uz
Feedback
ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ቅርንጫፍ

ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ቅርንጫፍ

Kanalga Telegram’da o‘tish
2 534
Obunachilar
+324 soatlar
+27 kunlar
+4230 kunlar
Postlar arxiv
ስፔን ቤልጂየምን በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍጻሜ አለፈች በዓለም ዋንጫው የሩብ ፍጻሜ መርሐ ግብር ስፔን ቤልጂየምን 2 ለ 1 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች። የስፔንን ግቦች ፋቢያን ሩዪዝ እና ሚኬ
+1
ስፔን ቤልጂየምን በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍጻሜ አለፈች በዓለም ዋንጫው የሩብ ፍጻሜ መርሐ ግብር ስፔን ቤልጂየምን 2 ለ 1 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች። የስፔንን ግቦች ፋቢያን ሩዪዝ እና ሚኬል ሞሪኖ አስቆጥረዋል። ስፔን በግማሽ ፍጻሜው ከፈረንሳይ ጋር ትገናኛለች፡፡ ትኩስ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ፋና ኤፍ ኤም 96.0 ቴሌግራም ፦ https://t.me/dessiefana ፊስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=1000799503520

አቶ ቸሩጌታ ገነነ የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ሆነው ተሾሙ። ደሴ-ሐምሌ 03/2018/ደሴ ፋና/ አቶ ቸሩጌታ ገነነ ወደ ሌላ የስራ ሃላፊነት ከተዛወሩት የቀድሞ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ
አቶ ቸሩጌታ ገነነ የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ሆነው ተሾሙ። ደሴ-ሐምሌ 03/2018/ደሴ ፋና/ አቶ ቸሩጌታ ገነነ ወደ ሌላ የስራ ሃላፊነት ከተዛወሩት የቀድሞ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አድማሱ ዳምጠው ጋር የስራ ርክክብ አድርገዋል። ላለፉት ሁለት አመታት የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ያገለገሉት አቶ ቸሩጌታ፣ በዛሬው እለት የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሸን ዋና ስራ አስፈሚነት ስራቸውን የጀመሩ ሲሆን፣ ከማኔጅመንት አባላት ጋርም ትውውቅ አድርገዋል። ትኩስ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ፋና ኤፍ ኤም 96.0 ቴሌግራም ፦ https://t.me/dessiefana ፊስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=10007995035

ሳዲዮ ማኔ ከብሔራዊ ቡድን ራሱን አገለለ ደሴ- ሐምሌ 03/2018/ደሴ ፋና/ የ34 ዓመቱ የቀድሞ የሊቨርፑል የአሁኑ የአል ናስር ተጫዋች ከሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ራሱን ማግለሉን ይፋ አዶርጓል። ማኔ
+2
ሳዲዮ ማኔ ከብሔራዊ ቡድን ራሱን አገለለ ደሴ- ሐምሌ 03/2018/ደሴ ፋና/ የ34 ዓመቱ የቀድሞ የሊቨርፑል የአሁኑ የአል ናስር ተጫዋች ከሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ራሱን ማግለሉን ይፋ አዶርጓል። ማኔ የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን በ2021 የአፍሪካ ዋንጫውን ማሳካት ከቻለው ስብስብ ውስጥ እንደነበር ይታወሳል። በብሔራዊ ቡድን ቆይታው 54 ግቦችን ሲያስቆጥር፤ 29 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን ለቡድን አጋሮቹ አመቻችቶ ሰቷል። በ2026 ዓለም ዋንጫ ሴኔጋል አስራ ስድስቱ ጥሎ ማለፍ ተጉዛ በቤልጂየም ተሸንፋ ከመድረኩ ተሰናብታለች። በግሉ ደግሞ ሁለት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ እና የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች በመባል ተመርጧል። "ለሀገሬ ሁሉንም ነገር ሰጥቻለሁ፤ በዚህም ደስተኛ ነኝ" ሲል ሳዲዮ ማኔ በማኅበራዊ ትስስር ገፁ መልዕክት አስተላልፏል። ትኩስ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ፋና ኤፍ ኤም 96.0 ቴሌግራም ፦ https://t.me/dessiefana ፊስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=10007995035

በሀርቡ ከተማ በሕገ-ወጥ የሺሻ ቤቶች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ ቀጥሏል። ደሴ- ሐምሌ 03/2018/ደሴ ፋና/ በደቡብ ወሎ ዞን በሀርቡ ከተማ አስተዳደር ውስጥ ወጣቶችን (ሴቶችንም ሆነ ወንዶች
+2
በሀርቡ ከተማ በሕገ-ወጥ የሺሻ ቤቶች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ ቀጥሏል። ደሴ- ሐምሌ 03/2018/ደሴ ፋና/ በደቡብ ወሎ ዞን በሀርቡ ከተማ አስተዳደር ውስጥ ወጣቶችን (ሴቶችንም ሆነ ወንዶችን) ለተለያዩ ሱሶች በመዳረግ ለጤና፣ ለማኅበራዊ ቀውስና ለጸጥታ ስጋት በሆኑ ሕገ-ወጥ የሺሻ ማጨሻ ቤቶች ላይ የተቀናጀ የቁጥጥር፣ የብርበራና የሕግ ማስከበር እርምጃ ተወሰደ። የከተማዋን ሰላምና የሕዝብ ደህንነት ለማረጋገጥ በተካሄደው የኦፕሬሽንና የፍተሻ ሥራ በሕገ-ወጥ መንገድ ለሺሻ ማስጨስ አገልግሎት ይውሉ የነበሩ 15 ቁሳቁሶችና መሣሪያዎች እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል። እነዚህ የተያዙ ሕገ-ወጥ መገልገያዎችም በሕግ አግባብ ሙሉ በሙሉ ከአገልግሎት ውጭ እንዲሆኑ ተደርጓል። ይህ የተወሰደው ቆራጥእርምጃ የነገ ሀገር ተረካቢ የሆኑ ወጣቶችን ከሱስ ተፅዕኖና ከሥነ-ልቦና መበላሸት ለመጠበቅ፣ የማኅበረሰቡን ሰላም፣ የፀጥታና አጠቃላይ ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ ለማረጋገጥ፣እንዲሁም በከተማዋ የሚታዩ ማናቸውንም ሕገ-ወጥ ድርጊቶች ቀድሞ ለመከላከል የተከናወነ ስኬታማ ሥራ ነው። የከተማዋ የጸጥታ መዋቅር እንዳስታወቀው፤ ማኅበረሰቡንና ወጣቱን ከእንዲህ ዓይነት የሱሰኝነት አደጋዎች ለመታደግ የተጀመረው ይኸው ተከታታይ የሕግ ማስከበርና የቁጥጥር ሥራ በቀጣይነትም በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል ይሆናል። "የወጣቶቻችንን ጤና እና የከተማችንን ፀጥታ በጋራ እንጠብቃለን!" ሀርቡ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት ትኩስ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ፋና ኤፍ ኤም 96.0 ቴሌግራም ፦ https://t.me/dessiefana ፊስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=10007995035

በደሴ የኤሌክትሪክ ትራንስፎርመር ላይ የስርቆት ወንጀል በመፈጸሙ በአከባቢው የኤሌክትሪክ መቋረጥ አጋጥሟል። ደሴ፤ ሀምሌ/03/18 (ፋና 96.0)፦ በደሴ ከተማ አራዳ ክፍለ ከተማ፣ መንበረ ፀሀይ ልዩ
+5
በደሴ የኤሌክትሪክ ትራንስፎርመር ላይ የስርቆት ወንጀል በመፈጸሙ በአከባቢው የኤሌክትሪክ  መቋረጥ አጋጥሟል። ደሴ፤ ሀምሌ/03/18 (ፋና 96.0)፦ በደሴ ከተማ አራዳ ክፍለ ከተማ፣ መንበረ ፀሀይ ልዩ ስሙ ምስራቅ በር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በ100 KVA የኤሌክትሪክ ትራንስፎርመር ላይ የስርቆት ወንጀል መፈጸሙን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ደሴ ሪጂን ዳይሬክተሩ አቶ ሀብቱ አበበ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ተናግረዋል። ​ዳይሬክተሩ እንዳሉት ሰርቆቱ ምሽትን አሰታኮ የተፈጸመ ሲሆን በዚህም በአከባቢው ነዋሪዎች ላይ ለጊዜው የኤሌክትሪክ አገልግሎት መቋረጡን ተናግረዋል። ​ዳይሬክተሩ እንዳሉት በመብራት ኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈጸሙ መሰል የስርቆት ወንጀሎች እንደ ሀገር የሚያደርሱት ጉዳት ከፍተኛ መሆኑን አንስተው ችግሩን ለመፍታት ማህበረሰቡ የጸጥታ አካሉ ሁሉም በጋራ ሊሰራ ይገባል ብለዋል። በደረሰው ስርቆት ምክንያት በወቅታዊ የገበያ ዋጋ ከ1 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ትራንሰፎርመር ከጥቅም ውጭ እንደሆነም ተነስቷል። ​ችግሩን ወደፊትም ለመከላከል ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በአከባቢው የሚገኙ የኤሌክትሪክ አገልግሎት መስጫ ተቋማትን መጠበቅ እንደሚገባው መልክት አሰተላልፈዋል። በከድር መሀመድ ትኩስ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ፋና ኤፍ ኤም 96.0 ቴሌግራም ፦ https://t.me/dessiefana [  ] ፊስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100079950

በተሁለደሬ ወረዳ ከ100 በላይ መምህራን ጥር ወር ላይ የደረጃ እድገት ብናገኝም እስካሁን አልተከፈለንም ሲሉ መምህራን ቅሬታ አቀረቡ። ደሴ- ሐምሌ 03/2018/ደሴ ፋና/ የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት
በተሁለደሬ ወረዳ ከ100 በላይ መምህራን ጥር ወር ላይ የደረጃ እድገት ብናገኝም እስካሁን አልተከፈለንም ሲሉ መምህራን ቅሬታ አቀረቡ። ደሴ- ሐምሌ 03/2018/ደሴ ፋና/ የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ጀማል ሰይድ የመምህራኑ ቅሬታ ትክክልና ተገቢ መሆኑን አምነዋል። የመምህራኑ የደረጃ እድገት የተፈቀደው ጥር ላይ በመሆኑ ወረዳው በአመቱ ከያዘው በጀት ጋር ሲነጻጸር የ800 ሺ ብር ልዩነት ስለመምጣቱም ተናግረዋል። እናም ወረዳው ካጋጠመው የጥሬ ገንዘብ እጥረት ጋር በተያያዘ ከጥር እስከ ሰኔ ባለው ጊዜ ጭማሬው ሳይከፈላቸው ቆይቷል። ትምህርት ጽ/ቤቱ ከመምህራን ጋር ያለውን ችግር በተመለከተ መግባቢት ላይ በመድረስ የመተማመኛ ደብዳቤ ተሰጥቷቸው እንደነበርም አስታውሰዋል ምክትል ኃላፊው። አሁን አዲስ በጀት አመት በመሆኑ ከሐምሌ ወር ጀምሮ አዲሱ ደመወዛቸው ተፈጻሚ እንደሚሆንና ያልተከፈላቸው የስድስት ወር ጭማሬ በአዲሱ በጀት ውስጥ ተካቶ በአጭር ጊዜ እንዲከፈላቸው ይደረጋል ብለዋል።     ሙሉቀን አበበ ትኩስ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ፋና ኤፍ ኤም 96.0 ቴሌግራም ፦ https://t.me/dessiefana ፊስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=10007995035

በደቡብ ወሎ ዞን ተንታ ወረዳ 01 ቀበሌ አባቦሩ የሚባል አካባቢ የውሃ ተቋም ተገንብቷል ቢባልም ወደ አገልግሎት አልገባም አሉ ነዋሪዎች። ደሴ- ሐምሌ 03/2018/ደሴ ፋና/ የወረዳው ውሃና ኢነርጂ
በደቡብ ወሎ ዞን ተንታ ወረዳ 01 ቀበሌ አባቦሩ የሚባል አካባቢ የውሃ ተቋም ተገንብቷል ቢባልም ወደ አገልግሎት አልገባም አሉ ነዋሪዎች። ደሴ- ሐምሌ 03/2018/ደሴ ፋና/ የወረዳው ውሃና ኢነርጂ ጽ/ቤት መሃንዲስ አቶ ሳሚል መኩሪያው በወረዳውና በሌሎች ተራድኦ ተቋማት ተገንብተው ወደ አገልግሎት ነፈየገቡ ተቋማት መኖራቸውን ተናግረዋል። የአባቦሩ ሜዳ ታዳጊ ከተማ ውሃ አቅርቦት በአባቦሩ ሜዳ የገጠር ውሃ አገልግሎት ድርጅት የሚመራ ቢሆንም እንደ ወረዳ ግን ወደ ስራ ያልገባ የውሃ ተቋም ስለመኖሩ መረጃ የለንም ብለዋል። የአባቦሩ ሜዳ የገጠር ውሃ አገልግሎት ድርጅት ስራ አስኪያጅ አቶ ሁሴን በቅርቡ የተረከብነው በቀይ መስቀል በኩል ተሰርቶ ርክክብ የተፈጸመበት የቦኖ ውሃ ወደ ስራ እንዲገባ አጥርና ጥበቃ እንዲሟላ ከማህበረሰቡ ጋር መግባባት ላይ ደርሰናል። ይህ እስከሚሟላ ግን ቦኖ ውሃው አገልግሎት እንዲሰጥ እየተደረገ ነው፤ ከዚህ ውጭ ግን ከስራ ውጭ የሆነ የውሃ ተቋም የለንም ብለዋል። ችግር አለ የሚል አካል ካለም መረጃ ቢሰጠን ለማስተካከል ዝግጁ ነን ብለዋል ስራ አስኪያጁ። ሙሉቀን አበበ ትኩስ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ፋና ኤፍ ኤም 96.0 ቴሌግራም ፦ https://t.me/dessiefana ፊስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=10007995035

የዩሪያ ማዳበሪያ ቀድሞ ብናገኝም ዳፕ ማዳበሪያ ግን አልደረሰንም አሉ በደሴ ዙሪያ ወረዳ የ09 ቀበሌ አርሶአደሮች። ደሴ- ሐምሌ 03/2018/ደሴ ፋና/ የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ደግሞ ቅሬታውን መሰረ
+1
የዩሪያ ማዳበሪያ ቀድሞ ብናገኝም ዳፕ ማዳበሪያ ግን አልደረሰንም አሉ በደሴ ዙሪያ ወረዳ የ09 ቀበሌ አርሶአደሮች። ደሴ- ሐምሌ 03/2018/ደሴ ፋና/ የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ደግሞ ቅሬታውን መሰረተ ቢስ ብሎታል። የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ጌታቸው እርጋታው በደሴ ዙሪያ ወረዳ ዘንድሮ የተሻለ የማዳበሪያ ስርጭት እንዳለ ተናግረዋል። ባለፋት ጊዜያት ወረዳው 19ሺ 725 ኩንታል ማዳበሪያ ለቀበሌዎች ያሰራጨ ሲሆን በዚህ ወቅት ከ500 ኩንቲል በላይ ማዳበሪያ በእጁ ላይ እንዳለ ተናግሯል። ስለዚህ አርሶአደሮች የሚበቃቸውን ያህል ማዳበሪያ መውሰድ እንደሚችሉም ኃላፊው አብራርተዋል። 09 ቀበሌ የግብርና ግብዓትን ከመጠቀም አንጻር ክፍተት ያለበት መሆኑን የተናገሩት አቶ ጌታቸው የዩሪያ ማዳበሪያ ከሚያስፈልገው መጠን የወሰደው 10 በመቶ ብቻ መሆኑንም አብራርተዋል። ሙሉቀን አበበ ትኩስ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ፋና ኤፍ ኤም 96.0 ቴሌግራም ፦ https://t.me/dessiefana ፊስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=10007995035

በአማራ ክልል ከአራት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊየን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ተሰራጭቷል። ደሴ- ሐምሌ 03/2018/ደሴ ፋና/ በአማራ ክልል ለመጪው መኸር ሰብል ልማት የሚውል ከአራት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊየን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ኃላፊ ደረጀ ማንደፍሮ እንደገለጹት፣ ለዘንድሮው የመኸር ሰብል ልማት ስምንት ነጥብ ስድስት ሚሊየን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ለማቅረብ ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል። እስካሁን ባለው ሒደትም ከአምስት ነጥብ አራት ሚሊየን ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ወደ አካባቢው የገባ ሲሆን ከዚህ ውስጥም አራት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊየን ኩንታል የሚሆነውን ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን ገልጸዋል። የማዳበሪያ ስርጭቱ ቀድመው ለሚዘሩ እንዲሁም በክረምት ለተሽከርካሪ አስቸጋሪ ለሆኑ አካባቢዎች ቅድሚያ በመስጠት መከናወኑን አስረድተዋል። ማዳበሪያንና ሌሎች የግብርና ግብአቶችን በወቅቱ ተደራሽ በማድረግ የክልሉን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ሰፊ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝም ነው ያስረዱቱ። የደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊ ደመቀ አድማሱ በበኩላቸው፣ በዞኑ ለዘንድሮው መኸር እርሻ ለማቅረብ ከታቀደው 644 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ 517 ሺህ ኩንታሉን ማስገባት ተችሏል ብለዋል። ከዚህ ውስጥም 387 ሺህ ኩንታል የሚሆነውን ለአርሶ አደሩ ማሰራጨት መቻሉን ገልጸዋል። በሰሜን ወሎ ዞን ለመኸር ምርቱ ለማቅረብ ከታቀደው 217 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ውሰጥ 160 ሺህ ኩንታል ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን የተናገሩት ደግሞ የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ ተገኝ አባተ ናቸው። በምርት ዘመኑ በተሻሻሉ ዘመናዊ አሰራሮች 231 ሺህ ሄክታር መሬት በማልማት ከ 7 ነጥብ አንድ ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱንም ተናግረዋል ሲል የዘገበው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ነው። ትኩስ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ፋና ኤፍ ኤም 96.0 ቴሌግራም ፦ https://t.me/dessiefana ፊስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=10007995035

አረንጓዴ አሻራ በደቡብ ወሎ ዞን አምሓራ ሳይንት ወረዳ ለአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚተከሉ ችግኞችን የማጓጓዝ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ። ትኩስ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ፋና ሚዲያ ኮርፖ
+4
አረንጓዴ አሻራ በደቡብ ወሎ ዞን አምሓራ ሳይንት ወረዳ ለአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚተከሉ ችግኞችን የማጓጓዝ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ። ትኩስ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ፋና ኤፍ ኤም 96.0 ቴሌግራም ፦ https://t.me/dessiefana ፊስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=10007995035

ስፔን ከቤልጂዬም፣ ተጠባቂው ጨዋታ… ደሴ- ሐምሌ 03/2018/ደሴ ፋና/ በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ጥምር አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው በ2026 የዓለም ዋንጫ ውድድር የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ ዛሬ
+2
ስፔን ከቤልጂዬም፣ ተጠባቂው ጨዋታ… ደሴ- ሐምሌ 03/2018/ደሴ ፋና/ በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ጥምር አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው በ2026 የዓለም ዋንጫ ውድድር የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ ዛሬም ቀጥሎ ይደረጋል፡፡ ምሽት 4 ሰዓት ላይ የአንድ ጊዜ የመድረኩ አሸናፊ ስፔን ከቤልጂዬም ጋር የምታደርገው ጨዋታ ይጠበቃል፡፡ ስፔን በ16ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ፖርቹጋልን እንዲሁም ተጋጣሚዋ ቤልጂዬም ደግሞ አዘጋጇን ሀገር አሜሪካን በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን መቀላቀላቸው ይታወሳል፡፡ የ2010 የመድረኩ ሻምፒዮን ስፔን በድጋሚ በመድረኩ ለመንገስ የምታደርገውን ጉዞ ለማጠናከር ወደ ሜዳ የምትገባ ይሆናል፡፡ በፈረንጆቹ 2018 ወርቃማ ትውልዷን ሳትጠቀም የቀረችው ቤልጂዬም በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ እስከ የት ድረስ ትጓዛለች የሚለው ተጠባቂ ነው፡፡ በስፔን ብሔራዊ ቡድን በኩል በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ 4 ግቦችን ያስቆጠረው ሚኬል ኦያርዛባል እና ወጣቱ ኮከብ ላሚን ያማል በዛሬው ጨዋታ ይጠበቃሉ፡፡ የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች አሸናፊ በግማሽ ፍጻሜው ከፈረንሳይ ጋር የሚጫወት ይሆናል፡፡ ትኩስ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ፋና ኤፍ ኤም 96.0 ቴሌግራም ፦ https://t.me/dessiefana ፊስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=10007995035

በደሴ ከተማ ባለፉት ዓመታት የሕዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል ደሴ- ሐምሌ 03/2018/ደሴ ፋና/ በደሴ ከተማ ባለፉት አምስት ዓመታት በማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች የሕዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን የከተማዋ ነዋሪዎች ገለፁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰሞኑን መስጠታቸው ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ማብራሪያ ላይ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በተለያዩ ዘርፎች የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በተደረገው ጥረት አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። ይህንኑ ማብራሪያ አስመልክቶ አስተያየታቸውን የሰጡ ነዋሪዎች እንደገለፁት፤ በከተማው ባለፉት አምስት ዓመታት በማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች የሕዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል። ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል የሀገር ሽማግሌ የሆኑት ጫኔ መንገሻ በሰጡት አስተያየት፤ ባለፉት ዓመታት በደሴ ከተማ እየተገነቡ ያሉ የመሠረተ ልማት ሥራዎች ከተማዋን ያዘመኑ ናቸው ብለዋል። በከተማዋ የተከናወኑት የኮሪደር ልማት፣ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ማሻሻል እንዲሁም በቱሪዝም፣ በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ትውልድ ተሻጋሪ መሆናቸውን ገልጸዋል። አቶ ዘሪሁን ማንደፍሮ እና ወይዘሮ ፈረጃ ሱሌማን በበኩላቸው፤ ባለፉት አምስት ዓመታት በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች በተከናወኑ ውጤታማ ተግባራት ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአካባቢያቸው የተገነባው የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት የአካባቢውን ቱሪዝም በማነቃቃት ለደሴ ከተማና ለአካባቢው ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠሩን፣ የአገልግሎት ዘርፉን ማሳደጉን በምሳሌነት አንስተዋል። በተለይ በጤናው ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት የእናቶችን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን ጠቁመው፤ የኮሪደር ልማት፣ የመኖሪያ ቤት ግንባታ መጀመርና ሌሎች የልማት ሥራዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው ብለዋል። ነዋሪዎቹ ከመንግሥት ጎን በመሰለፍ የተጀመረው ልማት ዳር እንዲደርስ የበኩላቸውን እንደሚወጡም ገልጸዋል። አማራ ኮምንኬሽን ትኩስ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ፋና ኤፍ ኤም 96.0 ቴሌግራም ፦ https://t.me/dessiefana ፊስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=10007995035

ፈረንሳይ ሞሮኮን አሸንፋ ለግማሽ ፍፃሜ አለፈች። ደሴ- ሐምሌ 02/2018/ደሴ ፋና/ በ23ኛው የዓለም ዋንጫ በፈረንሳይ እና በሞሮኮ መካከል የተደረገው የመጀመሪያው የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ፤ በፈረንሳይ 2
+2
ፈረንሳይ ሞሮኮን አሸንፋ ለግማሽ ፍፃሜ አለፈች። ደሴ- ሐምሌ 02/2018/ደሴ ፋና/ በ23ኛው የዓለም ዋንጫ በፈረንሳይ እና በሞሮኮ መካከል የተደረገው የመጀመሪያው የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ፤ በፈረንሳይ 2 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቅቋል። የፈረንሳይን የማሸነፊያ ግቦች 60ኛው ደቂቃ ላይ ኪሊያን ምባፔ እንዲሁም 66ኛው ደቂቃ ላይ ኡስማን ዴምቤሌ አስቆጥረዋል። ኪሊያን ምባፔ በዓለም ዋንጫ ተሳትፎ ታሪኩ ያስቆጠራቸው ግቦች 20 የደረሱ ሲሆን፤ 29ኛው ደቂቃ ላይ ፈረንሳይ አግኝታው የነበረውን ፍፁም ቅጣት ምት ሳይጠቀምበት ቀርቷል። ፈረንሳይ በግማሽ ፍፃሜው ከስፔን እና ቤልጂየም አሸናፊ ጋር ትጫወታለች። ትኩስ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ፋና ኤፍ ኤም 96.0 ቴሌግራም ፦ https://t.me/dessiefana ፊስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=10007995035

የባሕር በር ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ… ደሴ- ሐምሌ 02/2018/ደሴ ፋና/ የባሕር በር ባለቤትነት ሀገራዊ ደህንነትን ለመጠበቅ፣ ኢኮኖሚን ለማሳደግ እና ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ ጉልህ ሚና ይጫወታል፡፡ የባሕር በር አለመኖር የሀገርን የንግድ እንቅስቃሴ በመገደብ ለከፍተኛ ወጪ የሚዳርግ ሲሆን፤ ዓለም አቀፍ የንግድ እንቅስቃሴንም በሌሎች ሀገራት መልካም ፈቃድ ላይ የተመሰረተ እንዲሆን ያደርጋል፡፡ በአንጻሩ የባህር በር ባለቤት የሆኑ ሀገራት የንግድ፣ ጂኦፖለቲካዊና ቀጣናዊ ጥቅምን ለማስከበር በነጻነት የሚንቀሳቀሱ ሲሆን፤ ይህም በአካባቢያቸው ላይ የሚኖራቸውን የኃይል ሚዛን ለማስጠበቅ ይረዳል፡፡ የባሕር በር ባለቤትነት በሌላ ሀገር ላይ የሚኖር ጥገኝነትን በማስቀረት ቀጣናዊ ተጽዕኖን በመፍጠር ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ ያግዛል፡፡ ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ላይ የነበራት ተጽዕኖ እንዲሁም የወደብ ባለቤትነት የቅርብ ጊዜ ታሪክ ነው፡፡ በታሪክ አጋጣሚ ልክ ባልነበረ ፖለቲካዊ ውሳኔ የባህር በሯን ካጣች በኋላ የውጭ የንግድ እንቅስቃሴዋ በጎረቤት ሀገራት ወደቦች ላይ የተመሰረተ እንዲሆን አድርጓል፡፡ ይህም በየዓመቱ ቢሊየን ዶላሮችን ወጪ እንድታወጣ እያደረጋት ይገኛል፡፡ የ130 ሚሊየን ህዝብ ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ የባሕር በር አልባ በመሆኗ ብሔራዊ ጥቅሟ በጠላት ሴራ ውስጥ እየወደቀ ብዙ ፈተናዎችን ለማስተናገድ ብትገደድም በልጆቿ ትግል ስትሻገራቸው ቆይታለች፡፡ ኢትዮጵያ የምትገኝበት የቀይ ባሕር አካባቢ በዓለም የንግድና የፖለቲካ አሰላለፍ ውስጥ ወሳኝ ቀጣና ነው፡፡ በዚህም የራሷ የባህር በር ቢኖራት በአካባቢው የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የደህንነት ጉዳዮች ላይ ተሰሚና ተጽዕኖ ፈጣሪ ሀገር ያደርጋታል፡፡ ኢትዮጵያ በየትኛውም ጥያቄዎቿ ብሔራዊ ጥቅሞቿን የሚያስከብርና በጋራ የመልማትን እሳቤ የያዘ በሰላማዊ ውይይት የሚመጣ መልስን ትሻለች፡፡ ኢትዮጵያ የምትጠይቀው በታሪክም በሕግም የራሷ የነበረውን በአንድ ወቅት በግፍ የተነጠቀችውን አካሏን ነው፡፡ የኢትዮጵያ የባሕር በር የማግኘት ጥያቄ የ130 ሚሊየን ሕዝብ የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚወስንበት፣ እንደ ሀገር የማደግ፣ የመበልጸግ፣ የሕልውና እና ብሔራዊ ጥቅምን የማስከበር የፍትሀዊነት ጥያቄ ነው። በመልካም ፈቃዱ ትኩስ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ፋና ኤፍ ኤም 96.0 ቴሌግራም ፦ https://t.me/dessiefana ፊስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=10007995035

የቅመማ ውህደቱ የማታወቅ እና የምርት አገልግሎት ማብቂያ ጊዜውን የማይገልፅ ዱባይ የተባለ ፈሳሽ የጁስ መሳይ መጠጥን በህገወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ መያዙን ፖሊስ ገለፀ። ደሴ- ሐምሌ 02/2018/ደሴ
+4
የቅመማ ውህደቱ የማታወቅ እና የምርት አገልግሎት ማብቂያ ጊዜውን የማይገልፅ ዱባይ የተባለ ፈሳሽ የጁስ መሳይ መጠጥን በህገወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ መያዙን ፖሊስ ገለፀ። ደሴ- ሐምሌ 02/2018/ደሴ ፋና/በኮምቦልቻ ከተማ የአቢሻገር ክፍለ ከተማ ፖሊስ የቅመማ ውህደት ፣ የምርት ቀን እና የአገልግሎት ማብቂያ ዘመኑን የማይገልፅ ለጤና ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርስ የሚችል ፈሳሽ መጠጥ ውህድ ፖሊስ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአቢሻአገር ክፍለ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ አዛዥ ኢንስፔክተር ሁሴን መብራቱ ገለፁ። ይህ ለሰው ልጅ ጤና አደገኛ የሆነ ውህድ በሰሜን ወሎ ዞን መርሳ ከተማ ወጣ ብሎ ልዩ ቦታው ገንቦ በር አካባቢ እንደሚመረት ኢንስፔክተር ሁሴን ውህዱን ጭነው ሲያዘዋወሩ የነበሩ ተጠርጣሪወችን ዋቢ አድርገው ጠቅሰዋል። ይሄ አደገኛ ውህድ በተለያዩ አካባቢዎች በስፋት እንደተሰራጨ እና ኮምቦልቻ ከተማም 406 ደርዘን ወይም በቁጥር ከ4870 በላይ በክምችት እንደተገኘም አስረድተዋል። ኢንስፔክተር ሁሴን መብራቱ በመጨረሻም ከዚህ በፊት ማር እና ሌሎች ፈሳሽ መጠጦችን በቁጥጥር ስር በማዋል ህጋዊ እርምጃ መወሰዳቸውን አስታውሰው ህብረተሰቡ የዚህን እና መሰል አደገኛ የመጠጥ ምርቶችን በመለየት እና በማረጋገጥ መጠቀም እንዳለበት አስረድተዋል። ኮምቦልቻ ከተማ ፖሊስ ትኩስ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ፋና ኤፍ ኤም 96.0 ቴሌግራም ፦ https://t.me/dessiefana ፊስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=10007995035

በሐይቅ ከተማ ከፒያሳ እስከ ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት የሚዘረጋው የአስፓልት ንጣፍ ሥራ በተጠናከረ ፍጥነትና ጥራት እየተከናወነ ነው። ደሴ- ሐምሌ 02/2018/ደሴ ፋና/ በደቡብ ወሎ ዞን የሐይቅ ከተማን ገ
+4
በሐይቅ ከተማ ከፒያሳ እስከ ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት የሚዘረጋው የአስፓልት ንጣፍ ሥራ በተጠናከረ ፍጥነትና ጥራት እየተከናወነ ነው። ደሴ- ሐምሌ 02/2018/ደሴ ፋና/ በደቡብ ወሎ ዞን የሐይቅ ከተማን ገጽታ ለመቀየርና ለትውልድ የምትመጥን ስልጡን ከተማ ለመፍጠር የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ ከከተማዋ መካከለኛ ክፍል (ፒያሳ) እስከ ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት እየተገነባ የሚገኘው የአስፓልት መንገድ ንጣፍ ሥራ በከፍተኛ ጥራትና ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል። የከተማ አስተዳደሩ የከተማዋን ውበትና ፅዳት ለመጠበቅ፣ ቁጥቋጦዎችን በመግለጥና አቧራን በማራገፍ ዘመናዊ መሠረተ ልማትን ለመዘርጋት ሌት ተቀን እየሠራ ይገኛል። በአሁኑ ወቅትም ይህ ለቱሪዝምና ለሕዝብ ትስስር ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው የፒያሳ - ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት መንገድ የአስፓልት ንጣፍ ሥራው በተሻለ ደረጃ ላይ ደርሷል። ከድር መሐመድ ትኩስ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ፋና ኤፍ ኤም 96.0 ቴሌግራም ፦ https://t.me/dessiefana ፊስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=10007995035

በሰሜን ወሎ ዞን የሃራ ከተማ የረጅም ጊዜ የውሃ ችግርን የሚፈታው ጥልቅ የውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ ተገለጸ። ‎ ደሴ- ሐምሌ 02/2018/ደሴ ፋና/ ‎በአማራ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ድጋፍ ለሃራ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት በአላውሃ ሩፈንቲ ላይ ሲካሄድ የነበረው የጥልቅ ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ በተሳካ ሁኔታ እየተጠናቀቀ ነው። ‎ ‎የቁፋሮ ስራው በ250 ሜትር ጥልቀት ላይ የተከናወነ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የውሃ ማፍሠሥ እና የውሃ ማጥራት ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል። ‎ ‎የሃራ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ስራ አስኪያጅ አቶ ሰኢድ ኢብራሂም ማህበረሰቡ ለረጅም ጊዜ የውሃ ችግር እንዲፈታላቸው በተደጋጋሚ ጥያቄ ሲያቀርቡ የቆዩ መሆኑን ገልፀዋል። አሁን የተገኘው የውሃ ምንጭ ግፊት እጅግ ከፍተኛ በመሆኑ፣ የነዋሪዎችን ጥያቄ ከመፍታት ባሻገር የከተማዋን ቀጣይ እድገት ታሳቢ ያደረገ ዘላቂ መፍትሄ መሆኑን አስረድተዋል። ‎ ‎ቀጣይ የሚከናወኑ የሲቪል ስራዎች (Civil works) እና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራዎችን በተሳካ ሁኔታ ለማጠናቀቅ መንግስት እና ህዝብ በጋራ በመቆም የተቀናጀ ጥረት እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርበዋል። ‎ ‎ይህ ታሪካዊ ስኬት እንዲመዘገብ ግንባር ቀደም በመሆን በባለቤትነት ለሰሩት ለአማራ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ አመራሮችና ባለሙያዎች፣ ለሰሜን ወሎ ዞን ውሃና ኢነርጂ መምሪያ፣ ለጉባላፍቶ ወረዳ ውሃ ጽ/ቤት እንዲሁም ለሃራ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ስራ አመራር ቦርድ በሃራ ማህበረሰብ እና በድርጅቱ ስም ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ‎ መረጃው የሰሜን ወሎ ዞን ኮሙኒኬሽን ነው። ትኩስ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ፋና ኤፍ ኤም 96.0 ቴሌግራም ፦ https://t.me/dessiefana ፊስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=10007995035