uz
Feedback
አንድነት ሃይል ነው

አንድነት ሃይል ነው

Kanalga Telegram’da o‘tish

እንኑር ለዲናችን አንድነት ነው ብርታት አችን ቁርዓን ነው መመሪያችን ወደፊት እንጂ አንበል ወደ ኋላ 😍🙏

Ko'proq ko'rsatish
6 610
Obunachilar
-1124 soatlar
-287 kunlar
-20630 kunlar
Postlar arxiv
መልካም ዜና ለኢትዮጵያዊያን በሙሉ ወ/ሪት ለይላ ኑርሰቦ ረዲ ከእስር ተፈትተው ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ተወሰነ፣ ========================= (ሪያድ ፣ ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም) ወ/ሪት ለይላ ኑርሶቦ ረዲ የተባሉና በስራ ምክንያት ከዛሬ 13 ዓመት በፊት ወደ ሳዑዲ አረቢያ ለስራ የመጡ ዜጋችን የሰው ህይወት በማጥፋት ወንጀል ተከሰው በክስ ቻርጅ ቁጥር 13456902511 በሳኡዲ አረቢያ ሪያድ ከፍተኛ ፍ/ቤት በዋለው ችሎት ጥፋተኛ ናቸው በሚል በሞት እንዲቀጡ የፍርድ ውሳኔ አስተላልፎ እንደነበር ይታወሳል። በወቅቱ ዜጋችን ለስራ ከአገር ወጥተው በሰራተኝነት እያገለገሉ በነበሩበት ሁኔታ ከላይ የተጠቀሰውን ወንጀል በመፈጸማቸው የሞት ፍርድ መወሰኑ የመላ ኢትዮጵያዊያንን ልብ የሰበረ ነበር። ከዚህ በመነሳት ኤምባሲያችን ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት በእርቅ እንዲፈታ ከቤተሰባቸውና ከማህበረሰቡ የተውጣጣ ኮሚቴዎችን እንዲቋቋሙ በማድረግ፣ ጉዳዩን በማስተባበር ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል። በዚሁ መሠረት የተደረገው ሰፊ የዲፕሎማሲ ጥረት ፊሬ አፍርቶ ለተጎጂ ቤተሰብ የገንዘብ ካሣ በመክፈል ምህረት እንዲያገኙና ተወሰኖባቸው የነበረው የሞት ፍርድ ተነስቶላቸው ለአገራቸው እንዲበቁ በመወሰኑ እንኳን ደስ አላችሁ፣ እንኳን ደስ አለን። በዚህ አጋጣሚ ይህ ውጤት እንዲገኝ የተጎጂ ቤተሰቦችን በመካስ የዜጋችን ህይወት ለማትረፍ የተረባረባችሁ ኢትዮጵያዊያን በተለይም በሪያድ የምትገኙ የኮሚቴ አባላት፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የዜጋችንን ጉዳይ እንደራሳችሁ ጉዳይ ወስዳችሁ ቀን እና ሌሊት የደከማችሁ ወገኖቻችን፣ ለወገናችን ድምፅ በመሆንና ገንዘብ በማሰባሰብ እገዛ ያደረጋችሁ የሚዲያ ባለቤቶች፣ አገር ቤት ከህዝብ የተሰበሰበውን ገንዘብ በውጭ ምንዛሪ ተቀይሮ ለካሳ ክፍያው እንዲውል ለረዱን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አመራሮችና ሠራተኞች፣ እንዲሁም ይህ ውጤት እንዲገኝ ድጋፍ ላደረጉልን የሳዑዲ መንግስት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የስራ ሃላፊዎችና የፍትህ አካላት እንዲሁም በተለያየ መንገድ አስተዋፅኦ ለባረከታችሁ በሙሉ ኤምባሲው ከፍተኛ ምስጋና ያቀርባል። በተመሳሳይ መልኩ በተለያዩ ወንጀሎች ክስ ተመስርቶባቸው በእስር ላይ የነበሩ 1665 ዜጎቻችንን ሚሲዮናችንና የጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤታችን ባደረጉት ሰፊ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት የክስ ሂደታቸዉ ተቋርጦ ወደ አገራቸዉ እንዲመለሱ መደረጉ ይታወሳል። ይህ የሁለቱ አገሮች ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትና ትብብር በከፍተኛ ደረጃ እየተጠናከረ ለመምጣቱ አንድ ማሳያ ነው። በዚህ አጋጣሚም ዜጎቻችን ወደ ሳዑዲ አረቢያ ለስራ መምጣት ፍላጎት ካላችሁ በሁለቱ ሀገራት እየተተገበረ የሚገኘውን ህጋዊን የስራ ሰምሪት ተከትላችሁ እንዲትመጡ፣ በተሰማራችሁበት ቦታ ሁሉ የአገሩን ህግ አክብራችሁ እንድትሰሩ፣ አስቸጋሪ ሁኔታ ቢገጥማችሁ እንኳን በትግስት በማሳለፍ መብታችሁን በህጋዊ መንገድ ብቻ በማስከበር ከእንዲህ ዓይነቱ ወንጀሎች ራሳችሁን እንድትጠብቁ ኤምባሲው ይመክራል።