ውስጥ እንዲያሳልፉ መገደዳቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።
አውሮፕላኑ ወደ የአሜሪካዋ የባህር ዳርቻ ግዛት በደረሰበት ጊዜ የበረራው ሰራተኞች እረፍት ሳያደርጉ እንዲሰሩ የሚፈቀድላቸው የስራ ሰዓት አልፎ ነበር። በዚህም ምክንያት አየር መንገዱ ሌሎች ተተኪ ሰራተኞችን ለበረራው ያስመጣ ሲሆን፤ በመጨረሻም አውሮፕላኑ በማግስቱ በረራውን ቀጥሏል።
ድብድብ የጀመሩት ሁለቱ ተሳፋሪዎች የወንጀል ክስ አልተመሰረተባቸውም። ይሁን እንጂ ሁለቱም በተለያዩ በረራዎች ወደ ትውልድ ሀገራቸው እንዲመለሱ መደረጉን ዘገባው ጠቁሟል፡፡
