1 149
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-37 kunlar
-1830 kunlar
Postlar arxiv
1 149
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከጉ/ክ/ከ ለተወጣጡ 2500 የሴፍትኒት ተጠቃሚዎች የንግድ ስራ ክህሎት እና የንግድ ሥራ እቅድ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ ።
🇪🇹የካቲት 04/2018 ዓ.ም🇪🇹
ከጉለሌ ክፍለ ከተማ ለተወጣጡ 2500 የሴፍትኒት ተጠቃሚዎች በ3 ዙር የንግድ ስራ ክህሎት እና የንግድ ሥራ እቅድ ስልጠና በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና በሽሮሜዳ ካምፓስ መሰጠት ተጀመረ ።
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአጫጭር ሥልጠና አስተባባሪ አቶ ታደሠ አበራ ለሰልጣኞች እንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር በማድረግ በቆይታቸው ወቅት ማድረግ ስለሚገባቸው መብትና ግዴታ በዝርዝር ያብራሩ ሲሆን በተቻለ መጠን ሁሉም ሰልጣኝ በተመደበበት ክፍል በመገኘት ለተከታታይ አምስት ቀናት በመከታተል የስልጠናውን አላማ ግቡን እንዲመታ እና ሰልጣኞችም በቂ እውቀት አግኝታችሁ የቀጣይ የሂወት ውጣ ውረድን አሸንፋችሁ በስኬት ጎዳና እንድትጓዙ እንፈልጋለን ብለዋል። አያይዘውም ኮሌጁ የ100 ዓመት የካበተ ልምድና ISO 21001:2018 እውቅና ያገኘ በመሆኑ ብቃት ያላቸው አሰልጣኞችን በመመደብ በቅርብ ሆነን ክትትልና ድጋፍ የማድረግ ስራ እንደሚሠራ ገልፀው የሚያጋጥሙ ክፍተቶች ካሉም ፈጣን የሆነ የማስተካከያ መፍትሔ የሚሰጥ መሆኑን ገልፀዋል ።በመጨረሻም ስልጠናው በአግባቡ ላጠናቀቁ ሠልጣኞች ሠርትፍኬት የሚሠጥ መሆኑን አሳውቀዋል ።በቀጣይም የተፈሪ መኮንን ፖ/ቴ/ኮሌጅ በልዩ ልዪ መስኮች የአጫጭር ስልጠናዎችን ለዜጎች ለመስጠት በሙሉ አቅም እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመቶኛ ዓመት ክብረ በዓል፣ የስም ቅያሬ እና የዓለም አቀፍ የጥራት እውቅና (ISO) ዓለም አቀፍ የጥራት እውቅና የምስክር ወረቀት በድምቀት አከበረ።
🇪🇹የካቲት 03/2018 ዓ.ም🇪🇹
በአገራችን የትምህርት ታሪክ ውስጥ ቀዳሚ ከሆኑት ተቋማት አንዱ የሆነው የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ፣ ምስረታውን 100ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓሉን፣ የተቋሙን አዲስ የስም ቅያሬ እና የISO 21001:2018 (EOMS) ዓለም አቀፍ የጥራት እውቅና የምስክር ወረቀት በድምቀት አከበረ።
የካቲት 03 ቀን 2018 ዓ.ም. በተካሄደው በዚህ ታሪካዊ መርሃ ግብር ላይ የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ ከፍተኛ አመራሮች፣ የአዲስ አበባ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ዲኖች፣ የቀድሞ የተፈሪ መኮንን ተማሪዎች ማህበር ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ኮሌጁ ያለፈባቸውን መቶ ዓመታት ስኬታማ የልማትና የክህሎት ጉዞ የዘከረ ሲሆን፣ አሁን ካለው ተለዋዋጭ የቴክኖሎጂና የኢንዱስትሪ ፍላጎት ጋር ራሱን ለማጣጣም ያደረገውን የስም ቅያሬ በይፋ አብስሯል።
የዕለቱ ልዩ ክስተት የነበረው ኮሌጁ የትምህርት ተቋማት የአመራር ስርዓት (Educational Organizations Management System - EOMS) ዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃን ማሟላቱን የሚያረጋግጠው የISO 21001:2018 የምስክር ወረቀት መረከቡ ነው። ይህ እውቅና ኮሌጁ የሚሰጣቸው ስልጠናዎችና አገልግሎቶች ዓለም አቀፍ መስፈርቶችን የጠበቁ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ነው።
የኮሌጁ የሥልጠና አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ዲን እና ጊዜያዊ የኮሌጁ ዋና ዲን ተወካይ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ባደረጉት ንግግር፣ የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከአመሰራረቱ ጀምሮ ለሀገር ግንባታ ያበረከተውን አስተዋጽኦ በማስታወስ፣ አሁን ላይ ተቋሙ የደረሰበትን የላቀ የቴክኒክና ሙያ ደረጃ አብራርተዋል።
"ይህ የISO እውቅና ተቋማችን ለጥራትና ለልህቀት የሰጠው ትኩረት ውጤት ነው" ያሉት አቶ ደመላሽ፣ ለዚህ ስኬት መገኘት ከፍተኛ ድጋፍ ላደረጉ የመንግስት ተቋማት እና የኮሌጁ የISO ቡድን አባላት ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመቶኛ ዓመት ክብረ በዓል፣ የስም ቅያሬ እና የዓለም አቀፍ የጥራት እውቅና (ISO) ዓለም አቀፍ የጥራት እውቅና የምስክር ወረቀት በድምቀት አከበረ።
🇪🇹የካቲት 03/2018 ዓ.ም🇪🇹
በአገራችን የትምህርት ታሪክ ውስጥ ቀዳሚ ከሆኑት ተቋማት አንዱ የሆነው የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ፣ ምስረታውን 100ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓሉን፣ የተቋሙን አዲስ የስም ቅያሬ እና የISO 21001:2018 (EOMS) ዓለም አቀፍ የጥራት እውቅና የምስክር ወረቀት በድምቀት አከበረ።
የካቲት 03 ቀን 2018 ዓ.ም. በተካሄደው በዚህ ታሪካዊ መርሃ ግብር ላይ የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ ከፍተኛ አመራሮች፣ የአዲስ አበባ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ዲኖች፣ የቀድሞ የተፈሪ መኮንን ተማሪዎች ማህበር ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ኮሌጁ ያለፈባቸውን መቶ ዓመታት ስኬታማ የልማትና የክህሎት ጉዞ የዘከረ ሲሆን፣ አሁን ካለው ተለዋዋጭ የቴክኖሎጂና የኢንዱስትሪ ፍላጎት ጋር ራሱን ለማጣጣም ያደረገውን የስም ቅያሬ በይፋ አብስሯል።
የዕለቱ ልዩ ክስተት የነበረው ኮሌጁ የትምህርት ተቋማት የአመራር ስርዓት (Educational Organizations Management System - EOMS) ዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃን ማሟላቱን የሚያረጋግጠው የISO 21001:2018 የምስክር ወረቀት መረከቡ ነው። ይህ እውቅና ኮሌጁ የሚሰጣቸው ስልጠናዎችና አገልግሎቶች ዓለም አቀፍ መስፈርቶችን የጠበቁ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ነው።
የኮሌጁ የሥልጠና አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ዲን እና ጊዜያዊ የኮሌጁ ዋና ዲን ተወካይ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ባደረጉት ንግግር፣ የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከአመሰራረቱ ጀምሮ ለሀገር ግንባታ ያበረከተውን አስተዋጽኦ በማስታወስ፣ አሁን ላይ ተቋሙ የደረሰበትን የላቀ የቴክኒክና ሙያ ደረጃ አብራርተዋል።
"ይህ የISO እውቅና ተቋማችን ለጥራትና ለልህቀት የሰጠው ትኩረት ውጤት ነው" ያሉት አቶ ደመላሽ፣ ለዚህ ስኬት መገኘት ከፍተኛ ድጋፍ ላደረጉ የመንግስት ተቋማት እና የኮሌጁ የISO ቡድን አባላት ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
Repost from N/a
ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከአንድ ምዕተ ዓመት ጉዞ በኋላ ወደ ጥንታዊ ስያሜው ሲመለስ የዓለም አቀፍ ጥራት (ISO) የምስክር ወረቀት ባለቤት ሆኗል፡፡
🇪🇹 የካቲት 3/2018 ዓ.ም 🇪🇹
በአገራችን የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ታሪክ ውስጥ ፈር ቀዳጅ የሆነው አንጋፋው ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተመሰረተበትን 100ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በልዩ ድምቀት አከበረ።
ኮሌጁ ይህንን ታሪካዊ ምዕራፍ ሲያከብር ለዓመታት "እንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ" ተብሎ ይጠራበት የነበረውን ስያሜ በመተው ወደ ቀድሞው ታሪካዊ መጠሪያው "ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ" በይፋ ተመልሷል።
በተጨማሪም የትምህርት ጥራት አስተዳደር ስርዓቱን ዓለም አቀፍ ደረጃ ለማድረስ ባደረገው ጥረት የ ISO 21001:2018 (EOMS) የምስክር ወረቀት ባለቤት መሆኑ በበዓሉ ላይ ተበስሯል።
በበዓሉ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ የውጤት ተኮር ሥልጠናና ተቋማት ልማት ዘርፍ ኃላፊ ክብርት ዳግማዊት ግርማ የኮሌጁን ታሪካዊ ጉዞ በማውሳት አድንቀዋል።
ኮሌጁ ለአንድ ምዕተ ዓመት የአገሪቱን የኢንዱስትሪ መሪዎችና ባለሙያዎችን ሲያፈራ የኖረ የጥበብ ማዕከልም ነው ያሉት ኃላፊዋ ስያሜው ወደ ቀድሞው መመለሱ ታሪክን ከቴክኖሎጂ ጋር ለማገናኘት ትልቅ ፋይዳ እንዳለውና የISO እውቅና ማግኘቱ ደግሞ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ዜጎችን ለማፍራት ዋስትና እንደሚሆን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የማርኬቲንግ ዳይሬክተር አቶ ተኬ ብርሃነ በበኩላቸው፣ ኮሌጁ የጥራት ፍተሻዎችን አልፎ የISO 21001:2018 ባለቤት መሆኑን አረጋግጠዋል። "ይህ የምስክር ወረቀት ኮሌጁ የሚሰጠው ትምህርትና ስልጠና ዓለም አቀፍ መስፈርቶችን የሚያሟላ መሆኑን ማረጋገጫ ነው፤ ይህም ለሌሎች የቴክኒክና ሙያ ተቋማት አርአያ የሚሆን ተግባር ነው" ሲሉ የጥራት ደረጃውን አስፈላጊነት አስረድተዋል፡፡
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተወካይ ዋና ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ በበዓሉ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ቀኑ ለኮሌጁ ማህበረሰብ ድርብ ደስታ የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል። ኮሌጁ ወደ ቀደመ ስያሜው መለወጡ ታሪኩን አድሷል በISO የምስክር ወረቀት ደግሞ የወደፊት ጉዞውን በጥራት ላይ እንዲመሰረት አድርጓል ብለዋል። ኮሌጁ በቀጣይም በቴክኖሎጂ ሽግግርና በሰው ኃይል ልማት የአንበሳውን ድርሻ መወጣቱን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ1917 ዓ.ም ተመስርቶ የኢትዮጵያን ዘመናዊ ትምህርትና ቴክኖሎጂ በማቀጣጠል ረገድ ትልቅ አሻራ ያረፈበት ተቋም ነው። አሁን ላይ ታሪካዊ ስያሜውንና ዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃውን አጣምሮ መያዙ ለቀጣዩ 100 ዓመት አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል።
በመርሀ ግብሩ ኮሌጁ ያፈራቸው የጥበብ ባለሙያዎችን ጨምሮ የቀድሞ ተማሪዎች ህብረት አባላት፣የኮሌጅ ዲኖች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
<<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>>
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
👉 Tiktok
https://www.tiktok.com/@bols20116?_t=ZM-8y9L28EOubG&_r=1
👉Facebook
https://www.facebook.com/addisababatvetbureau
👉Telegram
https://t.me/AABOLS
👉YouTube
https://youtube.com/@bureauoflaborandskill?si=t9ZklwKzGx9rRyXf
👉website
https://aabols.gov.et
👉ለቅሬታ፣ አስተያየትና ጥቆማ
https://complain.aabols.gov.et
👉ለነፃ የስልክ ጥሪ
6524
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
