1 146
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-37 kunlar
-1830 kunlar
Postlar arxiv
1 146
+9
ዕለተ ረቡዕ ጥር 21/2016 ዓ.ም
ለስራ ፈላጊ ወጣቶች የህይወት ክህሎት
ስልጠና ተሰጠ።
በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከጉለሌ ክ/ከተማ ለተውጣጡ ከ4ሺ በላይ ስራ ፈላጊ ወጣቶች ልል ክህሎት/ የህይወት ክህሎት ስልጠና ከጥር 14/2017 - 20/2017 ተሰጥቷል ።
በስልጠናው ከተሳተፉበት አጠቃላይ ሠልጣኞች ቁጥር 60% ሴቶች መሆናቸውን አስተባባሪው አቶ ታደሰ አበራ ይገልጻሉ ።
የህይወት ክህሎት ስልጠና ስራን በአግባብ ለመከወን ብቻ ሳይሆን በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያቸው ውስጥ ትልቅ ሚና እንዳለው በማስገንዘብ ስልጠናውን በተገቢው መንገድ መውሰድ እንዲችሉ ተደርጓል ።
በቀጣይም በመረጡት ዘርፍ የሙያ ስልጠናውን የሚወስዱ ሲሆን በስልጠናው ማጠቃለያ በCOC ምዘና ተመዝነው ብቃታቸው ሲረጋገጥ ወደ ስራ እንደሚገቡ ለማወቅ ተችሏል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+4
ዕለተ ማክሰኞ ጥር 20/2017ዓ.ም
በሠልጣኞች የሥነ- ምግባር እና የፀረ-ሙስና ክበብ የልምድ ልውውጥ ተካሄደ።
ለልምድ ልውውጥ በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተገኘው የአዲስ አበባ ተግባረዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሠልጣኞች የሥነ- ምግባር እና የፀረ-ሙስና ክበብ አባላት ሲሆኑ በኮሌጃችን የሠልጣኞች የሥነ- ምግባር እና የፀረ-ሙስና ክበብ አወቃቀር፣ እያከናወናቸው ያለቱን ስራዎች ፣ የሚኒ ሚዲያ ተግባራት እና አጠቃላይ በሠልጣኞች እና በስልጠናው ዙሪያ የክበቡ እንቅስቃሴን አስመልክቶ በተነሱ ጥያቄዎች ዙሪያ የሠልጣኞች የሥነ- ምግባር እና የፀረ-ሙስና ክበብ ተጠሪ ሠልጣኝ አቤሴሎም ብርሃኑ ለቀረበለት ጥያቄ በመረጃ የተደገፈ ማብራሪያ ሰጥቷል።
በተጨማሪም የሥነ- ምግባር እና የፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ባለሙያ አቶ መከታው ሹመት በተመሳሳይ ማብራሪያ ሰጥተው በተግባረዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሥነ-ምግባር ዳይሬክቶሬት በሠልጣኞች የሥነ- ምግባር እና የፀረ-ሙስና ክበብ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን እንዲያጋሯቸው ጠይቀው የክበቡ ተጠሪ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተውበታል።
እንዳህ ያሉ የልምድ ልውውጦች ያለንን ለማጋራት እና ለመቀበል ያላቸው ፋይዳ የጎላ በመሆኑ ተጠናክረው ቢቀጥሉ
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
ዕለተ ሰኞ ጥር 19/ 2017ዓ.ም
በኢንኩቤሽን ሴንተር የጋራ የግንዛቤ
መፍጠሪያ ውይይት ተካሄደ።
የኮሌጁ ኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን በቀደሙ ግዚያት ያስጀመረው እና ስራው በሂደት ላይ ያለው የኢንኩቤሽን ሴንተር ፣ የሃሳብ ማፍለቂያ እና ማጎልበቻ ስፍራ ላይ መሟላት ያለባቸውን አስፈላጊ ቁሳቁሶች በማሟላት ደረጃውን ጠብቆ ስራውን እንዲያስኬድ ለማስቻል መከናወን ያለበትን ተግባር በተለያዩ አግባብ በተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ሰፊ ውይይት ተካሂዶበታል።
በተጨማሪም በተማሪዎች የተጠነሰሰው የቢዝነስ ሃሳብ የቀረበ ሲሆን ለስራው ተግባራዊነት ነባሩና አዲስ አመራሩ ከኢንኩቤሽን ሴንተር ቡድን አባላት ጋር በጋራ በመወያየት ስራውን ወደ ተግባር ለመለወጥ መሰራት ባለባቸው ስራዎች ዙሪያ ውይይት እና በቀጣይ ሊሰሩ በሚገባቸው ተግባራት ላይ የስራ አቅጣጨ ተሰጠ ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን።
1 146
ዕለተ ሰኞ ጥር 19/2017ዓ.ም
የስልጠና ዘርፎች የስራ ርክክብ ተካሄዱ ።
ከአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ በተሰጠ አቅጣጫ መሠረት የተጀመረው የሪፎርም ስራ በስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች መካከል ውድድር ተካሂዷል ።
በመሆኑም ባለፈው ሳምንት በተካሄደው የመተካካት ሂደት የቀደመውን የስልጠና ዘርፍ ተጠሪ በክብር መሸኘታቸው የሚታወቅ ሲሆን በዛሬው ዕለት ርክክባቸውን ያካሄዱት የGMF ስልጠና ዘርፍ ፣ የከተማ ግብርና እና የቢዝነስ ስልጠና ዘርፎች ርክክባቸውን አካሂደዋል።
የርክክብ ሂደቱ በአራት ዘርፍ የተጠናከረ ሲሆን 1- የስልጠናው ሂደት ያለበት ደረጃ
2- የአሰልጣኝ ምደባ መረጃዎች
3- የISO ትግበራ ሂደት እና ስራዎቹ
4- የ2017ዓ.ም የተከለሰ ዕቅድና
ሪፖርት እንዲሁም የቢሮ ቁልፍ ርክክብ የተደረገባቸው ሲሆን ከዚህም በተጨማሪም በርክክቡ ላይ የተገኙት አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ምንም እንኳን ርክክቡ ቢካሄድም በቀደሙት የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች መጠናቀቅ አለባቸው ያሏቸውን ተግባራትም ዘርዝረዋል። እነሱም የስድስት ወር የስራ አፈጻጸም፣ የተጀማመሩና አሁን መጠናቀቅ አለባቸው ያሏቸውን ስራዎች እንዲያጠናቅቁም አሳስበዋል።
በተጨማሪም በስራው ሂደት ነባሩም ሆነ አዳዲስ ምድብተኞች በመደጋገፍ እና በመረዳዳት ስራቸውን እንዲያከናውኑ ጠይቀው የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎቹ ለነበራቸው ቆይታና ተሳትፎ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
ዕለተ ሐሙስ ጥር 15/2017ዓ.ም
የእንጦጦ ፖ/ቴ ኮሌጅ/የተፈሪ መኮንን የ፻ ኛ ዓመት በዓል አከባበር ሂደት ላይ ከፍተኛ ውይይት ተካሄደ ።
ውይይቱን ያደረጉት የቀድሞ የተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ተማሪዎች ማህበር አመራሮች እና የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮር የማኔጅመንት አመራሮች ከበዓል አከባበሩ ዓብይ ኮሚቴ ጋር በመሆን ነው።
ለዚህ ውይይት መነሻ የሚሆን ረቂቅ የመወያያ ሰነድ በማህበሩ አመራር ቀርቦ በይዘቱ ላይ ነጥብ በነጥብ ስፋትና ጥልቀት ባለው መልኩ ውይይት ከተደረገበት በኋላ በጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል።
በውይይቱ ከተነሱት ነጥቦች ውስጥ የኮሌጅ የዋና በር ግንባታ የምረቃ ስነ-ስርዓት እና የባለ አራት ወለል አዲስ የህንጻ ግንባታ የመሠረት ድንጋይ ማስቀመጥ ዋነኞቹ እንደነበሩ ታውቋል። በመቀጠል ሂደቱ በዝግጅት ምዕራፍ እና የትግበራ ምዕራፍ ተብሎ በማስቀመጥ በነዚህ ሁለት ክፍሎች ስለሚከናወኑ ተግባራት እንደዚሁም ተግባራቱን ለማከናወን በሃላፊነት የሚመሩ አካላትን የመለየት ስራዎች በውይይቱ መግባባት የተደረሰባቸው ነጥቦች ናቸው።
በትግበራ ምዕራፍ ክፍሉ በዓሉ የሚከበርባቸው ሦስት ተከታታይ ቀናትን የለየ (ከሚያዚያ 19-21/2017ዓ.ም) ሲሆን የመጀመሪያው ቀን የዋና በር ግንባታ እንደሚመረቅና የአዲሱ ህንጻ ግንባታ የመሠረት ድንጋይ እንደሚቀመጥ ሰነዱ ላይ ተመላክቷል። ለነዚህ ዓበይት ስራዎች አፈጻጸም የሚረዳና የበዓል አከባበሩ የሚደምቅበት ዝርዝር የድርጊት መርሃ ግብር ተካቷል ። በሁለተኛው ቀን ደግሞ የቡድን ውድድሮች እና ባዛር እንደሚኖሩ የተጠቆመ ሲሆን በሦስተኛው ቀን የበዓል አከባበሩ ዕለት የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራሞችን ጨምሮ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት እውቅና መስጠትና የሙዚቃ ድግስ እንደሚኖር መርሃ ግብሩ ያመላክታል።
በቅድመ ዝግጅት ከሚከናወኑት ተግባራት መካከል ከበዓል አከባበሩ አንድ ወር ቀድሞ የሚደረገው የፓናል ውይይት ተጠቃሽ ሲሆን ቀጣይነት ባለው የትምህርት ስርዓት ጥቅም ላይ እንደሚያተኩርም ታውቋል።
በመጨረሻም ዝግጅቱና ትግበራው በተቀመጠለት ፕሮግራም እንዲካሄድና ሃላፊነት በተሰጣቸው አካላት እንዲመራ መግባባት ላይ በመድረስ ወቅቱን በጠበቀ ክትትል ድጋፍ ተደርጎለት እንዳስፈላጊነቱ የማስተካከያ አሰራር እንደሚኖር ተወያዮቹ አውስተዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
ዕለተ ሐሙስ ጥር 15/2017ዓ.ም
ኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ስልጠና ዘርፍ በከፍተኛ አመራሩ ተጎበኘ።
የስልጠና ስራውን ውጤታማ ለማድረግ እና የተሳለጠ እንዲሆን የሾፕ አደረጃጀት በስምንት እስቴሽን የተከፋፈለ ሲሆን እያንዳንዱ አደረጃጀት የካይዘን ትግበራ ውጤታማነት የታየበት እና እንደ አብነትም የሚጠቀስ መሆኑን መመልከት ተችሏል።
ከዚህ በተጨማሪ ስልጠና ዘርፉ ያለውን የሰው ሃይልና ማቴሪያል በማቀናጀት ስልጠናውን ውጤታማ ለማድረግ በራስ ተነሳሽነት የተለያዩ ተግባራትን አከናውኗል ። ከነዚህም መካከል ስራን በቴክኖሎጂ ከማዘመን አንጻር መረጃ ማሰባሰቢያ ዳታ ማኔጅመንት ሲስተምን ተግባራዊ በማድረግ የማሰልጠኛ ሞጁሎች፣ ለስራው የሚጠቀሙባቸውን የተለያዩ ሰነዶች እና የሠልጣኝ መረጃዎች ፣የስልጠና ፕሮግራምና እና ሌሎች መረጃዎችን በአንድ የመረጃ ቋት የማስገባት ስራ ተሰርቷል ።
በሌላ መልኩ ደግሞ የስልጠና ሾፖችን ደህንነት ለመቆጣጠር የሚያስችል የደህንነት ካሜራ በስልጠና ዘርፉ የማሰልጠኛ ክፍሎች በመትከል ከአንድ ማእከል መረጃውን ለመከታተል የሚያስችል ስራ ተሰርቷል ።
በመጨረሻም ጉብኝቱን ያደረጉት ዲን የስልጠና ዘርፉን ስራ በማድነቅ በቀጣይነት ሊሰሩ ይገባቸዋል ያሏቸውን ስራዎች ማለትም ሰልጣኞች በኮሌጁ ውስጥ ባሉና በብልሽት አገልግሎት በማይሰጡ እቃዎች ልምምድ እንዲያደርጉ ፣ በክፍሉ የተሰራው የደህንነት ካሜራ ወደ ሌሎች የስራ ክፍሎች እንዲስፋፋ ቢደረግ የሚልና ስራው በኢንተርፕራይዝ ተካቶ ተጨማሪ ገቢ ለማስገኘት የሚያስችል ስራዎችን ለመስራት ቢቻል የሚል አስተያየታቸውን ለግሰዋል።
የኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ስልጠና ዘርፍ በአራት የትምህርት ዘርፍ በኤሌክትሮኒክስ፣ በቪዲዮ ግራፊ፣ ኢንስትሩመንት እና የህንጻ መስመር ዝርጋታ ላይ ስልጠና ይሰጣል። ስልጠናውን በበለጠ ለማስፋትና ሙሉ አቅሙን ተጠቅሞ ለመስራት ያለበትን የግብአት እጥረት ለመቅረፍ ጥረት ቢደረግ የሚል አስተያየት በአሰልጣኝ ይድነቃቸው ደምበል ተሰጥቷል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+7
ዕለተ ሐሙስ ጥር 15/2017ዓ.ም
የሪፎርም ፕሮግራም በስልጠና ዘርፍ
ተጠሪዎችና አስተባባሪዎች ተካሄደ።
ከአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ በተሰጠ አቅጣጫ መነሻነት በዛሬው ዕለት ውጤቱ ይፋ የሆነው የሪፎርም ስራ ስድስት መመዘኛዎችን /መስፈርቶችን መሠረት አድርጎ የተሰራ መሆኑን የኮሌጁ ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ ገልጸዋል ።
ከነዚህም በዋነኛነት የተቀመጡት በአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ የተሰጠው የጽሁፍ ፈተና ሲሆን ፆታዊ ተዋጽኦ፣ የስራ አፈጻጸምና የስራ ተነሳሽነት እና ሌሎችም የመወዳደሪያ መስፈርቶች መሆናቸው ታውቋል።
በመቀጠልም ለውጥ የተደረገባቸው የኤስቴቲክስ፣ ቢዝነስ፣የከተማ ግብርና፣ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ እንጨትና ብረታ ብረት ስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች ለነበራቸው ቆይታ የምስጋና የምስክር ወረቀት ተሠጥቷቸዋል።
በተያያዘም ቀድሞ የነበሩና አዲስ የተመለመሉ የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች በጋራ በቀጣይ ትኩረት የሚደረግባቸው የስራ አቅጣጫዎች ተሰጥቷል ። ይህንን ውጤታማ ለማድረግ አመራሩ በአዲስ መልክ ከተዋቀረው የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎችና አስተባባሪዎች ጋር በጋራ እንደሚሰሩና የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን እንደሚሰጡ ቃል ገብተዋል ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
ዕለተ ዓርብ ጥር 9/2017ዓ.ም.
የ2ኛ ሩብ ዓት /የስድስት ወር የዕቅድ አፈጻጸም
ሪፖርት እና የ90 ቀናት ዕቅድ ቀረበ ፡፡
የተካሄደው ስብሰባ ሁለት ዋና አጀንዳዎች ላይ
ያተኮረ ነበር፡
1. የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖረት
2. የ90 ቀናት ዕቅድ
የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖረቱ የበጀት ዓመቱ ሁለተኛ ሩብ ዓመት ላይ መሰረት ያደረገ ሲሆን በዕቅድ ዝግጅትና ክትትል ዳይሬክቶሬት ወ/ሪት ፀዳለ አድማሱ የ6 ወራት የዕቕድ አፈጻጸም ሪፖርት ለኮሌጁ ማህበረሰብ ቀርቧል፡፡ በስራ ክፍሎች ምን ታቀደ፣ምንስ ተሰራ ብሎ ለመዳሰስ የተሞከረበት ነበር፡፡ በዚህ ስበሰባ ሁሉም በአብዛኛው የኮሌጁ ማህበረሰብ ዲኖች፣አሠልጣኞች እና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች የተሳተፉበት ነበር፡፡
በሁለተኛ ደረጃ ለውይይት የቀረበው አጀንዳ የ90 ቀናት ዕቅድ ላይ የተካተቱት 8 ዐበይት ተግባራት ላይ ያተኮረ ሲሆን ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ሥራና ክህሎት ቢሮ ለኮሌጆች በቀጣይ 90 ቀናት ሊተገብሩዋቸው የሚገቡ 8 ዐበይት እና ዝርዝር ተግባራትን የያዘ መሆኑን በአቶ ወንድም ሲያምረኝ መኮንን የኢነዱስተሪ ኤክስቴንሽን መክትል ዲን ካቀረቡት መረጃ ለማወቅ ተችሏል፡፡ እነሱም ፡-
1. የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎችን መልሶ ማደራጅት
2. በአሁኑ ወቅት ሥልጠና የማይሰጡ
አሰልጣኞችን መለየት
3. ዞኒግ እና ዲፈረንሸሽንን መተግበር
4. የአሰልጣኞችን ብቃት መመዘን
5. የኢ-እስኩል ምዝገባን ማጠናቀር
6. የተቋም/የምድረ ግቢ ማደራጀት
7. የ ISO 21001፡2018 ትግበራን ማጠናቀቅ
8. የኮሌጅ ኢንተርፕራይዝ ማቀቀም የሚሉ አጀንዳዎች በዝርዝር ከቀረቡ ቦኋላ በዋና ዲኑ አቶ አብዱለበር መሐመድ አወያይነት ከቤቱ በተለያየ መልክ ማለትም በጥያቄና ምልስ ፤በአስተያየት ወይም ቢጨመር የተባሉ እና ባይካተት የተባሉ ሃሳቦች ቀርበው ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን በስጋት መልክ የተነጸባረቁም ነበሩ፡፡ ለምሳሌ የዕቅድ ክንውን ሪፖረቱ ያላካተታቸው የስራ ክፊሎች የፋይናንስ፣የበጀት፣የግዢ ተካተው ሪፖረቱ የተሟላ ማድረግ ቢቻል ፡፡ እንደዚሁም በሶስተኛ ሩብ ዓመት የሚከናወኑትን ተግባራት አፈጻጸማቸው ዜሮ ተብሎ ሪፖርት መደረግ እንደማይገባ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ በሌላ መልኩ ደግም እንደ ስጋት ከተንጸባረቁት አንዱና ዋነኛው ከአሠልጣኞች ምደባ ጋር ተያየዞ በ90 ቀናት ውስጥ እንዲጠናቀቅ መወሰኑን የሚመለከት ጉዳይ ከግዜው አንጻር ቢታይ የሚሉ ነበሩ ፡፡ በመጨረሻም የሚከተሉት የማጠቀለያ ነጥቦች ተቀምጠዋል፡፡
ማጠቃለያ
ይህ የ90 ቀን ዕቅድ በተሳካ ሁኔታ መተግበር እንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዓላማውን ለማሳካት ብቻ ሳይሆን በቀጣይ ለሀገር ዕድገትና ብልጽግና ጠንካራ መሰረት ይጥላል፡፡
ኮሌጁ በስልጠናና በሰራተኞች ብቃት ረገድ የላቀ ውጤት በማምጣት በሰልጣኞችና በሁሉም የኮሌጁ ሰራተኞች ላይ ከፍተኛ አዎንታዊ ተጽእኖ ለማሳረፍ ተዘጋጅቷል፡፡
በመጨረሻም የአካባቢው ማህበረሰብ ስለ ቴክኒክ አና ሙያ ስልጠና ጥራት ያላቸውን እምነት እንዲጨምር አስተዋጽኦ ያደርጋል፡፡
ሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰብ በጋራ የሚያደርጉት ጥረት ይህንን ዕቅድ ዕውን ለማድረግ ወሳኝ በመሆኑ ከአደራ ጭምር ለስኬታማነቱ እንድንረባረብ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
ኮሙኒኔሽን ቡድን
1 146
+7
ዕለተ ዓርብ ጥር 9/ 2017ዓ.ም
ሁለተኛው ዙር የሙዚቃና የስነ-ጽሁፍ ምሽት ተዘጋጅቷል።
የቀድሞ የተፈሪ መኮንን የአሁኑ እንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኤስቴቲክስ ስልጠና ዘርፍ የሙዚቃና የስነ-ጽሁፍ ምሽት በዛሬው ዕለት ከቀኑ 9:00 ጀምሮ ተካሂዷል።
ፕሮግራሙን ያዘጋጁት የ3ኛ ዓመት የሙዚቃ ትምህርት ክፍል ሠልጣኞች ሲሆኑ ዓላማው መደበኛና የማታ ክፍለ ግዜ ሠልጣኞች በአንድ መድረክ የሚያገናኙበትና በሙያቸው መደጋገፍ የሚያስችላቸውን ከቀደሙ ባለሙያዎች ልምድ የሚያካብቱበት መድረክን ለመለማመድ የሚያግዛቸው መድረክ ሲሆን ለቀጣይ ስራዎቻቸው መደላድልን ለመፍጠር እንዲያስችላቸው ታልሞ የተዘጋጀ ነው ያሉን የፕሮግራሙ አዘጋጅ ሠልጣኝ አቤሴሎም ብርሃኑ ናቸው።
በፕሮግራሙ መክፈቻ ላይ የተገኙት የኮሌጁ ስነምግባርና የፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ተጠሪ ወ/ሮ ዝግጁ ግዛቸው ሠልጣኞች በሙያቸው ለሚያከናውኑት ተግባራት ታማኝ በመሆን እንዲያከናውኑ ምክራቸውን ለግሰዋል ።
በማስከለም በትምህርት ክፍሉ ሠልጣኞች ግጥም፣ሙዚቃና ሞኖሎግ መነባንብ የቀረበ ሲሆን ሠልጣኞች የተለያዩ ባለሙያዎች ስራዎችን በማስመሠል ተጫውተውታል።
በአጠቃላይ ፕሮግራሙ ቀጣይነት ኖሮት የእርስ በርስ መቀራረቡ እና መድረክ መልመዱ፣ ከቀደሙት ባለሙያዎች ልምድ መጋራቱ ቀጣይነት እዲኖረው ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ አስተባባሪው ሠልጣኝ አቤሴሎም ብርሃኑ ይጠይቃሉ ።
"ባለቤት ያቀለለውን አሞሌ ---- " እንደሚሉት የስልጠና ዘርፉ እና የሚመለከተው አካል ትኩረት ሠጥቶ እንዲሰራበት የዝግጅት ክፍላችን መልዕክቱን ያስተላልፋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
