uz
Feedback
Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗

Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗

Kanalga Telegram’da o‘tish

Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Comments Construction Solution Official Service

Ko'proq ko'rsatish
3 585
Obunachilar
-124 soatlar
-17 kunlar
+5430 kunlar
Postlar arxiv
የታህሳስ_ወር_2017_ዓ_ም_የሀራጅ_ሽያጭ_ማስታወቂያ.PDF2.81 MB

⚠️የጸደቀው የሕንፃ አዋጅ የስነ ሕንጻ -ንድፍ ሙያተኞች ላይ ስጋት እንደሚፈጥር ተገለጸ!
አዲሱ የሕንፃ አዋጅ የስነ ሕንጻ -ንድፍ ባለሙያ (አርክቴክቶች)ን ሙያ የሚያሳጡ ነጥቦች የተካተቱበት ነው ሲል የኢትዮጵያ አርክቴክቶች ማህበር ቅሬታውን ለአሐዱ ገልጿል። በዛሬው ዕለት በተከናወነው 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት በ4ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ 9ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ የሪል ስቴት ልማትና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ አዋጅን ጨምሮ ሦስት አዋጆችን መርምሮ አጽድቋል። "ይሁንና በፀደቀው አዋጅ ላይ ቅሬታችንን ብናቀርብም ተቀባይነት ተነፍጎንናል" ያለው የስነ ሕንፃ ንድፍ ባለሙያዎች ማሕበሩ፤ ቀድሞውኑ በረቂቅ አዋጁ ላይ ቅሬታው እንደነበረው አስታውቋል። የስነ ሕንጻ - ንድፍ ባለሙያዎች ማህበር፤ "በቀድሞው የሕንፃ አዋጅ ላይ ተጠብቀው የኖሩና የሕንፃ ንድፈ ሐሳብ አፍላቂዎችን የሕንፃ ሥራ ባለሙያዎችን የማያካትቱ አሰራሮችን በአዲሱ አዋጅ ላይ ተካተዋል" ሲል ገልጿል ፡፡ በሕንጻ ሥራ ላይ ተጠያቂነት የሚሰፍንበትን አካሄድ ያላከበረ ከመሆኑ በተጨማሪም፤ በአለም ዓቀፍ ካለው ልምድ አንፃር የሚጣረስ መሆኑም ገልጿል፡፡ በሂደት ላይ በነበረው የሕንጻ ሥራ አዋጅ ላይ የተሰተዋሉትን ቅሬታዎች ለምክር ቤቱ ቢያቀርቡም ተቀባይነት አለማግኘታቸውን ለአሐዱ የገለጹት የማህበሩ ፕሬዝዳንት ሐብታሙ ጌታቸው ናቸው። ልክ እንደ ሕክምና ባለሙያዎች ሙያ የሚዳኝበት ገለልተኛ ተቋም ሊቋቋም ይገባል እንጂ፤ በዘፈቀደ የሚታይበት አካሄድ የግንባታ ዘርፍን የሚጎዳው መሆኑን ገልጸዋል። ሌላኛው በአዋጁ ላይ ከተነሱት ቅሬታዎች መካከል ሕንጻ በሚገነባበት ወቅት በሌሎች ባለሙያዎች በሚፈጥሩት ስህተት የስነ ሕንጻ ንድፋ ወይንም የአርክቴክቸር ባለሙያዎችን ተጠያቂ የሚያደርግበትን አካሄድ አንዱ እንደሆነም ማሕበሩ ስሞታውን ለአሐዱ አሰምቷል። የማሕበሩ ፕሬዝዳንት አክለውም፤ የሙያ ደህንነትን ጉዳይ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መውደቁን የገለጹ ሲሆን፤ "በተጨማሪም አዋጁ በግንባታ ዘርፍ ላይ ለሚደርሱ ጥፋቶች ተጠያቂነትን የማያሰፍን ነው" ሲሉ ተችተዋል። አዋጁ ባለፈው ወር ለሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ለውይይት ቀርቦ የነበረ ቢሆንም፤ በርካታ አለመግባባቶች የተስተዋሉበት እንደነበር አሐዱ መዘገቡ ይታወሳል። የኢትዮጵያ ግንባታ ተቋራጮች ማሕበርን ጨምሮ የኢትዮጵያ አርክቴክቶች ማህበር በአዋጁ ላይ ከፍተኛ ትችት ከሰነዘሩ መካከል ይገኙበታል ነገር ግን እነዚህ ቅሬታዎች እና ትችቶች ምላሽ ሳያገኙ ምክር ቤቱ አዋጁ ተፈፃሚ እንዲሆን አፅድቆ ወደ የሚመለከተው አካል መምራቱ ነው የተገለጸው። Via~ አሐዱ ሬዲዮ

+2
👉የሪል እስቴት ልማት እና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ ረቂቅ አዋጅ ፀደቀ። 🏷የህ/ተ/ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ ረቂቅ አዋጁ ላይ ከተወያየ በኋላ ረቂቅ አዋጁ፤ አዋጅ ቁጥር 1357/2017 ሆኖ በሁለት ተቃውሞና በአንድ ድምፀ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምጽ አፅድቋል። 🚧ዛሬ በምክር ቤት የፀደቀው ረቂቅ አዋጅ የሪል ስቴት አልሚ ድርጅት ያለደንበኛው ፍላጎትና ፈቃድ አጠቃላይ ግንባታው ቢያንስ 80 በመቶ ያልተጠናቀቀ ቤት ለደንበኞች ሊያስተላልፍ እንደማይችል አስቀምጧል። ⏺በተጨማሪ በሪል ስቴት ልማት ላይ የሚሳተፍ ማንኛውም አካል የውሸት ማስታወቂያ ማስነገር እንደማይችልም አስቀምጧል። @etconp

የሪል_ስቴት_ልማት_እና_የማይንቀሳቀስ_ንብረት_ግብይትና_ግመታ_አዋጅ_1.pdf1.75 MB