cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

Janderebaw Media

የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በጠቅላይ ቤተ ክህነት የማኅበራት ማደራጃ መምሪያ ዕውቅና የተሰጠው መንፈሳዊ ማኅበር ነው:: የሚከለክለኝ ምንድን ነው?

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
52 641
Obunachilar
+2324 soatlar
+2147 kunlar
+1 91930 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

ዐሥራ ሦስት የአብነት ደቀ መዛሙርት ዲቁና ተቀበሉ | ጃንደረባው ሚድያ | ግንቦት 6 2016 ዓ.ም.| አዲስ አበባ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የማኅበራት ማደራጃ መምሪያ የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ በጃን እስጢፋኖስ ላለፉት ሁለት ዓመታት በአዳር የአብነት ትምህርት ያስተማራቸውንና መሥፈርቱን ያሟሉ ዐሥራ ሦስት ተማሪዎች በዛሬው ዕለት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አቡነ ሄኖክ አንብሮተ ዕድ ማዕረገ ዲቁናን ተቀብለዋል:: የኢጃት ቦርድ ሰብሳቢ ዲ/ን ዶ/ር ዳዊት "ኢጃት ከተመሠረተበት ጊዜ አንሥቶ በጃን ማዕተብ ከሰባ በላይ ንዑሰ ክርስቲያንን ለምሥጢረ ጥምቀት ፣ ብዙኃንን በጃን ዮሐንስ ለምሥጢረ ንስሓና ቁርባን ፣ በጃን ቃና ዘገሊላ ደግሞ ለምሥጢረ ተክሊል ያበቃ ሲሆን አሁን ደግሞ ያስተማራቸውን ደቀ መዛሙርት ለምሥጢረ ክህነት አብቅቶአል" ብለዋል:: "ዲያቆናቱ በአግባቡ የተማሩና ለአገልግሎት ዝግጁ የሆኑ ናቸው" ያሉት የጃን እስጢፋኖስ ሰብሳቢ መምህር ኤፍሬም ሲሳይ ሲሆኑ "ተማሪዎቹ ምንም ዓይነት ትምህርት ሳይኖራቸው ወደ ኢጃት መጥተው በአግባቡ ተምረው ለዚህ በመብቃታቸው እጅግ ደስ ብሎናል:: ትምህርት ሳይጨርሱ ወዴትም እንዳይሔዱ በማስገደድም በአበው ልማድ መሬት ላይ እየተኙ በሌሊት እንዲማሩና ከአብነት ትምህርቱ ጋር መሠረታዊ ነገረ ሃይማኖትም እንዲማሩ ተደርጓል" ብለዋል:: በማያያዝም "በቅርቡ ሱባኤ እስጢፋኖስ የተሰኘ የዲያቆናት ብቻ ሱባኤ ጉባኤ ለማካሔድም ዝግጅታችንን ጨርሰዋል ብለዋል" ዲያቆናቱን አስተምረው ለዚህ ካበቁ መምህራን መካከል አንዱ የሆኑት መምህር ኃይለ ኢየሱስ ተሻለ በበኩላቸው "ወደ አገልግሎት ለመግባት በአግባቡ ደጅ ጸንተውና የአገልግሎቱን ምንነት ተረድተው ለዚህ መብቃታቸው ቤተ ክርስቲያንን የበለጠ ለማገልገል ያስችላቸዋል:: ለዚህ ደርሰው ማየታችን ለኢጃት ትልቅ ደስታ ነው" ብለዋል::
Hammasini ko'rsatish...
874👍 123🙏 75🔥 12
የሰሙነ ሕማማት ጸሎትና ስግደት | ለከ ኃይል፣ ኪርያላይሶን፣ መልክአ ሕማማት ሰላምታ ዘነግህ https://www.youtube.com/watch?v=HBndYSvPSRA
Hammasini ko'rsatish...
🙏 453 299👍 52🔥 27
959👍 124🙏 67🔥 2
ሁላችሁም ተጋብዛችኋል
Hammasini ko'rsatish...
656👍 126🔥 28🙏 19
ይህንን checklist ይጠቀሙ
Hammasini ko'rsatish...
316👍 45🙏 38🔥 8
ሰባተኛ ሳምንት ኒቆዲሞስ ቻሌንጅ 1)ምሽታችንን ቃለ እግዚአብሔርን በማዳመጥ ማሳለፍ 2)ለሕማማት ሳምንት መዘጋጀት 3)ያልተረዳናቸውን ነገሮች መምህራንን መጠየቅ 4)ኪዳን ማድረስ 5)ለዚህ ሳምንት መጽሐፍ ቅዱስ ጥናት በኒቆዲሞስ ሰንበት ቅዳሴ የሚነበበውን ወንጌል ዮሐ. 3 :1 – 12፣ የሚነበቡትን መልዕክታት ሮሜ. 7:1 – 19 ፣ 1ኛ ዮሐ 4፡ 18 - 21 ማጥናት እንዲሁም የሚሰበከውን ምስባክ መዝ 18፡3 – 4 መጸለይ ከ እነዚህም የወደዳችሁትን ቃል ያጋሩን..
Hammasini ko'rsatish...
400👍 83🙏 33
ታማኝ አገልጋይ ማን ነው? ሳምንት 6 ቻሌንጅ እግዚአብሔር የሰጣችሁ ጸጋ፣ ችሎታ ምንድን ነው በምንስ ሙያ ተሰማርታችኋል? ቻሌንጅ 1. እግዚአብሔር በሰጠን ጸጋ፣እውቀት፣ችሎታ እንዲሁም በተሰማራንበት ሙያ እግዚአብሔርን በምን ማገልገል እንደምንችል በማሰብ፣ በተግባር ማዋል ።  የተፈጠርንበት አላማ ማገልገል ነውና፣ አገልግሎትን ሕይወታችን በማድረግ ቤተክርስቲያንን ማገልገል 2. አሥራት በኩራትን ማውጣት፣ 3.በገብርኄር ሰንበት በቅዳሴ የሚነበበውን ወንጌል ማቴ 25፡14–31፣ የሚሰበከውን ምስባክ መዝ 39፡8–9 ፣ እንዲሁም የሚነበቡትን መልእክታት 2ኛ   ጢሞ. 1 – 16 ፣  1ኛ  ጴጥ. 5 ፡ 1– 12 ማጥናት
Hammasini ko'rsatish...
592👍 108🙏 91
ለምዝገባው ከታች ያለውን የመመዝገቢያ ሊንክ ይጠቀሙ። https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScp7LD5_h9NWBPiyzhsYgd7bN_H_TvSMnOIrCo0INHcmgihmg/viewform?usp=sf_link
Hammasini ko'rsatish...
491👍 97🙏 44🔥 22
ሳምንት 5 ደብረዘይት ቻሌንጅ 1) ራሳችንን ፈትሸን: ንስሐ ገብተን : ወደ ንስሐ አባቶቻችን ቀርበን የተናዘዝን : የተሰጠንን ቀኖና የጨረስን እና "እግዚአብሔር ይፍታ" ተብለን የተዘጋጀን ከንስሐ አባታችን ጋር በመማከር ከቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ መቀበል 2)ራሳችንን ፈትሸን ለኑዛዜ የተዘጋጀን ወደ ንስሐ አባቶቻችን በመቅረብ ኑዛዜ መፈጸም : ቀኖና መቀበል 3)ክርስቶስ ዳግም ሊፈርድ ሲመጣ የሚጠይቀንን 6ቱ ቃላተ ወንጌልን መፈጸም ለዚህም በግላችን ወይም ከ6ቱ ቃላተ ወንጌል ጉዞ መሳተፍ 4)የታሰሩ ሰዎችን መጠየቅ 5)በደብረዘይት ሰንበት በቅዳሴ የሚነበበውን ወንጌል *ማቴ 24:1-36 የሚሰበከውን ምስባክ መዝ 45:2-3 እንዲሁም የሚነበቡትን መልእክታት *1ኛ ተሰ 4:13-18 *2ኛ ጴጥ 3:7:15 ማስታወሻ በመያዝ ማጥናት 6)በሰው ከመፍረድ መቆጠብ 7)በዚህ ጾም ምን እንዳሻሻልን:ምን እንደተጠቀምን ራሳችንን መመዘን ስለዚህ፥እናንተ ደግሞ ተዘጋጅታችኹ፡ኑሩ፥የሰው ልጅ በማታስቡበት ሰዓት ይመጣልና" -ማቴ 24:44
Hammasini ko'rsatish...
382👍 95🙏 50🔥 1
ይህንን checklist ይጠቀሙ
Hammasini ko'rsatish...
292👍 50🙏 14