Abu hatim Abduselam Aselefiy
ትክክለኛው እስላማዊ አስተምህሮ ከቁርአንና ከሐዲስ ከደጋግ ቀደምቶች አረዳድ ከታማኝ ዑለሞች ንግግር የሚሰራጭበት ቻናል ነው።
Ko'proq ko'rsatish- Kanalning o'sishi
- Post qamrovi
- ER - jalb qilish nisbati
Ma'lumot yuklanmoqda...
Ma'lumot yuklanmoqda...
እራስህን ሁል ጊዜ ለቁርኣንና ለሀዲስ ተጎታች አድርግ! በአንድ ነገር ላይ ከቁርኣንና ከሀዲስ ማስረጃ ሳታገኝ አቋም አትያዝ! ሁሌም ለሰዎች መልካምን ተመኝ! ለሀቅ እንጂ ለሰዎች ወጋኝ አትሁን
እራስህን ሁል ጊዜ ለቁርኣንና ለሀዲስ ተጎታች አድርግ! በአንድ ነገር ላይ ከቁርኣንና ከሀዲስ ማስረጃ ሳታገኝ አቋም አትያዝ! ሁሌም ለሰዎች መልካምን ተመኝ! ለሀቅ እንጂ ለሰዎች ወጋኝ አትሁን
ይህ ነገር አገልጋይ እንዳያሳጣቸው የፈሩት ግብፃዊያን ፊርዓው ዘንድ ሄደው አቤቱታ ሲያቀርቡ አንድ አመት የሚወለደው ተትቶ በሌላኛው አመት የሚወለደው እንዲታረድ አዘዘ። የአላህ ፍላጎት ሆነና ነብዩላሂ ሙሳ ወንድ ህፃናቶች በሚታረዱበት አመት ተወለዱ። የእስራኢላዊያን ህፃናት መወለድ የሚጠባበቁ ሰራዊቶች በመኖራቸው የነብዩላሂ ሙሳ እናት ጊዜዋ በመድረሱና አመቱ ወንድ ህፃናት የሚታረዱበት በመሆኑ ጭንቅ ውስጥ ገባች። የተፈራው አልቀረም ህፃኑ ተወለደ። እናት ምን ይዋጣት!!!?
↪️ አላህ ሁሉን ቻይ መሆኑን ሊያሳያት በሳጥን አድርገሽ ወደ ቀይ ባህር ወርውሪው የሚል መልእክት እንዲመጣላት አደረገ። ወረወረችውም። ወደ አላህም ፍፁም ተማፀነች። አላህም ልጇን እንደሚመልስላት ቃል ገባላት። ባህሩ ሳጥኑን ወደ ፊርዓውን ቤተመንግስት እየነዳ አደረሰው። የፊርዓው አገልጋይ ሴቶች ሳጥኑን አገኙት ሲከፍቱት የሚያምር ህፃን ነው!!!። ወደ ቤተመንግስት ተወሰደ። ኣሲያ የፊርዓው ባለቤት የአይናችን ማረፊያ ይሆናል ልጅ አድርገን እንያዘው አትግደለው አለችው ተቀበላት።
➲ ረሃብ ይዞት ሲያለቅስ የሚቀርብለት ጡት በሙሉ እንቢ አለ። ምናልባት የሚስማማው ጡት ከተገኘ ብለው ሴቶችን ሲፈለጉ እህታቸው ማንነቷን ደብቃ አንድ ህፃናት በሙሉ ጡቷን የሚጠቡላት ሴት ላመላክታችሁ ወይ ብላ ጠየቀች አው አሉ። እናታቸው ወደ ቤተመንግስት መጣች!!!። ሱብሃናላህ በፊርዓውን ቤተመንግስት በእሱ ተንከባካቢነት በእናታቸው ጡት እንዲያድጉ አላህ አደረገ። በወቅቱ እስራኤላዊያን በቂብጦች የመከራ ገፈት ይጎነጩ ነበር። አላህ በሙሐረም 10ኛ ቀን ፊርዓውንን ከነሰራዊቱ አጥፍቶ እሳቸውንና ህዝቦቻቸውን ነጃ አወጣ።
➽ የአላህ መልእክተኛ ነብዩ ሙሐመድ – ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም – ወደ መዲና ሲሄዱ አይሁዶች ይህን ቀን ሲፆሙ አገኙዋቸው። ለምንድነው የምትፆሙት ብለው ሲጠይቁዋቸው ይህ ቀንማ አላህ ፊርዓውን አጥፍቶ ሙሳን ያዳነበት ቀን ነው። ለዚህ ነው የምንፆመው አሉዋቸው። እሳቸውም ለሙሳማ እኔ ከናንተ የቀረብኩኝ ነኝ ብለው መፆም ጀመሩ ተከታዮቻቸውንም እንዲፆሙ አዘዙ። ያለውንም ምንዳ ሲናገሩ እንዲህ አሉ:–
"صِيَامُ يَوْمِ عَرَفَةَ أَحْتَسِبُ عَلَى اللَّهِ أَنْ يُكَفِّرَ السَّنَةَ الَّتِي قَبْلَهُ وَالسَّنَةَ الَّتِي بَعْدَهُ وَصِيَامُ يَوْمِ عَاشُورَاءَ أَحْتَسِبُ عَلَى اللَّهِ أَنْ يُكَفِّرَ السَّنَةَ الَّتِي قَبْلَهُ"
رواه مسلم ( 1162).
"የዓረፋ ቀንን መፆም ያለፈውንና የሚመጣውን አመት ወንጀል ያስምራል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ። የዓሹራእ ቀንን መፆም ደግሞ ያለፈውን አመት ወንጀል ያስምራል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ።"
♻️ አዩዶችን ለመኻለፍ አላህ ካቆየኝ የሚመጣውን አመት ዘጠነኛውን የሙሐረም ቀን እፆማለሁ ብለው ነበር። ከዚህ በመነሳት የሙሐረምን ዘጠነኛና አስረኛ ቀን መፆም ይወደዳል። አብዛኛዎች ፉቀሃዎች ዘጠነኛ አስረኛና አስራ አንደኛውን ቀን መፆም ሱና ነው ይላሉ። ነገር ግን ከመረጃ አንፃር ዘጠነኛና አስረኛው ነው። ይህ ካልተቻለ አስረኛና አስራ አንደኛውን በመፆም አይሁዶችን መኻለፍ ይቻላል።
አላህ ይወፍቀን።
ከተወሰነ ማስተካከያ ጋር በድጋሚ የተለቀቀ።
http://t.me/bahrutekaالسلام عليكم ورحمة الله وبركاته قناة رسمية لمحاضرات ودروس الأستاذ بحرو تكا (أبو عبيدة) الدعوة السلفية በአላህ ፈቃድ በዚህ ቻናል የአማርኛ ትምህርቶችን እንዲሁም አጫጭር የአረብኛና የአማርኛ ፁሁፎችን እንለቃለን ከዚህ ቻናል ውጪ ከሌላ ቦታ ተወስደው ለሚለቀቁ ኦዲዮዎች እውቅና አልሰጥም
https://telegram.me/bahrutekaየሙሳ (ዐለይሂ ሰላም) አጭር የሕይወት ታሪክ:(pdf)ሷሊሃ የሆነችዋ የፊርዐውን ሚስት ኣሲያህ (ረዲየላሁ ዐንሃ) አሳማሚ ቅጣትና አማሟቷ: ነቢ ሙሳ ❨ዐለይሂ ሰላም❩ ይዘው የመጡትን ጥሪ ሳታንገዳግድ ሙሉ በሙሉ ተቀበለች፣ወደ እስልምናም ሙሉ በሙሉ ገባች፣ እንደታዘዘችው አላህንም ተገዛች፣ባለቤቷ ግን ጨካኝ፣ አረመኔ፣ አምባገነን፣እብሪተኛ... እና በመሬት ላይ እየኮራ የሚሄድ ሰው ነበር። አምባገነኑ ፊርዐውን እሷ (ኣሲያ) እስልምናን መቀበሏን ካወቀ በኃላ አሳማሚ የሆነ ቅጣት ሲቀጣት የነበረ አረመኔ ሰው ነበር። የሱ ቅጣት እሷን ለሞት አበቃት። የገደላት አገዳደል አጅግ በጣም አስከፊና አስቀያሚ በሆነ ሁኔታ ነበር የገደላት፤ነገር ግን እሷ ከትክክለኛው አቋሟ «ፍንክች» አላለችም ነበር። አስከ መጨረሻ እስትንፋሷ ደረስ በእስልምናዋ ለይ ጸናች። ፊርዐዉን ኣሲያን ሲያሰቃያት እንዲህ ነበር ያደረጋት፡ በጠራራ ፀሃይ ሜዳ ላይ አውጥቷት ትከሻዋን፣እግሯን፣እጇን...በብረት ሚስማር ወጥሯት ትቷት ሄደ። በጠራራ ፀሃይ ወጥሯት ከሄደ በኃላ በዛችኑ ቅፅበት ኣሲያህ (ረዲየላሁ ዐንሃ) እንዲህ ነበር ያለችው፦«ጌታዬ ሆይ! አንተ ዘንድ በጀነት ውስጥ ለእኔ ቤትን ገንባልኝ፡፡ ከፊርዐውንና ከሥራውም አድነኝ፡፡ ከበደለኞቹ ሕዝቦችም አድነኝ» ይህንን ዱዓ ካደረገች በኃላ መላኢካዎች መጡ። በክንፋቸውም አጠለሏት (ክንፋቸውን ጥላ አደረጉላት) አላህ ጀነትን ከፈተላት!!!፣በጀነት የተገነባላትን ቤቷንም አሳያት። ረሡል (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፦ "ከሴቶች በኩል እነኝህ አራቶቹ ብቁ ናቸው፡ መርየም ቢንትዒምራን፣ኸዲጃህ ቢንት ኹወይሊድ፣ ፋጢማህ ቢንት ሙሐመድ እና ኣሲየህ የፊርዐውን ሚስት። (ከፒዲኤፉ) 📝 አዘጋጅ: ሸይኽ አቡ ኸዲጃ (ሀፊዘሁሏህ) 📝 ትርጉም: አቡ ሀፍሳህ https://t.me/semirEnglish
ትክክለኛው እስላማዊ አስተምህሮ ከቁርአንና ከሐዲስ ከደጋግ ቀደምቶች አረዳድ ከታማኝ ዑለሞች ንግግር የሚሰራጭበት ቻናል ነው።
የሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) አጭር የሕይወት ታሪክ:ክፍል-1 አል-ሙጀዲድ ሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) በሒጅራው ቀመር አቆጣጠር በ'1115 ኡነይዛ ከተሰኘች ከተማ ተወለዱ። ኡነይዛ የተሰኘችው ከተማ፣ ከሳዑዲ አረቢያ ዋና ከተማ ከሪያድ በስተ ሰሜን-ምእራብ 70 ኪሎሜትር ያክል እርቀት ላይ ትገኛለች። የሸይኹ ቤተሰቦች የተከበሩና ዑለማኦች ነበሩ። አባቱ ሸይኽ ዐብዱል-ወ'ሓብ ብን ሱለይማን (ረሂመሁላህ) ጥልቅ እውቀት እንዳላቸውና እንዲሁም አጅግ ትሁትና መልካም ሰው እንደነበሩ ይነገራል። የሙሐመድ ዐብዱል-ወ'ሓብ አባት እውቀትን የቀሰሙት፣ ከአባታቸው ከሸይኽ ሱለይማን ብን ዐሊይ እንደሆነ ታሪክ ይዘክራል። ይህ በንዲህ እንዳለ፣ሸይኽ ሱለይማን ብን ዐሊይ (ረሂመሁላህ) በጊዜው ከነበሩ ዑለማኦች፣ዋና ሊቀመንበርና ፈትዋ ሰጪ እንደሆኑ ታሪክ ያስረዳል። አል-ሙጀዲድ ሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) የመጀሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን የተማሩት ከአባታቸው ነው። ይህም የሆነው እዛው በትውልድ ስፍራቸው ላይ ነበር። ሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) ታንፀው ያደጉትም በአባታቸው ነበር። ሸይኹ ቁርኣንን የሃፈዙት ገና በለጋ እድሜያቸው ላይ ነበር። ይህም የሆነው 10 አመት ሆኗቸው ሳለ ነበር። ሸይኹ ተፍሲር፣ሐዲስ፣ፊቅህ...ተምረዋል። ይህ በንዲህ እንዳለ፣ ሸይኹ የሰለፎችን ኪታብ በብዛት እንደማያነቡ ይነገራል፣በተለይም የሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያና ብርቅዬ የሆነው የተማሪያቸው የኢብኑል ቀይምን ኪታቦች ማንበብ ያጓጓቸው እንደነበር የታሪክ መዛግብት ያስረዳሉ። ሸይኹ እድሜያቸው ለጉርምስና በደረሰ ጊዜ፣ከአምስቱ የኢስላም ማዕዘናት የሆነውን ሐጅን ለመፈፀም ወደ መካ አቀኑ፤ከዚያም መካ ከሚገኙ ዑለማኦች እውቀትን ቀሰሙ። ሸይኹ ከመካ ቆይታ በኃላ፣እውቀትን ለመቅሰም ወደ መዲና አቀኑ፤እዛው መዲና ጥልቅ እውቀት ያላቸው እንደነ፡ ሸይኽ ዐብዱሏህ ቢን ኢብራሂም ብን ሰዒድ ነጅዲ እና ሸይኽ ሙሐመድ ሐያት ሲንዲ የመሳሰሉ ከታላላቅ ሙሁሮች ጋር ለረጅም ጊዜ ተማሪ ሆነው አሳለፉ። ሸይኹ እውቀትን (ዒልም) ፍለጋ በመካና መዲና ላይ አላበቁም። ሸይኹ ለዒልም ከነበራቸው ከፍተኛ ጉጉትና ፍላጎት ፣መዲና ላይ ለረጅም ጊዜ ከተማሩ በኃላ፣ ወደ ኢራቅና በስራ ጉዞ አቀኑ። ይሁን እንጂ፣ በዚህን ጊዜ የነጅድ ሁኔታ በጣም አስቸጋሪ ነበር፤ማለትም የተለያዩ ሺርክያቶች፣ ኢስላማዊ ያልሆኑ ድርጊቶች ይፈፀሙ ነበር። ሙሉበሙሉ በሚባል ደረጃ ነጅድ በሺርክ ማዕበል ተጥለቅልቃ ነበር። መቃብሮች፣ ዛፎች፣ ድንጋዮች፣ዋሻዎች፣መጥፎ መንፈሶች፣ከአላህ ውጭ ይመለኩ ነበር። መሰረት የሌላቸው አፈታሪኮችና ትንበያዎች በጊዜው ተንሰራፍቶ ነበር። በጊዜው የነበሩ ዑለማእ ተብዮችም ስሜታቸውን በመከተል ህዝቡን ከትክክለኛው መስመር ኢንዲስት አደረጉት። ይህ በንዲህ እንዳለ፣ጠንቋዮችና ትንቢት ተናጋሪዎች በጊዜ በህብረተሰቡ ላይ ተፅኖ ፈጣሪ የሚባሉት እነሱ ነበሩ። እነኝህን አካለት፡ ማለትም ጠንቋዮችን፣ትንቢት ተናጋሪዎች፣አጋሪዎች...በጊዜው ደፍሮ ሚጋፈጣቸው ሰው አንነበረም። በተመሳሳይም ይህ ሁኔታ በመካ፣በመዲና እንዲሁም በየመን ላይ ይስተዋል ነበር። ሸይኹ ትልቅ የዳዕዋ ተልእኮና ዓላማ አንግበው ተነሱ። በርግጥ ለሸይኹ ትልቅ ፈተና ነበር። በርግጥም፣ ይህንን ተለዕኮ መፈፀም ከባድ ፈተና እንደሆነ ለሁሉም ግልፅ ነው። ሸይኹ በቁርጠኝነት ጥሪያቸውን አንግበው ተነሱ። ሰዎችን ወደ ተውሒድ ጥሪ አደረጉላቸው፤ ወደ ቁርኣንና ሱንናም ጥሪ አደረጉላቸው፤ በጊዜው የነበሩ ዑለሞችንም ወደ ቁርኣንና ወደ ሱንና እንዲመጡ አነሳሷቸው። ሸይኹ በዚህ ብቻ አላቆሙም፤ጭፍን ተከታይነትን አጥብቀው ተቃወሙ። ከጭፍን ተከታይነት ወጥተን ቁርኣንና ሱንናን እንከተል የሚል ጥሪም አቀረቡ። ሸይኹ ጥሪያቸው አጥብቀው ባለማቋረጥ ቀጠሉ፤ ሸይኹ ለተለያዩ በጊዜው ለነበሩ ዑለሞች ይህንን አስከፊ ሺርክ ለማጥፋት ከጎናቸው እንዲቆሙ ጥሪ አቀረቡ። ይህንን የሸይኹን ጥሪ አያሌ የሆኑ ዑለማኦች...ከመካ፣ከመዲና እንዲሁም ከየመን የሸይኹን ጥሪ በመቀበል ሸይኹንም በመደገፍ ከሸይኹ ጎን ተሰለፉ፤ ረዱትም ጭምር። ከፊሎች ደግሞ፣ ዳር በመያዝ ሸይኹን መተቸትና ማብጠልጠል ጀመሩ። ልብ ይበሉ! እንደዚህ የሚያደርጉት ዓለማዊ ጥቅም ፈላጊ ዑለማእ ተብየዎች ናቸው። በዚህ ብቻ አላበቃም ሌሎችን በሸይኹ ላይ በማነሳሳት ዳዕዋውን ለማኮላሸት መሞከራቸው የሚዘነጋ አይደለም። ሸይኹን የነዚህ ጥቅመኛ ዑለማእ ተብየዎች አመፅና ትችት ከዳዕዋው ዝንፍ አላደረጋቸውም፤በል እንዳውም ሸይኹ የተውሂድን ጥሪ ለማድረስ ወደተለያዩ ስፍራዎች አቀኑ። ለምሳሌ፡ "ዘቢር፣ አሕሳ፣ሁረይመለ..." ከዚያም ዑወይነህ ደረሱ። ዑወይነህ ከደረሱ በኃላ፣የገጠማቸው መልካም ነገር ነበር። በጊዜው የነበረው የዑወይነህ አስተዳደር፡ ዑስማን ብን ሐምድ ብን መ'ዕመር ይባላል። ይህ አስተዳደር ሸይኹን በደስታ ተቀበላቸው፤እንዲሁም ከሸይኹ ጎን እንደሆነና ሸይኹ ደዕዋቸውን ማስኬድ እንደሚችሉ አረጋገጣላቸው። ሸይኹም እራሳቸውን ይበልጥ ለተውሂድ ተልዕኮ አዘጋጁ። ኢንሻአላህ ይቀጥላል.... https://t.me/semirEnglish https://t.me/semirEnglish
የሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) አጭር የሕይወት ታሪክ:ክፍል-2 (የመጨረሻው ክፍል) ሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) የዑወናው አስተዳደር አቀባበል ካደረገላቸው በኃላ፣ሸይኹ በከፍተኛው ሞራልና ትግል ዳዕዋቸውን በቁርጠኝነት ቀጠሉ። ዑወይነህ ላይ ሲፈፀሙ የነበሩ አስቀያሚ ሽርኪያቶች ሸይኹ ሰበብ በማድረሳቸው በአላህ ፍቃድ ሊጠሩ ችለዋል። እዛው ዑወይነህ ከተማ ውስጥ ሸይኹ ከመሄዳቸው በፊት፣ መቃብሮች፣ዋሻዎች፣ዛፎች...በሙስሊም ተብዬዎች ይመለኩ ነበር፤ሆኖምግን በዑወይነህ አስተዳደር አሚር ዑስማን ቢን መ'ዕመር...ከሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) ጎን በመሰለፍ የተለያዩ የባዕድ አምልኮ ተግባራትን በአላህ ፍቃድ ሊያስወግዱ ችለዋል። ይህ ደግሞ የሆነው፣ዑወይነህ ከተማ ብቻ ሳይሆን ዙሪያውን ጭምር ነው። ይህ በንዲህ እንዳለ፣በዑወይነህ ከተማ ውስጥ የእስልምና ህግጋት ተግባራዊ መሆን ጀመሩ። ለአብነት ያክልም...አንዲት ባለትዳር ሆና ዝሙት የፈፀመች ሴት ኢስላማዊ ህግጋት በሷ ላይ ተግባራዊ አንዲሆን ሸይኹን መጥታ ጠይቃለች። ዝሙት የፈፀምችው ሴትዮዋ ኢስላማዊ ህግጋት በሷ ላይ ተግባራዊ ኢንዲሆን መጠየቋን ተያይዞ፣ ስለ ሁኔታዋ፣ማለትም ጤነኛ ነች ወይ? ተገዳ ነው ወይ? የሚሉ ምርመራዎች ከተካሄዱ በኃላ፣እንዲሁም ወንጀሉ ከተረጋገጠ በኃላ፣ ሸይኹ ተወግራ እንድትገደል አዘዙ። የሸይኹ ዝናና ጀብድ በተለያዩ ከተሞች እየተስፋፋና እየተሰራጨ መሄድ ጀመረ። ሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) "የዑወይነህ" ቆይታቸውን ካጠናቀቁ በኃላ፣ "ደርዒየህ" ወደ ተሰኘች ከተማ አቀኑ። ሸይኹ ወደ "ደርዒየህ" ማቅናታቸውን ከታወቀ በኃላ፣የአል-አህሳ አስተዳደርና እንዲሁም ብን ሱለይማን የሸይኹን ገናናነት እና ተፅኖ-ፈጣሪ መሆናቸውን ለመለየት በህዝብ መካከል ሆኖ ይከታተል ነበር። ሁኔታው አጅግ በጣም አስፈራው፤ምክንያቱም ስልጣኔ ይነጠቃል የሚል ስጋትም ጭምር አደረበት። ይህ ሱለይማን የተባለው ግለሰብ፣ለአሚር ዑስማን ስጋቱን በመግለፅ ሸይኹን እንዲገላቸው ጥያቄ አቀረበ፤ይሁንእንጂ አሚር ዑስማን የሱለይማንን ጥያቄ ለመቀበል ፍቃደኛ አንነበሩም። ሱለይማን የአሚር ዑስማንን አቋም ከተረዳ በኃላ ተሸበረ፣ተጨነቀ፣ምድር ሰፊ ከመሆኗም ጋር ጠበበችው....አሚር ዑስማን ሸይኹን ተቀበሏቸው፤ በግዛቱ የፈለጉበት ቦታ መንቀሳቀስ እንደሚችሉ አስረግጦ አሳውቋቸው። የደርዒየህ ነዋሪዎችና ህዝቦች የሸይኹን የተውሂድ ተልእኮ ተረዱ። የደርዒያው አስተዳዳሪ አሚር ሙሐመድ ብን ሰዑድ፣ ሸይኹ ወደ ግዛቱ ስለገቡ በእጅጉን ተደሰተ። አስተዳዳሪው ቀጥታ ሸይኹ የሚገኝበት ድረስ በመሄድ ጉብኝት አድርጓል። በሸይኹ የተውሒድ ጥሪም ተደስቷል። ከሸይኹም ጋር የሃሳብ ልውውጥ አድርጓል። አሚር ሙሐመድ ብን ሰዑድ ለሸይኹ ድጋፍ እንደሚያደርግላቸው ቃል ገባላቸው። ሸይኹም ለአሚሩ ዱዓ አደረጉለት። ሸይኹ ይህንን ወርቃማ የሆነውን አጋጣሚ በመጠቀም፣አያሌ የሆኑ ህዝቦችን ማስተማር ጀመሩ። የደርዒየህ እና አካባቢዋ በተውሂድ ተናወጠች፤የተውሂድ ሰንደቅዓላማ መውለብለብ ጀመረ... ምን ይሄ ብቻ የደርዒያው ዋና አስተዳዳሪ አሚር ሙሐመድ እራሱን እና ቤተሰቦቹን ይዞ እንደተማሪ ሆኖ በመቅረብ፣ ከህዝቡ ጋር በመታደም የሸይኹን ትምህርቶችን መከታተል ጀመረ። ይህ ዜና በተለያዩ አከባቢዎች ተሰራጨ። ዜናውን የሰሙ ሰዎችም ከበረከቱ ለመቋደስ፣እውቀት ለመቅሰም ወደ ደርዒየህ መሰደድ ጀመሩ። ደርዒየህ የተውሂድ ማዕከል ሆነች። ይህ በንዲህ እንዳለ፣የሸይኹ ጠላቶች በሸይኹ ላይ የተለያዩ ቅጥፈቶችን መንዛት ጀመሩ። ምን ይሄ ብቻ?! ጠንቋይ፣ ድግምተኛ፣ ሙናፊቅ (ዚንዲቅ)...በመሳሰሉ ቃላቶች በሸይኹ ላይ መንዛት ጀመሩ። በተለያዩ የውሸት ቅጥፈቶች ሸይኹን ለማሸማቀቅና ከዳዕዋው ለማሰናከል በሚክሩም፣ሙከራቸው ሳይሳካ ቀርቷል። ሸይኹ የተቺ ተቺዎች ሴራ ሳይበግራቸው ተልዕኮውን ቀጠሉ። በል እንዳውም ተቃራኒ ከሆኑ አካላቶች ጋር ጨዋነት በተሞላበት ስልት ተከራክረዋል። ከዚህም በተጨማሪ፣ከተለያዩ ከአረብ ደሴት (Arabian peninsula) የመጡ የተለያዩ ልዑካን ቡድኖችን ትክክለኛው የተውሒድ ጥሪ ካደረጉላቸው በኃላ፣ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ ህዝባቸውን ወደ ተውሒድ እንዲጠሩ አጥበቀው መክረዋል። ሸይኹ በዚህም ብቻ አላቆሙም ለአረብ ደሴት መሪዎችና ሊቃውንቶች ደብዳቤዎችነ ፃፉ። የደብዳቤው ዋና መልእክት ሽርክን እንዲሁም ኢስላም የማያውቀው ባዕድ የሆኑ አምልኮዎችን ህዝባቸውን እንዲታደጉ ነበር። ሸይኹ ደብዳቤዎችን የፃፉት ለነጅድ፣ ሪያድ፣ኸርጅ፣ ቀሲም፣ሀዬል፣ወሽም፣ ሱደይር፣አህሳ፣ መካ፣ መዲና፣ የመን...ለመሳሰሉት ሀገራቶች ፅፈው ነበር። ልብ ይበሉ! ደብዳቤው የተፃፈው በሀገሩ ለሚገኙ አስተዳደር እና ዑለማች ነው። ሸይኹ አሁንም በዚህ አላበቁም፤ከአረብ ደሴት ውጭ ለሆኑ ሀገራትም ደብዳቤዎችን ፅፈዋል፤ለምሳሌ፡ ለነ ሶሪያ፣ ኢራቅ፣ሕንድ...ለመሳሰሉት ሃገራት በደብዳቤ የዳዕዋ ጥሪ አቅርበዋል። ሸይኹ ቁርኣንና ሱንናን አብራርተዋል። ምስጋና ለአላህ የተገባ ይሁንና ዳዕዋቸው ግብ መቷል። የሸይኹን ዳዕዋ ከተቀበሉ ሀገራቶች መካከል፡ ሕንድ፣ኢንዶኔዥያ፣አፍጋኒስታን፣አፍሪካ፣ሞሮኮ፣ግብፅ፣ሶሪያ...የመሳሰሉ ሀገራቶች የሸይኹን ዳዕዋ በመቀበል ትልቅ ተፅዕኖ አድሮባቸዋል። ይህም ብቻ ሳይሆ ከሸይኹ ጎንም ጭምር ተሰልፈዋል። ሸይኹ በሒጅራው ቀመር አቆጣጢ ከ"1158" እስከ "1206" ባሉት ጊዜያት ውስጥ ትልቅ የሆነ ተግል በማድረጋቸው አመክንዮ፣ በነጅድ ሙሉበሙሉ በሚባል ደረጃ አላህ ሸይኹን ድል አጎናፀፋቸው። ሰዎች ዶሪህን፣ ቀብርን፣ እንጨትን፣ዛፍን...ማምለክ ተው። ጭፍን ተከታይነት ሚባል ነገር ጠፋ። ይህ ባህል ነው፣የአባቴ መንገድ ነው፣የአያቴ መንገድ ነው...ከማለት ሰዎች ተወገዱ። ጥርት ወዳለው እስልምና ገቡ። አላሁ አክበር ዲን እንደገና ሕያው ሆነ። ቁርኣንና ሱንና በሰዎች ላየ ተንፀባረቀ። በመልካም ማዘዝ ከመጥፎ መከልከል ተግባራዊ ስራ ሆኖ ቀጠለ፤ መስጂዶች ውስ ሰዎች ሞልተው መስገድ ጀመሩ። በሀገሪቷ ሰላምና መረጋጋት ሰፈነ። ገጠሬዎችም ከተሜዎች...በሰላም መኖር ጀመሩ። የተውሒድ ሰንደቅዓላማ ተውለበለበ። ከሸይኹ እወቀትን የቀሰሙ አካላቶች በመላው ዓረቢያ ደሴት የተውሒድ ተልዕኮን ይዘው ተሰሬጩ። ሸይኹ በሕይወት ካለፉ በኃላም ልጆቻቸው እና ተማሪዎቻቸው ዳዕዋውን በአላህ ፍቃድ ማስቀጠል ችለዋል። ከልጆቻቸው መካካል ዳዕዋውን ካስቀጠሉ እንደነ፡ ሸይኽ ኢማም ዐብዱሏህ ብን ሙሐመድ፣ ሸይኽ ሑሰይን ብን ሙሐመድ፣ ሸይኽ ዐሊይ ብን ሙሐመድ፣ሸይኽ ኢብራሂም ብን ሙሐመድ....ይገኙበታል። ከሸይኹ ከልጅ ልጆቻቸው መካከል ደግሞ፣ሸይኽ ዐብዱር-ረሕማን ብን ሐሰን፣ሸይኽ ዐሊይ ብን ሑሰይን፣ሸይኽ ሱለይማን ብን ዐብዱሏህ... ይገኙበታል። ከተማሪዎቻቸው መካከል ደግሞ፡ እንደነ ሸይኽ ሐምድ ብን ናሲር...የመሳሰሉ ይገኙበታል። ሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) ለዚህ ኡማ ትልቅ የሆነን አሻራ ጥለው አልፈዋል። ለዚህም ነው ሰዎች በሺርክና በተለያዩ ባዕድ በሆኑ አምልኮ ተጨማልቀው ሳለ፣ በአላህ ፍቃድ ሸይኹ ትግል አድርገው፣የአንበሳውን ድርሻ ተጫውተው ነው ከዚች ዓለም ያለፉት።
Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.