ለትውልድ | LETIWULID 🦋
2 246
Obunachilar
-424 soatlar
-117 kunlar
-4030 kunlar
- Kanalning o'sishi
- Post qamrovi
- ER - jalb qilish nisbati
Ma'lumot yuklanmoqda...
Obunachilar o'sish tezligi
Ma'lumot yuklanmoqda...
Photo unavailableShow in Telegram
ድል አለን!
:
ከልጅ እስከ አዋቂ፣ ከሊቅ እስከ ደቂቅ፣ ከትሽ እስከ ትልቅ ሁላችን እንደክብራችን ሁላችን እንደ ኢትዮጲያዊነታችን ድል አለን። ድል ሲባል አንድ ሰሞን የሚነሳ በሌላ ጊዜ የሚወድቅ አይደለም፣ ድል ሲባል በቁስ ወይም በገንዘብ የሚገለፅ ድል አይደለም ድላችን የማንነት ነው፣ ድላችን የእኛነት ነው፣ ድላችን የኢትዮጲያዊነት ብሎም የጥቁር ህዝቦች ጌጥ ነው። ማንም ብቻውን ተዋግቶ ያላሸነፈው፣ ማንም ልብቻው ተጋፍጦ ያላለፈው፣ ማንም ከኢትዮጵያዊነት በላይ ዘሩን ያላስቀደመበት፣ ሁሉም በኢትዮጵያውያዊነቱ እራሱን የሰጠበት፣ በህብረት የተፋለመበት፣ በሃሳብ በአላማ አንድ ሆኖ ተባብሮ ድል ያደረገበት፣ ወራሪውን ሃይል ያሳፈረበት ዘመን የማይሽረው፣ ታሪክ የማይረሳው ታላቅ ድል አለን። እኛ ዛሬ እኛን ስለመሆናችን፣ እያንዳንዳችን የሚያኮራንን ማንነት ስለመያዛችን፣ በየራሳችን ቋንቋ፣ በየራሳችን ባህል ስለመታወቃችን፣ ውስጣችን በጀብድ ልባችንም በንቃት ስለመሞላቱ ዋናው ምክንያት የአያት ቅድመ አያቶቻችን አርበኝነት ነው።
የምትሰጠው አትጣ!
፡
የሚሰስት ትርፍ የለውም፣ መስጠት የማይወድ በረከት የለውም፤ እርካታ የለውም። መኖር በመስጠት ውስጥ ነው። ስትሰጥ የምታገኘውን ስጦታ፣ የሚሰማህን ስሜት ምንም ብታደርግ አታገኘውም፣ ምንም ብትፈፅም ሊሰማህ አይችልም። የህይወት ትርጉም የአምላክን ፀጋ በእኛ በኩል ለሰዎች ማሻገር ነው። ሁሉን የሚሰጥ ደግ አምላክ፣ ቸር ፈጣሪ ነው። ባህሪው መስጠት ነው፤ ንፉግነት የለበትም። የእርሱን ባህሪ ለሚከተለው ሌላ ይጨምርለታል፤ ለማይሰጠው ለንፉጉም የሚገባውን ባይከለክለውም እንኳን በመስጠት የሚያገኘውን የተትረፈረፈ በረከት ግን ያሳጣዋል። ለጋስ ለመሆን ከሰፊ አዛኝ ልብ ውጪ የሚያስፈልግ ነገር የለም።
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ!
@MentalCounsel
❤️ LIKE & SHARE
ቤተሰብ ይሁኑ👉 https://t.me/letiwulid🥰 6❤ 1
❇️ VACANCY ANNOUNCEMENT❇️
Position: Sales Person
Job type: Full Time with Shift
Quantity: 2
Gender: Female
Company: Dagnu Wood Work and Furniture
Salary: 4500 - 5000 + 1% Commission
Location: Gurd Shola
Requirements:
Excellent communication and negotiation skills
Excellent Customers handling
Note: First applicants will get a priority
Don't forget to Consider the proximity of your residence with work place
Contact: @epha_aschalew
Deadline: Wed, 31/01/2024
❤ 2👍 1👏 1
God said, "love your enemy" and I obeyed & loved myself.
እግዚአብሔርም አለ፦ "ጠላትህን ውደድ" እኔም አከበርኩትና እራሴን ወደድኩ።
- Khalil Gibran❤ 6👏 2🔥 1🥰 1
ትችሉ ነበር አሁንም ትችላላችሁ!
፡
አንዳንድ ሰዎች የእሳቤ ሂደት ይህንን ይመስላል፡-
“እንደምችል አውቀዋለሁ” በሚል ጠንካራ እሳቤ ይጀምሩና ከዚያም ቀስ በቀስ፣ “የምችል ይመስለኛል” ወደሚል እሳቤ ወረድ ይላሉ፡፡ ብዙም ሳይቆዩ፣ “የምችል ይመስለኝ ነበር” ወደሚለው እሳቤ ከተንሻራተቱ በኋላ በመጨረሻ “አልችል” በማለት ይደመድሙታል፡፡
እንደምንችል እናውቀው ነበር! እንችል ነበር! አሁንም እንችላለን!
❤️ LIKE & SHARE
ቤተሰብ ይሁኑ👉 https://t.me/letiwulid❤ 6👏 2🔥 1🥰 1
Repost from ELODIA™ ኤሎድያ
🍸ብርጭቆ ተጋበዝ!
በመጀመሪያ ባዶ ብርጭቆን ተመልከት። ከዚያም የተወሰነ ያህል ውሃ ጨምርበት። ከዚያም አፍስሰው... ተመልሶ ባዶ ይቀራል አይደል?
አሁን ራስህን ተመልከት
🥃 አሁንም ብርጭቆውን ግማሽ ያህል ውሃ አድርግበት። ከዚያም የተወሰነ ያህል አፍስሰው። ድጋሜም የተወሰነ ያህል አፍስስ... አሁንም እንደዛው አፍስሰው… ብርጭቆው ባዶ መቅረቱ አይቀርም አይደል?
እንዲህ ብታደርግስ?
🥃 ብርጭቆውን ሙሉ ውሃ ሙላው። ከዚያም የሞላው ላይ ውሃ መጨመርህን ቀጥል። ብርጭቆው ሲጎድል ይታይሃል? በፍጹም ሊጎደል አይችልም። እንዲያውም ይፈሰዋል አይደል?
እስኪ ምን ተረዳህ? ጊዜ ውሰድና አሰብ አድርግ።
🥃 በትክክል! ራስህን ምን ያህል ትወዳለህ? ራስህን ሳትወድ፣ ራስህን ሳታከብር፣ ለራስህ ሳይኖርህ በፊት ለሰዎች የምትሰጠው ማንኛውም ገንዘብ፣ ክብር፣ ፍቅር አንተን ባዶ ያስቀርሃል። ባዶነትህን ደሞ የሚወድልህ አይኖርም!
ስለዚህ?
☑️ አዎ በቅድሚያ ሙሉ ለሙሉ ራስህን ውደድ፣ ለራስህ ክብር ይኑርህ፣ የራስህ ነገር ይኑርህ። ከዚያ ለሌሎች ሞልተህ መፍሰስ ትጀምራለህ። ቅድሚያ ለራስህ ስጥ! አይዞህ ይህ ኃጢአት ወይም በሰዎች የመከፋት ዝንባሌ አይደለም። ራስህን ከልብ መውደድ ስትችል ሌሎችንም ከልብህ መውደድ ይቻልሃል፤ ራስህን የእውነት ስታከብር... የራስህ ነገር ሲኖርህ ሌሎችም እንዲኖራቸው የምትመች ትሆናለህ። አንተ እንደ ብርጭቆው ነህ ወይ ሞልተህ መፍሰስ አሊያም ባዶ ሆነህ መቅረት ያንተው ናቸው።
/በራስ መተመመን መጽሐፍ/
©Teklu Tilahun
THANK YOU FOR READING
ELODIA READING📚📖
ኤሎድያ ንባብ📚📖
#share and join for more👍
@Elodia_G ንባብ @Elodia_G READING
@Elodia_G ንባብ @Elodia_G READING
@Elodia_G ንባብ @Elodia_G READING
👍 4❤ 1👏 1🤔 1
ማንም በሌለበት
!
:
በዛ በጨለማ
ማንም በሌለበት
፣ ጠያቂ በማታገኝበት፣ አይዞህ ባይ አበርታች፣ በሃሳብም ሆነ በገንዘብ የሚደግፍህ በሌለህ ሰዓት ምን እያደረክ ነበር? ስለሆነብህ እያማረርክ ወይስ ምሬትህን ለመቀየር ጠንክረህ እየሰራህ? ብቸኝነትህን እየረገምከው ወይስ እራስህን ለመገንባት እንደ መልካም አጋጣሚ እየተጠቀምከው? እድለኛ እንዳልሆንክ እያሰብክ ወይስ ሁኔታውን ለመቀየር እየተፋለምክ? ብቻህን ስትሆን የሚኖርህ ማንነት ያንተ ትክክለኛው ማንነት ነው። አንተና ፈጣሪ ብቻ የምታውቁት የግል ሚስጥርህ ይኖራል። በገባህ ልክ እለት እለት ለብቻህ የምትፋለምለት ሃሳብ ይኖርሃል። "ብቻዬን ነኝ፣ ሰው የለኝም፣ የሚያግዘኝ አላገኘውም፣ የማደርገው ነገር በማንም ተቀባይነት አላገኘው፣ ማንም አላመነበትም።" ብለህ አታቆመውም።
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ!
@MentalCounsel
❤️ LIKE & SHARE
ቤተሰብ ይሁኑ👉 https://t.me/letiwulidለትውልድ | LETIWULID 🦋
🔰ንቃት ለትውልድ🔰 ቤተሰብ ይሁኑ! 🙏
እራስህን ምረጥ
!
፡
ብቻህን ብትቀርም፣ ብትገፋም፣ ስምህ ቢጠፋም፣ ቦታ ባይሰጥህም
እራስህን ምረጥ
፣ ለራስህ ታመን፣ ለራስህ ኑር፣ እራስህንም ከልብህ ውደደው። አንተ ያልመረጥከውን ማንነት ማንም አይመርጥልህም፣ አንተ ያልወደድከውን ስብዕናህን ማንም አይወድልህም፣ አንተ የማታከብረውን ሰውነት ማንም አያከብረውም። ያለህ ነገር በሙሉ በእግዚአብሔር ተመርጦልህ እንጂ አንተ መርጠሀው አይደለም፤ የተሰጠህ በሙሉ ያንተ በመሆን እንደምታተርፍ ስለታወቀ እንጂ ቢጎዳህ በፈጣም አይሰጥህም ነበር። ብቸኝነትህ ዋናው የስኬትህ ቁልፍ ነው። ብቸኝነት ነፃነት አለው፣ ከብዙ እስራት ነፃ የሚያወጣ ነፃንተ፣ ገደብህን አልፈህ እንድትሔድ የሚያግዝ ነፃነት፣ ህልምህን እንድትኖር፣ ደስታህን እንድታጣጥም፣ ለራስህ ጊዜ እንዲኖርህ የሚያደርግ ነፃነት አለው።
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ!
@MentalCounsel
❤️ LIKE & SHARE
ቤተሰብ ይሁኑ👉 https://t.me/letiwulid👍 4❤ 4🔥 1🥰 1
የመቀላቀል አባዜህን አስተካል
!
:
ትኩረትህን አሰልጥን፣ በመሃል የሚመጡ ሃሳቦችን ሞግታቸው፣ አዕምሮህን ከሚያናጋ አጫጭር ነገር እራስህን ቆጥብ፣ በአንዴ አንድ ነገር ብቻ የመስራት ልምድ አዳብር። ከእያንዳንዱ ተግባር ጀርባ ውስጣዊ እርካታና ጠዓም አለ፣ ከእያንዳንዱ እቅድና ሃሳብ ጀርባ ውጤት አለ። በአንድ ጊዜ ሃሳብህ ላይ ብቻ ካላተኮርክ ተግባሩ ከንቱ ምኞት ነው፤ ተግባሩን በሙሉ ልብህ ካልሰራሀው፣ ደጋግመህ ካላረምከው፣ ተገቢውን ጊዜ ካልሰጠሀው የፈለከውን ውጤት በጠበከው ጥራት የማግኘት እድልህ እጅጉን አናሳ ነው። ከመቀላቀል በላይ ለፈለከው ነገር እራስህን ስጥ፣ ከማምታትት በላይ በአንዴ አንድ ነገር ላይ ብቻ አተኩር። የልፋትህን ውጤት፣ የድካምህን ፍሬም በፈለከው ጥራትና መጠን ልክ አግኘው።
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ!
@MentalCounsel
❤️ LIKE & SHARE
ቤተሰብ ይሁኑ👉 https://t.me/letiwulid👍 5
ልብሽ ይማርካል!
:
መንፈስሽ ይስባል፤ ቀልብን ይሰርቃል፤ ውስጥን ያረጋጋል፤ መንፈስን ያድሳል። ነፍስሽ እንቁ ነች፤ ማንነትሽ ግሩም ነው፤ ስብዕናሽ ድንቅ ነው። በስብራት ውስጥ የተሰራ፣ ፈተናዎችን ያሸነፈ፣ እራሱን የመሰለ፣ እራሱን የሆነ ነው። መልካም ውብ ሴት መሆን፣ ማራኪ የተከበረች አክባሪ ሴት መሆን ክፍያው ብዙ አይደለም፤ ቅንነት፣ መልካምነት፣ ደግ አሳቢነትና በእራስ መተማመን ብቻ ነው። መንገስ ከፈለግሽ በቁመናሽ ሳይሆን በማንነትሽ ንገሺ፤ መወደድ ከፈለግሽ በገፅታሽ ሳይሆን በአንቺነትሽ ተወደጂ፤ እንዲቀበሉሽ፣ እንዲደመሙብሽ፣ እንዲደነቁብሽ ከፈለግሽ በተክለሰውነትሽ ሳይሆን በስብዕናሽ አስደምሚ፣ በቅንነትሽ አስደንቂ፣ በሰውነትሽ አስገርሚ።
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ!
@MentalCounsel
❤️ LIKE & SHARE
ቤተሰብ ይሁኑ👉 https://t.me/letiwulid❤ 4👏 4