cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

Ethio Mereja 2

Mereja Channel

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
200
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-27 kunlar
-830 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

Photo unavailableShow in Telegram
" የትግራይ ጡረተኞች ክፍያው እንዲፈፀምላቸው ተወስኗል " - ዶ/ር እዮብ ተካልኝ በትግራይ ክልል በነበረው ጦርነት ምክንያት የጡረታ ገንዘብ ያልተከፈላቸው ጡረተኞች፤ በፖለቲካ ውሳኔ መሰረት ደሞዝ እንዲከፈላቸው መወሰኑን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታና የጡረታ ፈንድ የቦርድ አባል ዶክተር እዮብ ተካልኝ ማሳወቃቸውን ብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል። ዶ/ር እዮብ ፤ የጡረታ መዋጮ ባልተሰበሰበበት ሁኔታ ጡረታ እንዲከፈል የሚፈቅድ አሰራር አለመኖሩን ጠቅሰው፤ ውሳኔው ፖለቲካዊ ስለመሆኑ ተናግረዋል። በዚህም ከፕሪቶሪያው ስምምነት በፊት ክፍያ ተቋረጦባቸው የነበሩ ጡረተኞች፤ በሚቀጥሉት ሳምንታት ክፍያ ይፈፀምላቸዋል ብለዋል። አሰራሩ በመንግስት ተቋማት እና በግል ድርጅቶች ይሰሩ የነበሩ ጡረተኞችን እንደሚመለከት ጠቁመዋል። ከትግራይ ጡረተኞች ክፍያ ጋር በተያያዘ ተደጋጋሚ ጥያቄ ሲነሳ እንደነበር ጠረተኞችም ሰላማዊ ሰልፍ እስከመውጣት መድረሳቸው ይታወሳል። ከቀናት በፊት ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ ከትግራይ ክልል ከመጡ የህዝብ ተወካዮች ጋር ባደረጉት ውይይት፤ የጡረተኞች የደሞዝ ክፍያ አልተፈጸመም የሚል ቅሬታ ቀርቦ ነበር። ጠ/ሚኒስትሩ ፤ " ከሚመለከታቸው የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ጋር ተነጋግሬ በአጭር ጊዜ ምላሽ ይሰጣል " የሚል ምላሽ ሰጥተው እንደነበር ይታወሳል። በተደረሰው ፖለቲካዊ ውሳኔ በጦርነቱ ምክንያት ያለተከፈለ የጡረተኞች ደሞዝ ተሰልቶ ይከፈላቸዋል ተብሏል።
Hammasini ko'rsatish...
የቱርክ የሀገር ውስጥ ሚንስቴር ምርመራ ጀመረ ! ትላንት ምሽት በቱርክ ሱፐር ሊግ ፌነርባቼ ትራብዞንስፖርን በሜዳው 3ለ2 ባሸነፈበት ጨዋታ የተፈጠረውን ክስተት ተከትሎ የቱርክ የሀገር ውስጥ ሚንስቴር ምርመራ መጀመሩን አሳውቋል። እስከ 87ኛው ደቂቃ ሁለት አቻ የነበሩት ሁለቱ ክለቦች ሚኪ ባትሹዋይ ለፌንርባቼ በመጨረሻ ደቂቃ የማሸነፊያ ግብ አስቆጥሮ ጨዋታውን ትራብዞንስፖር በሜዳው 3ለ2 ለመሸነፍ ተገዷል። ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ የባለሜዳው ክለብ ትራብዞንስፖር ደጋፊዎች ወደሜዳ ጥሰው በመግባት ደስታቸውን ሲገለፁ ከነበሩ የፌነርባቼ ተጨዋቾች ጋር ፀብ ውስጥ ገብተው ተስተውለዋል። ከምሽቱ ጨዋታ በኋላ የቱርክ የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር በሰጡት አስተያየት በጉዳዩ ላይ ምርመራ መጀመራቸውን ገልፀው እስካሁን አስራ ሁለት ግለሰቦችን መለየታቸውን እና ምርመራው መቀጠሉን አረጋግጠዋል። የቱርክ እግርኳስ ፌዴሬሽን በበኩሉ ባወጣው መግለጫ ድርጊቱን " ተቀባይነት የሌለው " ሲል ያወገዘ ሲሆን የድርጊቱ ተጠያቂ አካላት ላይም ጠንካራ ቅጣት እንደሚጥል አሳውቋል።
Hammasini ko'rsatish...
#CBE የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖ ምን አሉ ? - " ችግሩ የተከሰተው አንድ ሂሳብ ማስታረቅ ቅልጥፍና እንዲያመጣ ታስቦ የተሰራ የሲስተም ማሻሻያ ሲተገበር ስህተት በመፈጠሩ ነው። የተፈጠረው ስህተት ለሌቦች ቀዳዳ ከፍቶ ነበር። " - " የሲስተም ማሻሻያው የተተገበረው አርብ መጋቢት 6/2016 ዓ.ም ከምሽቱ 3 ሰዓት አካባቢ ነበር። ከሌሊቱ 8 ሰዓት አካባቢ ችግር እንዳለ ሊለይ ችሏል። ይህን ተከትሎም አንዳንድ የተጠረጠሩ አገልግሎቶች እንዲቋረጡ ተደርጓል። ይህም ሆኖ ሙሉ በሙሉ ችግሩ ስላልቆመ ሁሉም የዲጂታል ባንክ ስርዓቶች እንዲቋረጡ ተደርጎ ነበር። " - " ባንኩ ችግሩ በተከሰተበት ወቅት ከ490 ሺህ በላይ የገንዘብ ልውውጥ ተካሂዷን። ሌሊቱን ሙሉ ግብይት ሲፈጸምባቸው የነበረባቸው የባንክ ሂሳቦች በሙሉ እስኪጣራ ድረስ #እንዲታገድ ተደርጓል። " - " በቀጣይ ከፍተኛ እና ያልተገባ ግብይት የፈጸሙ አካላትን እየለየን ለህግ የማቅረብ ስራ ይሰራል። " - " የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በወንጀሉ ዋነኛ ተዋናይ መሆናቸው አሳዝኖናል። በየአካባቢው ያሉ የዲስትሪክት ኃፊዎች በየአካባው ከሚገኝ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመቀናጀት ተማሪዎች የወሰዱትን ገንዘብ #እንዲመልሱ እየተደረገ ነው። " - " ከተፈጠረው ችግር ጋር ተያይዞ አጠቃላይ የደረሰው ጉዳት ላይ ምርመራ እየተደረገ ነው። የችግሩ መሰረታዊ መንስዔ እና ያስከተለውን ጉዳትም ምርመራው ሲጠናቀቅ ይፋ ይደረጋል። " - " ባንኩ ላይ የደረሰው ጉዳት ባንኩ ካለው ሀበት እና አቅም አንጻር የጎላ ተጽእኖ የለውም፤ ከደንበኞች ሂሳብ ጋርም አይገናኝም። " #አልአይን
Hammasini ko'rsatish...
ዋጋቸው አልቀመስ እያለ የመጣው የመኮሮኒ እና የፓስታ ዋጋ በቅርቡ ሊቀንስ ይችላል ተባለ፡፡ ይህን የተናገረው የኢትዮጵያ የዱቄት አምራቾች ማህበር ነው፡፡ ዛሬ የዱቄት፣ የስንዴና የዘይት አምራቾች ከገንዘብ ሚኒስቴር እና ከሚመለከታቸው ጋር ሲመክሩ ውለዋል፡፡ አንድ ኩንታል ዱቄት ከ6,800 ወደ 5,800 ዝቅ እንዲል መደረጉና በኤክሳይዝ ታክስ ማሻሻያ እና ማስተካከያዎች በመደረጉ ዋጋው እንዲቀንስ ምክንያት ሆኗል ተብሏል፡፡ ማህበሩ ባደረገው ጥናት የዱቄትና የዱቄት ምርት ማቀነባበሪያዎች እንደ ፓስታና መኮሮኒ እንዲሁም ብስኩት ላይ ያለውን ቫት ወይም ተጨማሪ እሴት ታክስ አሁንም እንዲነሳ ጥያቄ ቀርቧል፡፡ የገንዘብ ሚኒስቴር ቀድሞውኑ በስንዴ ዱቄት ላይ 25 በመቶ ጥሎት የነበረውን ታክስ በማንሳቱ አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ የስንዴ ምርትና ውጤቶች  በገበያው ላይ ቀንሶ ታገኙታላችሁ ተብሏል፡፡ በሌላም በኩል ብስኩት ላይ ተጥሎ የቆየው ተጨማሪ እሴት ታክስ እንዲነሳ ተጠይቋል፡፡
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
የዓባይ ግድብ የኤሌክትሪክ ማመንጫው ግንባታ በሰባት ወራት ይጠናቀቃል ድልድዩና ሙሉ ሥራው በቀጣይ ዓመት ያልቃል የዓባይ ግድብ ፕሮጀክት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫው ግንባታው በሰባት ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ የፕሮጀክቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ አስታወቁ። በዓባይ ወንዝ ላይ የሚገነባው ድልድይና የፕሮጀክቱ ሙሉ ሥራ በቀጣይ ዓመት እንደሚጠናቀቅም ጠቁመዋል። የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ እንዳመለከቱት፤ ቀንና ሌሊት በሚሠሩ ባለሙያዎች አማካኝነት የግድቡ ግንባታ የሲቪል ሥራው 99 በመቶ ተጠናቋል። ዋናው የግድቡ ክፍል 107 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ የኮንክሪት ሙሌት እንደሚይዝ የተናገሩት ኢንጂነር ክፍሌ፤ ከዚህ ውስጥ አንድ በመቶው ሥራ ብቻ እንደሚቀር አስረድተዋል። Via:ኢ.ፕ.ድ
Hammasini ko'rsatish...
ሚስቱንለ26 ዓመታት የቤት እመቤት ያደረገው ባል 96 ሺህ ዶላር ካሳ እንዲከፍል ተፈረደበት ፍርድ ቤቱም በ26 ዓመታት ውስጥ ለደረሰባት ጉዳት 96 ሺህ ዶላር እንዲከፈላት ወስኖላታል በስፔኗ ፖንቴቬድራ ግዛት የሚኖሩ ባልና ሚስቶች ከሰሞኑ ወደ ፍርድ ቤት አምርተዋል፡፡ እነዚህ ባልና ሚስቶች በ1996 ተጋብተው በትዳር ይኖሩ ነበር የተባለ ሲሆን አሁን ላይ ትዳራቸው በፍቺ ተጠናቋል፡፡ ለ26 ዓመታት በቆዩበት የትዳር ህይወት አንድ ሴት ልጅ ያፈሩ ሲሆን በትዳር በቆዩባቸው ጊዜያት ሚስትየዋ ልጃቸውን እና ቤታቸውን በመንከባከብ አሳልፋለች ተብሏል፡፡ ይህ ትዳር በፍቺ መፍረሱን ተከትሎም ሚስትየዋ እኔ በትዳር ውስጥ በነበርንባቸው ጊዜያት ውስጥ የቤት ውስጥ ስራዎችን ብቻ እንድሰራ አድርጎኛል እሱ ግን ሲማር፣ ስራ ሲያማርጥ ቆይቷል አሁን ላይ እኔ ገቢ የለኝም ካሳ ያስፈልገኛል ስትል ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት እንደወሰደችው ተገልጿል፡፡ 270 ጥንዶችን ያጋቡት ስፔናዊ ለትዳር የወንዶች ቁመት ወሳኝ ነው ይላሉ 26 ዓመት ላገለገልኩበትም 130 ሺህ ዶላር ካሳ ያስፈልገኛል ያለችው ይህች ተከሳሽ በክርክራቸው መጨረሻም 96 ሺህ ዶላር ካሳ እንዲከፈላት ተወስኖላታል፡፡ ለሴት ልጃቸው የሚያስፈልገውን ወጪ በጋራ እንዲሸፍኑ፣ ባልየው ለቀድሞ ሚስቱ በየወሩ 381 ዶላር ለሶስት ዓመታት እንዲከፍል በፍርድ ቤት ተፈርዶበታል ሲል ኦዲቲ ሴንትራል ዘግቧል፡፡ በአውሮፓ በትዳር ጊዜያቸው የቤት እመቤት ሆነው ያሳለፍ የቀድሞ ሚስቶች ባሎቻቸውን በመክሰስ ላይ ሲሆኑ ከሁለት ዓመት በፊት በስፔን እና ፖርቹጋል ለቀረቡ ተመሳሳይ ክሶች እያንዳንዳቸው 204 ሺህ ዶላር 72 ሺህ ዶላር ካሳ እንዲከፈላቸው ተወስኖላቸዋል፡፡ Via @Addis_Reporter
Hammasini ko'rsatish...
#Update ንግድ ባንክ የተወሰደበትን ገንዘብ ለማስመለስ ዘመቻ ሊጀምር ነው‼️ - ቅዳሜ ዕለት በየኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲጂታል መዋቅር ላይ የተከሰተውን ግድፈት ተጠቅመው ገንዘብ የወስዱ አካላትን ለማደን #ግብረ_ኀይል መቋቋሙ ተሰምቷል። ከብሔራዊ ባንክና ንግድ ባንክ ባለሙያዎች እንዲሁም የፀጥታ አካላት የተካተቱበት ይህ ግብረ ኀይል በስድስት ሰዓታት ጊዜ ውስጥ ከባንኩ ያለ አግባብ ተወስዷል ያለውን ገንዘብ ለማመለስ ያለመ ነው። ባንኩ የተወሰደበትን የገንዘብ መጠን አላሳወቀም። ፎርቹን ጋዜጣ እንደዘገበው ግን ከ66 ሺህ በላይ ደንበኞች አካውንት በችግሩ መታወኩን፣ ቅዳሜ ለስድስት ሰዓታት በቆየው መታወክ 25 ሺ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር መደረጉን እንዲሁም ሁለት ነጥብ ስድስት ቢሊየን ብር ተንቀሳቅሷል። ባንኩ መረጃውን ማረጋገጥ አልፈለገም። አንዳንድ የትምህርት ተቋማት ከወዲሁ ገንዘብ ከክፍያ ማሽኖች የወሰዱና በህገወጥ ዝውውሩ የተሳተፉ ተማሪዎች ገንዘቡን ለባንኩ እንዲመልሱና ራሳቸውን ከህግ ተጠየቂነት እንዲያተርፉ የሚያሳስብ ጥሪ አድርገዋል። በባንኩ ላይ የደረሰው ችግር የሳይበር ጥቃት አለመሆኑንና ውስጣዊ ግድፈት መሆኑን ባንኩ አበክሮ ገልጿል። የባንኩ የውስጥ ምንጮች #ለዋዜማ እንደተናገሩት ግን ባለፈው ሳምንት ሐሙስ የተከናወነ አንድ መንግስታዊ የባንክ ክፍያ (ከአንድ መቶ ሚሊየን ብር ያላነሰ) ከአንድ በላይ የከፋይ ወገን በዲጂታል ፊርማ ሊያፀድቀው ሲገባ በአንድ ሰው ፈራሚነት ወደ ተከፋይ መተላለፉ የባንኩን ሀላፊዎች አስደንግጦ ነበር። አርብ ዕለት ችግሩን ለማወቅና ለመፍታት ሙከራ ሲደረግ መዋሉንና የቅዳሜ ሌሊቱ ቀውስ መከተሉን ሰምተናል። ባንኩ የሳይበር ጥቃት አለመፈፀሙን ይናገር እንጂ ክስተቱ በባንኩ ዲጂታል መዋቅር ላይ በውስጥ አዋቂ የተፈፀመ ጥቃት ሊሆን እንደሚችል የሳይበር ደህንነት ባለሙያዎች ይናገራሉ። 
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
ሊቨርፑል ለመጨረሻ ጊዜ በኤፍኤ ካፕ 4-3 የተሸነፉት በ1990 ነበረ ቢሆንም የዛን አመት የፕሪምየር ሊጉን ዋንጫ ማሸነፍ ችለው ነበር ! በዚህ አመት በኤፍኤ ካፕ 4-3 ተሸንፈው ከውድድሩ ተሰናብተዋል ፕሪሚየር ሊጉን ያሳኩ ይሆን? 👀
Hammasini ko'rsatish...
#ፑቲን ቭላድሚር ፑቲን ለቀጣይ 6 ዓመታት ሩስያን መምራት የሚያስችላቸውን የምርጫ ውጤት ማስመዝገባቸው ተነገረ። ሩስያን በፕሬዜዳንትነት እየመሩ የሚገኙት የቀድሞው የKGB ሰላይ ቭላድሚር ፑቲን በሀገራቸው የተካሄደውን የፕሬዜዳንታዊ ምርጫ በከፍተኛ ብልጫ ማሸነፋቸውን ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ባለፉት 3 ቀናት በመላ ሩስያ ህዝቡ ድምፅ ሲሰጥ ቆይቷል። የ71 ዓመቱ ፑቲን " ጠንካራ ተቀናቃኝ አልገጠማቸውም " በተባለው በዚህ ምርጫ ከ87% በላይ ድምፅ በማግኘት ሀገሪቱን በፕሬዜዳንትነት መምራት እንዲቀጥሉ የሚያስችላቸውን ውጤት እንዳገኙ ተገልጿል። ፑቲን ለቀጣይ 6 ዓመታት ሩስያን ይመራሉ። በጠቅላይ ሚኒስትርነት እንዲሁም በፕሬዜዳንትነት ረጅም ዓመታትን የሀገሪቱን ዋነኛ ስልጣን በመያዝ እየመሩ የሚገኙት ቭላድሚር ፑቲን ይኸኛው የ2024ቱ ምርጫ ለ5ኛ የስልጣን ዘመን ያሸነፉት ምርጫ ነው።
Hammasini ko'rsatish...
ቢሾፍቱ ሆራ ሀይቅ ዳርቻ የተከሰተ ድርጊት! ድርጊቱ የተፈፀመው የዛሬ ሁለት ሳምንት በቢሾፍቱ ሆራ ሀይቅ ዳርቻ ነው። በርካታ በጥቃቅን እና አነስተኛ የእደጥበብ ምርት እና ሽያጭ ላይ የተሰማሩ አብዛኞቹ ሴቶች የሆኑ ዜጎች በአንድ ጃማይካዊት አስተባባሪነት አነስተኛ ባዛር/የንግድ ትርኢት ያዘጋጃሉ። ከቀኑ 11 ሰአት ሲሆን የታጠቁ ሰዎች ይመጡና እቃዎቻቸውን አይሱዙ መኪና ላይ ይጭናሉ፣ ሰዎቹንም እየመቱ በጫካ ውስጥ ሁለት ሰአት የፈጀ የእግር ጉዞ አድርገው ወስደው ወደ "ካምፓቸው" አደረሷቸው። በዚህ ካምፓ ለአምስት ቀን ተይዘው ከቆዩ በኋላ ገንዘብ ይጠይቃሉ፣ ገንዘብ የለንም ሲሉ ግን መታወቂያዎቻቸውን በመቀበል በቀጥታ ወደ ባንኮች እየደወሉ ያላቸውን የገንዘብ መጠን አረጋገጡ፣ ከዛም በግድ ገንዘብ ትራንስፈር አስደረጓቸው። ይህን ከፈፀሙ በኋላ በአምስተኛው ቀን ከለሊቱ 8 ሰአት ለቀዋቸው በድጋሜ 2 ሰአት በእግራቸው ተጉዘው ቢሾፍቱ ተመልሰዋል። Via:EliasMeseret
Hammasini ko'rsatish...