uz
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Assaye Derbie analitikasi

Assaye Derbie (@asayede) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 14 335 obunachidan iborat bo'lib, Bloglar toifasida 2 651-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 347-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 14 335 obunachiga ega bo‘ldi.

26 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -104 ga, so‘nggi 24 soatda esa -8 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 35.99% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 12.61% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 5 158 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 808 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 30 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Kanal uchun tavsif kiritilmagan.

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 27 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Bloglar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

14 335
Obunachilar
-824 soatlar
-327 kunlar
-10430 kunlar
Postlar arxiv
የአማራ አክቲቪስቶች ከሌላው በተለየ መልኩ መናከስ የሚያበዙት ለምን እንደሆነ ማወቅ ከፈለግክ በአንድ ሳምንት ውስጥ ብቻ በአማራዎች ላይ የተፈጸመውን ግፍ ልንገርህ! አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ➔ከ280 ሺ የሚበልጡ አማራዎች ከኦሮሚያና ቤኒሻንጉል ክልል ተፈናቅሉ። ➔የአማራ ተወላጅ የሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊሶች ከሥራቸው ተሰናበቱ። (ምንጭ ባልደራስ!) ➔ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአማራ አክቲቪስቶችና ፖለቲከኞች ብልጽግናን መተቸታቸውን ካላቆሙ... የአማራ ሕዝብ እፎይታ እንደማያገኝ የሚገልጽ ንግግር አደረጉ። ➔በአዲስ አበባ ከተማ በወጣው የፖሊሶች ቅጥር ላይ የአዲስ አበባ ልጆችና አማራዎች እንዳይሳተፉ ክልሎች ወጣቶችን እንዲመለምሉ ተደረገ ። ➔የአማራ ተወላጅ የሆኑ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ውጤት የማምታታት ሥራ ተሰራ። ➔በትናንትናው እለት በመተሀራ ከተማ 11 አማራዎች ሲገደሉ ከ20 በላይ ቆስለው አዳማ ሆስፒታል ገቡ። በርካቶች ደግሞ የገቡበት ጠፋ። ➔ይሄን ሁሉ ግፍ በማየት ድርጅታችንን ስንወቅስ አብን "ድምፄን አጥፍቼ ውስጥ ውስጡን እየሠራሁ ነው" በማለት መንጋውን ሲቆጣ እንደ ኢሳት ያሉ ሚዲያዎች ደግሞ የአማራ አክቲቪስቶችን ተናካሾች አድርገው ሲወርፉ ከረሙ! .....እናስ ከጫፍ እስከ ጫፍ በመንግሥታዊ ጥቃት የሚንገበገብ ሕዝብ ያለው አክቲቪስት "እንቢ አልገዛም" የሚል ሕዝብ ባለመፍጠሩ እንጂ መንግሥትን በመተቸቱ እንዴት ሊወቀስ ይችላል? Share

በመተሀራ ከተማ የታጠቁ ሃይሎች በፈጸሙት ጥቃት 11 የአማራ ንጹሐን ተገድለው ሲያድሩ፣ ከሃያ በላይ ደግሞ በጥይት ቆስለው አዳማ ሪፈራል ሆስፒታል ገብተዋል። በመቶዎች የሚቆጠሩ አማራዎችም የገቡበት ጠፍቷል።

አገርን የማፍረስና ዜጎችን የማቃወስ ሕልም ይዞ ወደ ሥልጣን በመጣ መንግሥት ዶክተሮች እና ኢንጂነሮች ፈላጊ አጥተው በሥራ እጦት ሲንገበገቡ አይተናል። በዚህም የተነሳ "ስታድጉ ምን መሆን ትፈልጋላችሁ
አገርን የማፍረስና ዜጎችን የማቃወስ ሕልም ይዞ ወደ ሥልጣን በመጣ መንግሥት ዶክተሮች እና ኢንጂነሮች ፈላጊ አጥተው በሥራ እጦት ሲንገበገቡ አይተናል። በዚህም የተነሳ "ስታድጉ ምን መሆን ትፈልጋላችሁ?" ለሚለው ጥያቄ እንደ ድሮው "ዶክተርና ኢንጂነር" በማለት ፈንታ "አመራር" የሚል መልስ የሚሰጡ ተማሪዎች ተበራክተዋል። እናም... ከሥራ መቀጠሪያ መስፈርቱ ውስጥ ብቃትን እና ውጤትን ሰርዞ "ቋንቋን" የተካው ይህ እኩይ ቡድን አሁን ደግሞ ወደ ዩኒቨርስቲ የመግቢያ መስፈርቱ ዘውግ ይሆን ዘንድ ወስኖ በኩራዝ ጭስ እየታጠኑ ሲያጠኑ የከረሙ ተማሪዎችን ተስፋ ለማደንገዝ ሲሞክር... በቸልታ ልናየው አይገባም። Share

የትናንት አጀንዳቸው "የአብን አመራሮችን የሚተቸው መንጋ መኮርኮም አለበት" የሚል ነበር። የነገ ርዕሳቸው ደግሞ "የተማሪዎች ውጤት ላይ ሸፍጥ ተሰርቷል በሚል ምክንያት የትምህርት ሚኒስትሩን የሚወቅሰ
የትናንት አጀንዳቸው "የአብን አመራሮችን የሚተቸው መንጋ መኮርኮም አለበት" የሚል ነበር። የነገ ርዕሳቸው ደግሞ "የተማሪዎች ውጤት ላይ ሸፍጥ ተሰርቷል በሚል ምክንያት የትምህርት ሚኒስትሩን የሚወቅሰው መንጋ መመታት ይገባዋል" የሚል ይሆናል። አገርን፣ ትውልድን፣ ሕዝብን፣ ፍትሕን፣ ዲሞክራሲን... ገድለው ጥቂት ባለሥልጣናትን ለመታደግ የሚንደፋደፉ ጉዶች‼️ በአማራ ክስመትና በኢትዮጵያ ውድቀት ላይ የብልጽግናን ሕያውነት ለማረጋገጥ የሚጥሩ ገራሚ ሰዎች‼️

"የማትሪክ ውጤትህ 162 ነው" የተባለ የመርጦ ለማሪያም ተማሪ ቅሬታ አቅርቦ ውጤቱ ሲጣራ ስንት አምጥቶ ቢሰቅል ጥሩ ነው? 647 😂 እኔ እምለው ግን የማትሪክ ውጤት እንደ ኮንዶሚኒየም ቤት በዘፈቀደ የሚሰጥ ሆኗል እንዴ?

ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ‹‹ጩኸታችሁን በማቆም የአማራ ሕዝብ እፎይታ እንዲገኝ አድርጉት›› የሚል መልዕክት ለአማራ አክቲቪስቶችና ፖለቲከኞች ማስተላለፍዎን ሰማሁ፡፡ እናም ለአፍታ ያክል አማራ ሆነው የሕዝቡን ሰቆቃ ያዳምጡበት ዘንድ ጆሮየን አውሸዎት፣ አንደበትዎን በመውሰድ እንዲህ ልልዎ ወደድኩ፡፡ ውሃን የሚያስጮኸው በውስጡ ያለው ድንጋይ ነው፡፡ ከጥቃታችን ጋር ሲነጻጸር ጩኸታችን ኢምንት ነው፡፡ ከፈሰሰው ደማችን ጋር ሲወዳደር እንባችን እና ለቅሷችን ምንም ነው፡፡ . ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፡- እኛ እኮ የምናለቅሰው የእርስዎ መንግሥት ሊጠብቃቸው ቀርቶ አጀንዳ ሊያደርጋቸው ያልቻሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ትኩስ አስከሬኖችን ታቅፈን እንጂ ከመቶ ዓመት በፊት የተፈጸመብንን ግፍ እያስታወሰን አይደለም፡፡ እኛ እኮ ስንጮህ የነበረው ‹‹ኖ ሞር›› እያልን እንጂ የሆነን ብሔር ‹‹ዳውን ዳውን›› እያልን አይደለም፡፡ ለመሆኑ ኦነግ ሸኔ የአማራ ንጹሐንን የሚጨፈጭፈው የእኛ ጩኸት እያበሳጨው ነው እንዴ? ትሕነግ ከአማራም አልፎ አፋርን የሚያወድመው የእኛ ድምጽ ደሙን እያፈላው ነው እንዴ? ሕዝቡን ከአደጋ ሊታደግ የተደራጀው ፋኖ ኢ-መደበኛ ሃይል ተብሎ በየስፍራው የሚሳደደውና የሚገደለው በአማራ አክቲቪስቶች ጩኸት የተነሳ ነው እንዴ? በዚያ ላይ ደግሞ የአማራ እሪታና ኡኡታ የእርስዎን ጆሮ አግኝቶ የሚያውቀው መቼ ነው? አሸባሪው ሃይል ጣርማ በር ደርሶ አራት ኪሎ ላይ መዛት እስኪጀምር ድረስ የአማራ እናቶች ዋይታ ሊያሳዝንዎት ይቅርና የፓርቲዎን ድግስና ፌሽታ ማደብዘዝ ችሎ ነበር እንዴ? እናስ በሰላማዊ መልኩ መኖር ሲጀምር የመንግሥት አመራሮች ባደራጃቿውና ይሁንታ በቸሯቸው አሸባሪዎች ጥቃት የሚንገበገበውን፣ ተደራጅቶ እራሱን መካለከል ሲጀምር ደግሞ ኢ-መደበኛ ተብሎ በመንግሥት ጥይት የሚደበደበውን ሕዝብ ችግር በመፍታት ፈንታ የጥቃቱን ምክንያት ከአክቲቪስቶች ጩኸት ጋር ማቆራኘት ለምን ፈለጉ? አንድ ነገር ልንገርዎ… በየትኛውም መልኩ ቢሆን የአማራ አክቲቪስቶች እና ፖለቲከኞች በእርስዎ አንደበት ሊሞገሱ እንጂ ሊወቀሱ የተገባ አይደለም፡፡ የአገሪቱ ጦር በከሃዲያን ብረት ሁለት ጊዜ ሲመታ ‹‹መከላከያን ይቀላቀሉ›› እያሉ ሲቀሰቅሱ፣ የዲጂታል ወያኔዎችን የሳይበር ዘመቻ ሲደመስሱ፣ ከወገናቸው ጥቃት ይልቅ የአገራቸውን ቀጣይነት አስቀድመው 'ኖ ሞር' እያሉ ሲጮሁና ዶላር ሲለግሱ፣ የፓርቲዎ ደጋፊ ሆነው የእራሳቸውን ፓርቲ ሲያፈርሱ…. የከረሙ የአማራ አክቲቪስቶችንም ሆነ ፖለቲከኞችን መውቀስ የሚችለው ጌታቸው ረዳ እንጂ እርስዎ አልነበሩም፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን አብዛኛው አማራ በእርስዎ መንግሥት ተስፋ መቁረጡን ሲረዱ የህውሓትን ፍረጃ ተረክበው የአማራ ልሂቃንን እና ባለሃብትን ለመወንጀል በቁ፡፡ በመንግሥት ቁማርተኝነት እና ዳተኝነት መቀመጫ ያጣውን ሕዝብ በሶሻል ሚዲያ ጩኸት ሊያሟክኩት ከጀሉ፡፡ የሕዝብ ሚዲያዎችን አፍነው፣ ተጠያቂነትን አምክነው፣ በሕግ ፈንታ በሃይል የምትተዳደር አገር እውን አድርገው፣ የአማራን እልቂት ከማሳ ጉብኝት ያነሰ አጀንዳ አድርገው…. ወገኖቻችንን ሰለባ ሲያደርጉ መክረምዎ አንሶ ‹‹ድምጻችሁን በማጥፋት አማራን ታደጉት›› የሚል ጥሪ አቀረቡልን፡፡ ይሄም በሌላ ቋንቋ ሲገለጽ መንግሥቴን መቃወም እስኪቆም ድረስ አማራን ማውደም ይቀጥላል›› እንደማለት ነው፡፡ እኔ እምልዎት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፡- ‹‹ዳውን ዳውን ነፍጠኛ›› የሚለውን የአዲስ አበባን ዩኒቨርስቲ ጩኸት በፈገግታ እያዳመጡ ፍትሕን በሚጠይቁ ድምጾች የሚቆጡ እስከ መቼ ድረስ ነው? የአማራን እልቂት እንዳልሰማ እያለፉ ጩኸቱን የሚያወግዙት፣ የሚፈስሰውን ደም ችላ ብለው እንባን የሚከለክሉት ይሄን ሕዝብ ምን ያህል ቢጠሉት ነው? ፋኖን እየበተኑ ከወሬ ያለፈ ተግባር እንፈጽም ዘንድ የሚመክሩን፣ በዞን የሚሸነሽኑ አመራሮች እየሾሙ አንድነታችንን እንዲናጠናክር የሚነግሩን፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አርሶ አደሮችን የምታፈናቅል አገር ከፈጠሩ በኋላ ሕዝቡ የተራበው በስንፍናው የተነሳ መሆኑን የሚያስረዱን፣ በሕገ መንግሥትና በመንግሥት ታዛ ስር በተጠለሉ ሃይሎች የሚፈጸመው ጥቃት ዋነኛ ምንጩ ጩኸት መሆኑን የሚነግሩን የማሰብ አቅማችን ምን ያህል ወርዶ ቢታይዎት ነው?›› ብዬ ከጠየቅኩ በኋላ የእራስዎን ምክር ወደ እርስዎ በመመለስ የህውሓትን ያህል የእፎይታ ጊዜ ይሰጡን ዘንድ እለምንዎታለሁ፡፡

የመንጋ ትርጉም ላልገባቸው አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ በጦርነቱ ወቅት የአብን አመራሮች ሕዝብን ሲያስተባብሩ ጠሚው ደግሞ ጦሩን ሲመሩ ነበር፡፡ እኛም ከግል አቋም ይልቅ የወገንን ጥቅም በማስቀደም ከአብን በተጨማሪ የብልጽግና ደጋፊ ሆነን የድርሻችንን ስናበረክት አሁን የሌላ ድርጅት ተከፋይ ያደረጉን ሃይሎች የዐቢይና የአብን ካድሬ አድርገው ባዶ ኪሳችንን በገንዘብ ሲሞሉት ነበር፡፡ በዘመቻው ጅማሮም ‹‹ይሄን ነቀርሳ ድርጅት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ነቅለን እንጣለው›› የሚል አገራዊ ጥሪ ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ወራሪው ሃይል ራያ በደረሰ ቅጽበት ‹‹አራት ኪሎን መመኘት የሚያመጣውን ጉዳት ካየህ ይበቃኻል›› ብለው ምሕረት ካደረጉለት በኋላ የሕዝብ ስጋት ሆኖ እንዲኖር ፈቅደውለት ሲመለሱ ‹‹የተዘረፍነውን ሳናስመልስ አንመለስም›› ሲሉ የነበሩ የአብን አመራሮች አብረው መመለሳቸው የሚያስገርም አይሆንም፡፡ እኛ ደግሞ እንደነ ናትናኤል ‹‹በዚህን ያህል ደሞዝ ካድሬ ሆኜ ላገለግል ቃል እገባለሁ›› የሚል የኮንትራት ውል ላይ ያኖርነው ፊርማ ባለመኖሩ መከላከያ ሠራዊትና መንግሥት ባለባት አገር ላይ አፋርና ሰቆጣ ዳግም ሲወረር ተመልክተን ወደ ቅዋሜ መመለሳችን ዜጋ ባይስብለን እንኳን መንጋ የሚል ታርጋ የሚያሰጠን አይሆንም፡፡ ምክንያቱም የመንጋ መገለጫው እንደ እስስት በሚለዋወጥ ፖለቲካና ፖለቲከኞች እየተመሩ አንዲት መፎክር እየደሰኮሩና የተሸመደደ መዝሙር እየዘመሩ መጎዝ እንጂ እየጠየቁ መጓዝ አይደለም። ይሄን ብዬ ወደ አብን ስመለስ ትናንት ልተቻቸው የቻልኩት በጦርነቱ ላይ ተሰውተው የቀሩ ይመስል የሚወክሉት ሕዝብ እሪታና ለቅሶ ምድሩን ሲያናውጥና በንጹሐን ላይ ጭፍጨፋ ለፈጸሙ አመራሮች ይቅርታ ሲሰጥ ጸጥ ለጥ ብለው ሲጓዙ በማየቴ ነው፡፡ ➔አብረዋቸው የተሾሙ የኦነግ አመራር የአድዋን ድል ድልድይ ስር ሲጥሉት ‹‹ዳግማዊ አድዋን እናከብራለን›› ሲሉ የነበሩ የእኛው ሹማምንቶች ግን መግለጫ ለማውጣት ሲሰንፉ በመታዘቤ ነው፡፡ ➔አብንን የተቸሁት ለቀብር የታሰበው ድርጅት ለድርድር ሲጋበዝ፣ ጌታቸው ረዳ ‹‹ፋሽሽቱ መንግሥት›› ማለቱን ትቶ በአማራ ኤሊት ላይ ጦሩን ሲመዝዝ፣ በወለጋ የተጨፈጨፉ ከ200 በላይ አማራዎች አስከሬን ወደ መቃብር ሲጋዝ፣ በመርሕ የለሽ የተግማማ ፖለቲካ ውስጥ እራሳቸውን አስማምተው ከመንግሥት ጋር ሲሽኮረመሙ በመታዘቤ ነው፡፡ ➔አብኖች ላይ ብእሬን ያነሳሁት ሹመት የሰጣቸው መንግሥት ፋኖን ኢ-መደበኛ ሃይል ብሎ ሲፈርጅ ‹‹ኖ›› በማለት የተቃወሙትን የአማራ ብልጽግና አመራሮች እያስወገደ ፋኖን ለመልቀም የተስማሙትን ሲሾም… የራያን ሕዝብ ከወራሪ እጅ መጣሉ አንሶ የወልቃይት ጥያቄንም ከስጋት ውስጥ ሲጥል… ለአማራ ሕዝብ ለመሞት የተዘጋጀ ፋኖ በአማራ እጅ ሲገደል፣ የብልጽግና የሃይል አሰላለፍ ከብአዴን ወደ ትሕነግ ሲያጋድል… እልፍ አእላፍ ሕዝብ ሲፈናቀል… ብሎም የአማራ ስጋት ከቀን ወደ ቀን ሲያይል…. መልስ ሆነው ሊገኙ ቀርቶ ጥያቄ የማንሳት አቅም አጥተው ሲልፈሰፈሱ ስላየሁ ነው፡፡ ይሄንንም ትችት በቀናነት ከመቀበል ይልቅ መንጋዎች፣ ምቀኞች፣ ተከፋዮች፣ ጩኸታሞች… በሚል ፍረጃ አጣጥለው ‹‹በስሌት እየተመራን የጀመርነውን የድል ጉዞ በስሜት እየደነፋችሁ አታበላሹብን›› የሚል ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ እኛም ይሄን ጥያቄ ተቀብለን ድምጻችንን ከማጥፋታችን በፊት እንዲህ ማለት እንሻለን፡፡ ‹‹አብን በዚህ መልኩ ከቀጠለ በብልጽግና ጉባዔ ላይ ብአዴን ነጥብ ጥሎ እንደወጣው ሁሉ… አብን ደግሞ ወደ አገራዊ ምክክሩ አጀንዳውን ይዞ ከገባ በኋላ ባዶ እጁን ይወጣል፡፡ ያኔ አማራን ሊታደግ ቀርቶ እራሱን ማስቀጠል ተስኖት ዞናዊ ፓርቲ ያቋቁማል፡፡ ወይም ደግሞ ይከስማል! ማርክ ማይ ወርድ!"

አብን የኦነግን ካርታ ፎቶ ኮፒ አድርጎ መንቀሳቀስ ባይጀምርም... ከአቶ ክርስቲያን ታደለና ከዶክተር ደሳለኝ ጫኔ ውጭ ያሉት አመራሮች የጠቅላይ ሚኒስትሩ ካዳሚዎች ሆነዋል። አብዛኞቹ አመራሮችም የአማ
አብን የኦነግን ካርታ ፎቶ ኮፒ አድርጎ መንቀሳቀስ ባይጀምርም... ከአቶ ክርስቲያን ታደለና ከዶክተር ደሳለኝ ጫኔ ውጭ ያሉት አመራሮች የጠቅላይ ሚኒስትሩ ካዳሚዎች ሆነዋል። አብዛኞቹ አመራሮችም የአማራን የሕልውና ጥያቄ በቤት እና መኪና ቀይረው ትግላቸውን አጠናቅቀዋል። ስለሆነም ፋኖዎች ቢገደሉ፣ አማራዎች ቢፈናቀሉ፣ አሸባሪዎች ዳግም ወረራ ቢፈጽሙ፣ የአማራ ሕዝብ ባልፈጸመው ጥቃት ቢወገዝ.... መግለጫ እንኳን ለማውጣት ልምምጥ የሚያስፈልጋቸው ዳተኞች ሆነዋል። እናም የአማራን የመኖር ያለመኖር ጥያቄ በፍርፋሪ የሸጡ የአብን አመራሮችን አስወግዶ በአዲስ አመራር በመተካት ፓርቲውን ማስተካከል ካልተቻለ ከዚህ በኋላ አብን ከተባለ ጥቅመኛ ፓርቲ የሚጠበቅ ድል ቀርቶ ትግል አይኖርም።

የኢሰመኮን ሪፖርት የአማራን ሥም በማጠልሸት መጋረድ አይቻልም! (አሳዬ ደርቤ) ▬▬▬▬▬ በአፋርና በአማራ ክልል ላይ ወረራ የፈጸመው የህውሓት ታጣቂ ‹‹በሰብዓዊ ፍጡር ላይ የጦር ወንጀል ማድረሱን የሚገልጸው የኢሰመኮ ሪፖርት ይፋ በወጣ ቅጽበት የትሕ-ኦነግ ደጋፊዎች ለተመልካች የሚዘገንን ተንቀሳቃሽ ምሥል ለጥፈዋል፡፡ በዚህም ምሥል ላይ ጥቃት ሲፈጽሙ የሚታዩት ታጣቂዎች የሌላ ክልል መለዮ የለበሱና ከአማርኛ በተጨማሪ ሌላ ቋንቋ ሲናገሩ የሚሰሙ ቢሆንም ‹‹አማርኛ የሚናገር ሁሉ አማራ ነው›› ብለው የሚያምኑት ሃይሎች ግን ‹‹አማራ የሚፈጽመውን ግፍ እዩልን›› በሚል ቅስቀሳ አማራና አፋር ላይ የፈጸሙትን ግፍ ይፋ ያወጣውን የኢሰመኮ ሪፖርት ለመጋረድ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ነው፡፡ በመሠረቱ በምሥሉ ላይ የሚታየው ጥቃት በማንም ይፈጸም በማን እጅግ ሊወገዝ የሚገባው አረመኔያዊ ተግባር ነው፡፡ የጥቃት አድራሾቹም ማንነት ተለይቶ እርምጃ ሊወሰድባቸው ይገባል፡፡ ከዚህ ውጭ ግን ባልተጣራ መረጃ ወደ ፍረጃ የገቡት ሃይሎች የጥምቀት ቀን በኦነግ ሸኔ የታገቱ 26 አማራዎች ከአንድ ቤት ውስጥ እንዲገቡ ከተደረጉ በኋላ በላያቸው ላይ እሳት እንደተለኮሰባቸው›› ሲነገር ድምጻቸው አልተሰማም፡፡ ኮምቦልቻን የወረረው አሸባሪም ከተማውን ለቅቆ ሲወጣ በፈጸመው ጥቃት የአስር የቀን ሠራተኞች አስከሬን በእሳት ተቃጥሎ እየጨሰ መገኘቱ ሲዘገብ ኀዘን አልተሰማቸውም፡፡ ዛሬ ግን በአፋርና በአማራ ሕዝብ ላይ የተፈጸመውን አረመኔ ድርጊት የሚገልጽ ሪፖርት ኢሰመኮ ይፋ ሲያወጣ… ይሄን ሪፖርት የሚጋርድ ተንቀሳቃሽ ምሥል በመለጠፍ በሌላ ክልል ሚሊታሪ አማራን ጥቃት ፈጸሚ አድርገው እሪሪሪ እያሉ ነው፡፡ እናም ወገን ሆይ፡- እነ አጅሬዎቹ የለቀቁትን እና ሥምህን የሚያጠለሹበትን ምሥል እያየህ ጉድ ጉድ በማለት ፈንታ የተፈጸመብህን ጥቃት የሚገልጸውን የኢሰመኮን ሪፖርት ሸምድድ እልኻለሁ፡፡

"ሕዝባዊ ጦር" በሚል ሥም ተደራጅቶ በፈጸመው ወረራ ዱቄቱን በስልቻ፣ ሊጡን በሞኻቻ ተሸክሞ በእምበር ተጋዳላይ እየጨፈረ የሄደ ወራሪ... የዘረፈውን ሊመልስ ካልሆነ በቀር "ተፈናቃይ" በሚል ሥም ሊመለስ አይገባውም።

ከተሞችን ሲመግቡ የኖሩ ከ7 ሚሊዮን በላይ አርሶ አደሮች ተፈናቃዮችና ተረጂዎች አድርጎ እልፍ አእላፍ ማሣ ፆም ያሳደረ መንግሥት በባልዲ የተተከሉ አራት ሰላጣዎች መሃከል ቁሞ "ያለ መሬት የሚተከል"
+4
ከተሞችን ሲመግቡ የኖሩ ከ7 ሚሊዮን በላይ አርሶ አደሮች ተፈናቃዮችና ተረጂዎች አድርጎ እልፍ አእላፍ ማሣ ፆም ያሳደረ መንግሥት በባልዲ የተተከሉ አራት ሰላጣዎች መሃከል ቁሞ "ያለ መሬት የሚተከል" እና "ያለ ዘይት የሚቀቀል" አትክልት ሲያስተዋውቅ መንግሥትነቱ ብቻ ሳይሆን ጤነኝነቱ ያጠራጥረኛል።

"ዘ-ሐበሻ" የተባለ ተልካሻ ሚዲያ የአቶ ገዱን ሥም ለማጠልሸት የሄደበት ርቀት ያስገርማል። ከትሕነግ ጋር በድብቅ የሚደራደሩና አፋርን ያስወረሩ ጠቅላይ ሚኒስትር እያንቆለጳጰሱ አቶ ገዱን በህውሓትነት
"ዘ-ሐበሻ" የተባለ ተልካሻ ሚዲያ የአቶ ገዱን ሥም ለማጠልሸት የሄደበት ርቀት ያስገርማል። ከትሕነግ ጋር በድብቅ የሚደራደሩና አፋርን ያስወረሩ ጠቅላይ ሚኒስትር እያንቆለጳጰሱ አቶ ገዱን በህውሓትነት መፈረጅ ምን የሚሉት ድንቁርና ነው? ለማንኛውም ብልጽግና የሚዘምትበት እና ፊቱን የሚያዞርበት አመራር የተሻለ ሕዝባዊ አስተሳሰብ ያለው መሆኑን ስለምረዳ ከአቶ ገዱና ከአቶ ጸጋ ጎን ቆሜ እንደ ዘ-ሐበሻ አይነት ልክስክስ ሚዲያዎችን ለመደምሰስ ተዘጋጅቻለሁ።

ከደቡብ ወሎ የተነሱ የአማራ ፋኖዎች ወደ ራያ ሲሄዱ ኡርጌሳ የሰፈረው በጀኔራል ተክሉ የሚመራው 21ኛ ክፍለጦር በ25/06/2014 ዓም መንገድ ላይ እንደያዛቸው ሰምተናል። ፋኖዎቹ በግልጽ ለሀገር እየ
ከደቡብ ወሎ የተነሱ የአማራ ፋኖዎች ወደ ራያ ሲሄዱ ኡርጌሳ የሰፈረው በጀኔራል ተክሉ የሚመራው 21ኛ ክፍለጦር በ25/06/2014 ዓም መንገድ ላይ እንደያዛቸው ሰምተናል። ፋኖዎቹ በግልጽ ለሀገር እየታገሉ ያሉ ስለሆኑ በአፋጣኝ ይለቀቁ። እኒህን የቁርጥ ቀን ጀግኖች በእጅ አዙር ትጥቃቸውን አስፈትቶ ያስጠረነፋቸው የአማራ ክልል መንግሥትም በዛሬዋ እለት ለችግሩ እልባት መስጠት አለበት። የአማራ ፋኖ ለመከላከያ ሠራዊቱ ደጀን እንጂ ሥጋት አይደለም!!

በብአዴን መዋቅር ውስጥ ጎጠኝነትና ጥቅመኝነት እንጂ ሐቀኝነት አሸንፎ አያውቅም ነበር። ዛሬ ግን የአቶ ጸጋ መራር እውነት የጥቅምን እና የጎጥን ሰንሰለት በጣጥሳ ማሸነፍ ቻለች። እናም ብድር በሚል ሥ
በብአዴን መዋቅር ውስጥ ጎጠኝነትና ጥቅመኝነት እንጂ ሐቀኝነት አሸንፎ አያውቅም ነበር። ዛሬ ግን የአቶ ጸጋ መራር እውነት የጥቅምን እና የጎጥን ሰንሰለት በጣጥሳ ማሸነፍ ቻለች። እናም ብድር በሚል ሥም ከአሠራር ውጭ 60 ሚሊዮን ብር የተከፋፈሉ አመራሮች ከእነ ወለዱ እንዲከፍሉና ከሥልጣናቸው እንዲታገዱ ተወስኗል።

የብልጽግና ፕሮጀክቶች እና የአዲስ አበባ ችግሮች የማይገናኙ በመሆናቸው ባሁኑ ሰዓት ታክሲ ማግኘት መኪና እንደ መግዛት ከባድ ሆኗል። ታሪፉንማ አታንሱት...!! አንድ መንግሥት ሠራተኛ በታክሲ ተጉዞ
+1
የብልጽግና ፕሮጀክቶች እና የአዲስ አበባ ችግሮች የማይገናኙ በመሆናቸው ባሁኑ ሰዓት ታክሲ ማግኘት መኪና እንደ መግዛት ከባድ ሆኗል። ታሪፉንማ አታንሱት...!! አንድ መንግሥት ሠራተኛ በታክሲ ተጉዞ ወደ ቢሮ ከሚሄድ "ደሞዜን ይቁረጡት" ብሎ ቢቀር ትርፋማ ይሆናል። እነሱ ከጠገቡ ሰው የሚራብ የማይመስላቸው፣ እነሱ ከተመቻቸው የሕዝብ እንግልት የማይታያቸው ጉዶች ናቸው እኮ!

"ከአማራዎች ይልቅ ሱዳኖች ይቀርቡናል" በሚል ንግግሩና ሕዝባችን ላይ ባስፈጸመው አረመኔያዊ ተግባሩ የሚታወቀው ዶ/ር ደጺ "ለኢሳያስ አሳልፎ የሰጠን ከሃዲው የአማራ ተስፋፊ ልሂቅ ከባድ ቅጣት ይጠብቀዋል" እያለ ሲዝት አስበው እስቲ...😁 ደግሞ እኮ ዛቻው የተለጠፈበትን የፌስ ቡክ ገጽ ገለጥ ገለጥ ብታደርገው ከጦርነቱ በፊት ፖስት የተደረጉት መግለጫዎች ሁሉ "የትግራይ እና የኤርትራ ሕዝቦች ተመሳሳይ ማንነትና ጠላት ያላቸው ሕዝቦች ናቸው" የሚሉና አማራን የሚያጥላሉ ሆነው ታገኛቸዋለህ።

ወገን ከሥልጣን የተነሱ ወይም የሚቀነሱ አመራሮች መጪውን ጊዜ በግልጽ ሲነግሩህ ‹‹ለምን አሁን ተናገሩ?›› ብለህ በማናናቅ ፈንታ ‹‹ለምን ተባረሩ?›› ብለህ ጠይቅ፡፡ ምክንያቱም ያለንበት ወቅት የአማራን ሕዝብ ማጥፋት የሚሹ ሃይሎች ሥልጣን የያዙበትና የእኒህን ሃይሎች ዙፋን ማስቀጠል የሚሻ ድርጅት የተሸከምንበት በመሆኑ ከአመራርነት የሚያስባርረው ሙሠኞችን መዋጋት እንጂ ሙሥና መብላት ሊሆን አይችልም፡፡ የሕዝብ ተቆርቋሪ እና የወገን ጠባቂ ሆኖ መገኘት ካልሆነ በቀር ሕዝብን ለጥቃት ዳርጎ የቤተሰብን ምቾት ማረጋገጥ ከሹመት የሚያስነሳ አይሆንም፡፡ ➔ከበላይ አካል አንድ ትዕዛዝ ሲመጣ ‹‹ታዛዥ ነኝ›› በማለት ፈንታ ‹‹ተቃውሞ አለኝ›› ያልክ ቀን ግን ገሸሽ ትደረጋለህ፡፡ ➔የምትመራውን ሕዝብ ለጉዳት የሚዳርግ እቅድ ሲሰጥህ ‹‹ጠቃሚ ነው›› በማለት ፈንታ ‹‹አውዳሚ ነው›› ያልክ ቀን ጥርስ ውስጥ ትገባለህ፡፡ ➔የሚሰጥህን ተልዕኮ ያለ ምንም ጥያቄ ተቀብለህ ሕዝብህ ላይ እየጫንክ ከርስህን እና ኪስህን ከመሙላት ይልቅ የኅሊናህ ተገዥ ሆነህ መቃወምና መጠየቅ የጀመርክ እለት ከጎናቸው ፈቀቅ ትደረጋለህ፡፡ ይሄን ስልህ ግን የሚሰናበተው አመራር ሁሉ ጤነኛ ነው እያልኩህ አይደለም፡፡ በተለያዩ የሥልጣን ሽኩቻዎችና በጥቅም ቅራኔዎች የሚባረሩ ብዙ ጥቅመኞችን ጎጠኞች ይኖራሉ፡፡ በብአዴን መዋቅር ውስጥ ከጎጠኝነት በላይ አማራዊ ስሜት፣ ከተላላኪነት ይልቅ እንቢተኝነት፣ ከአድፋጭነት ይልቅ ተሟጋችነት ከሥልጣን ያስባርራል ማለቴ እንጂ… አማራን ለማጥፋት ከሚሹ አሸባሪዎች ጋር አብረው ሲሠሩ ከተገኙ ቅጥረኞች በላይ ‹‹ፋኖ ይክስም፣ ልዩ ሃይሉ ይዳከም›› የሚል ትዕዛዝ ሲተላለፍ ‹‹አይሆንም›› ብለው የሚቃወሙ አመራሮች በአሽከሮች ፊርማ ይባረራሉ ማለቴ እንጂ… ከዚህ ባለፈ ደግሞ… በሥልጣኑ ሲባልግና ሢሞስን ተገኝቶ በጥፋቱ የተባረረ ወይም ደግሞ ከመናኛ ወንበር ላይ የተወረወረ አመራር ባለመታሰሩ አምላኩን እያመሰገነ አርፎ ይቀመጣል እንጂ ደረቱን ነፍቶ ከሥልጣኑ የተነሳበትን ምክንያትና ባንተ ላይ የተደቀነውን ስጋት አይነግርህም፡፡ በተረፈ ለአንድ ቀን ደፈር ብለው ሐቅን የተናገሩና ጠቃሚ ነገር የሠሩ ብሎም በሕዝብ ዘንድ ትንሽ ሥም ያፈሩ ከዙፋኑ ገሸሽ ሲደረጉ….ለመጣ ለሄደው ‹‹እሺ›› እያሉ ሕዝባቸውንና ኅሊናቸውን የሚሸጡት ግን ወንበሩ ላይ ለሽሽ ብለው ታገኛቸዋለህ፡፡

ባንድ ወቅት "እናት አገራችን በጠላት ተደፍራ ከቤታችን አናድርም" ብለው ለሸፈቱ አባቶቻችን መዋያ ማደሪያ የነበረው ዋሻ፤ የተፈናቀሉ አማራዎች መጠለያ ሊሆን የቻለው በብአዴን እና በአማራ ሙሕራን ይሁ
+2
ባንድ ወቅት "እናት አገራችን በጠላት ተደፍራ ከቤታችን አናድርም" ብለው ለሸፈቱ አባቶቻችን መዋያ ማደሪያ የነበረው ዋሻ፤ የተፈናቀሉ አማራዎች መጠለያ ሊሆን የቻለው በብአዴን እና በአማራ ሙሕራን ይሁንታ ነው። ታላቁ የአማራ ሕዝብ ጎጆውን ጥሎ የሚራወጠው፣ "ከተማ ታቆሽሻለህ" እየተባለ የሚሳደደውና ከዋሻ ውስጥ ሊጣል የቻለው.... ቪላ እና ቪ-8 ካገኘ የሕዝቡ መንኮታኮት ግድ የማይሰጠው ጥቅመኛ አመራርና መናኛ ሙሕር በመውለዱ ነው። Share

ለአንዳንዶ ኮካዎች አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ከወለጋ የተፈናቀሉ ዜጎች አገር እና መንግሥት ጠፍቷቸው እየተንከራተቱ ባሉበት ሁኔታ ዩክሬን የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው የሚመለሱበትን ሁኔታ መንግሥት እንዲያመቻች አንዳንድ ካድሬዎች እየጠየቁ ነው። ደፋር ሁላ! ባሁኑ ሰዓት ዩክሬን መገኘት ኢትዮጵያ ከመገኘት በላይ አስጊ ሆኖ ነዎይ ወደ አገራቸው የሚመለሱት? ወለጋ፣ አፋር፣ ራያ፣ ጎሃ ጽዮን፣ ጉጂ፣ መቀሌ መገኘት Kharkiv እና Kyiv ከመገኘት በላይ አደጋው የከፋ አይደለም ወይ? አደጋው እንኳን ተመሳሳይ ቢሆን ጭፍጨፋዋን ከምትደባብቀው ኢትዮጵያ ይልቅ የዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ዐይኑን የጣለባት ዩክሬን አትሻልም ወይ? በዚያ ላይ ደግሞ ዩክሬናውያን ወረራ የፈጸመ ጠላት እንጂ ታጣቂ አደራጅቶ ዜጎቹን የሚያስገድል መንግሥት የላቸውም።

ይህ ዶላር የሚሸቀልበት የዩቲዩብ ቻናል አይደለም። በዘመንህ እና በወገንህ ላይ የተፈጸመውን ክስተት ጠቅልሎ የያዘና ብዙ የተለፋበት መጽሐፍ እንጂ... ! ገቢውም መስዋዕትነት ለከፈሉ የፋኖ ቤተሰቦች
ይህ ዶላር የሚሸቀልበት የዩቲዩብ ቻናል አይደለም። በዘመንህ እና በወገንህ ላይ የተፈጸመውን ክስተት ጠቅልሎ የያዘና ብዙ የተለፋበት መጽሐፍ እንጂ... ! ገቢውም መስዋዕትነት ለከፈሉ የፋኖ ቤተሰቦች የሚውል ነው። በጥቂት ቅን ሰዎች እገዛ 75 % የሕትመት ወጪው ተሸፍኗል። ስለዚህ ቀሪውን የ25% ወጪ በአቅማችሁ ልክ መሸፈን የምትሹ ወገኖች ከስር ባለው አካውንት ታበረክቱ ዘንድ እጠይቃለሁ። ከዚህ በፊት ድጋፍ ያደረጋችሁ ወገኖችንም አመሠግናለሁ። በተረፈ መጽሐፉ ሲወጣ የመጀመሪያው ገጽ ላይ በስም ጠቅሼ የማመሰግን ይሆናል። 84755524 አቢሲኒያ ወይም 1000187948871 cbe