uz
Feedback
ግጥም🥰 ልጅ ወርቅነህ... ✍ ( lij werkneh )

ግጥም🥰 ልጅ ወርቅነህ... ✍ ( lij werkneh )

Kanalga Telegram’da o‘tish

➢ ለማንኛውም አስተያየት ይህን ሊንክ በመጫን አስተያየትዎን ያስቀምጡ 👇 👉 @Lijwerkneh 👉 @Lijwerkneh ➣ የቻናሉ አጋፋሪ (ወርቅነህ አስፋው) እና የእውቅ ገጣምያን ስራዎች በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ። ➣ የመጻህፍት ቅምሻ እና ጥቆማ ይደረጋል። ➣ የኪነ ጥበብ ምሽት ኘሮግራሞች ጥቆማ ➣ ከምስል ጋር የተቀናበሩ ግጥሞች በስፋት ይቀርቡበታል።

Ko'proq ko'rsatish
1 373
Obunachilar
-124 soatlar
-37 kunlar
-1930 kunlar
Postlar arxiv
የልጅነት ልቤን ሰርቃ እስከ ማደግ ዘመን የተከተልኳት አንዲት ውብ የሆነች ፍጥረት....በፍቅሯ የተነደፍኩላት ፣ሌላ ከማየት ዓይኔን የጋረደች እመቤት፣ እኔ ብቻ ሳልሆን ሌሎችም በፍቅሯ ወድቀው ውበታቸ
የልጅነት ልቤን ሰርቃ እስከ ማደግ ዘመን የተከተልኳት አንዲት ውብ የሆነች ፍጥረት....በፍቅሯ የተነደፍኩላት ፣ሌላ ከማየት ዓይኔን የጋረደች እመቤት፣ እኔ ብቻ ሳልሆን ሌሎችም በፍቅሯ ወድቀው ውበታቸው እንዳይወዳደር ስለሚያውቁ ዙሪያዋ የሚረግፉላት የውቦች ንግሥት.....! ለእርሷ ጣቶቼ ተርገፍግፈው ብዙ ለመሰደር ቢድኹም ግን በሚገባት ልክ አልሆነምና ይቅርታዋን እንደማትነፍገኝ አምናለሁ....!። ከዘጠኝ ወር ምሽግ በኋላ የረገጥኩት መሬቷ፣ የቀመስኩት አፈር ፣ የዳበስኩት ገላዋ ፣ የሳብኩት መዓዛዋ ዕድሜ ልክ አብሬያት እንድኖር ያስገደደኝኝ መስሎ ይሰማኛል ፣ብቻ የሆነ ልዩ ኃይል አላት!......ከፈጣሪ እጅ በቀር በማንም የማትፃፍ አንድ ስም! ከእርሷ በመሆኔ ደስተኛ ዕድለኛም ነኝ....! መውደዴን ጥልቅ ፍቅሬን ብታውቅልኝ ብዬ በቻልኩት የቃላት ግጥምጥም ለመግለጥ ከወረቀት ጋር ታግያለሁ...!። ሰማይና ምድርን ያጸና ምንድነው ቢሉ " ኃያል ፍቅር" ነው...ነፍስ ያለው ሁሉ ስለ ፍቅር ይዘምራል ፤ ያለ ፍቅር የሆነ ፣ የቆመና የኖረ አንዳች ነገር የለም...! በፍቅር መዳፍ እምነት፣ጉልበት፣ስኬት፣ውድቀትና መሰሎቻቸው ታቅፈው ልብ ስላልኩ እኔው ጋር ብቻ ከሚቀር እነርሱንም ብዕሬ የመስመር ዘለላዎችን ደፍሮ አስፍሮባቸዋል..!። በእኔ ለጋ ዕድሜ የተኖረ ፣ የተገኘ ፣ የተፈጠረና የተገለጠ ስድር ተከትቦ እዚህ ደረሷል..... ተወዳዳሪ የሌላት የኔ" የውቦች ንግሥት" ብቸኛ እንዳትሆን በሌሎች ታጅባ ልትነበብ እንዲህ ተሰናድታ ቀርባለች...!። የመጽሐፉ ዋጋ 400 ብር የኢት.ንግድ ባንክ 1000266560846 ቴሌብር 09 47 81 23 70 #ቅድመሽያጭ ሼር በማድረግ ቀና ምላሽዎን ያሳዩኝ 🙏

አያቴ አደራ ሰጥታኝ የሚያልፍ ዝናብ እንዳይመታኝ፤ ለሚቀር አውርቼ እንዳልቀር ፣ ለሚሞት ህይወት እንዳልሰጥ ፣ ፀጥ! የሚያልፈው አፌን ሳይከፍተው ዝግ ዝም እንድል እንድተው፤ አያቴ አደራ ብላኝ ተባይ
አያቴ አደራ ሰጥታኝ የሚያልፍ ዝናብ እንዳይመታኝ፤ ለሚቀር አውርቼ እንዳልቀር ፣ ለሚሞት ህይወት እንዳልሰጥ ፣ ፀጥ! የሚያልፈው አፌን ሳይከፍተው ዝግ ዝም እንድል እንድተው፤ አያቴ አደራ ብላኝ ተባይ ቃል አፌን ቢበላኝ ፣ መተንፈስ ሁሉ እስኪያቅተኝ ምላሴ ሲተናነቀኝ ምላሼ ሲተናንቀኝ ፣ ታግዬ ስንቱን ዝም አልኩት አይቼ ስንቱን አለፍኩት። ዙሪያዬ የነገር እቁብ ቆጥረዋት ምላሴን ከቁብ ፣ ጣል ቢሉኝ ቃል ካንደበቴ አደራ ይዞኝ ያ'ያቴ ፣ አቋም አቅሜን ደብቄ ስንቱን ያለፍኩት ታምቄ ፣ ምስኪን... ራሴን ባለማወቄ! የሚያልፈው ዝናብ ሳይመታኝ ለማለፍ ዙሪያዬን ስቃኝ ፣ ባየሁት ቃሌ እየቃጣ ስውጠው ፈርቼ ጣጣ ፣ ሳምቀው ኖሬ ሳፍነው ምስኪን... ለካስ እኔው ነኝ የማልፈው!

በክህደት ዓለም... ምን ከንፈር ቢሳሳ፤ የሚያም ባይመስልም ወዳጅን ለመሸጥ... ለይስሙላ መሳም፤ ከመንከስ አያንስም። / ልጅ ወርቅነህ ...✍✍ /
በክህደት ዓለም... ምን ከንፈር ቢሳሳ፤ የሚያም ባይመስልም ወዳጅን ለመሸጥ... ለይስሙላ መሳም፤ ከመንከስ አያንስም።                            / ልጅ ወርቅነህ ...✍✍ /

እናት ምን ተሰማት..? የሆነውን ሰምቶስ፣ ምን አለ ሀገሩ ሰው እንደ እህል ዘር፣ ሲዘራ ከአፈሩ ። / ልጅ ወርቅነህ...✍ / 😭😭😭 ፈጣሪ ለሟች ቤተሰቦች መጽናናትን ይስጥልን! ​በአደጋው የተጎ
እናት ምን ተሰማት..? የሆነውን ሰምቶስ፣  ምን አለ ሀገሩ ሰው እንደ እህል ዘር፣ ሲዘራ ከአፈሩ ።                       / ልጅ ወርቅነህ...✍ / 😭😭😭  ፈጣሪ ለሟች ቤተሰቦች መጽናናትን ይስጥልን! ​በአደጋው የተጎዱ ወገኖቻችንን ለመደገፍና የተደቀነውን ስጋት በጋራ ለመወጣት የሚከተሉት የባንክ አካውንቶች በይፋ ተከፍተዋል፦ ​የጋሞ ልማት ማህበር (Gamo Development Association) ​የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)፦ 1000021467174 ​የጋሞ ዞን አደጋ ስጋት (Gamo Zone Disaster Risk Management) ​የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)፦ 1000321312865 ​📢 የሁላችንም ግዴታ ​የወገኖቻችን እንባ እንዲታበስና የተረፉትም ተገቢውን ድጋፍ እንዲያገኙ፦ ​በአቅማችን ያለውን የገንዘብ ድጋፍ እናድርግ። ​ይህንን መረጃ #ሼር በማድረግ ለብዙዎች እንዲደርስ እናግዝ። 🙏

ዛሬም ቦታዬ ላይ ቆምያለሁ ታም ታራራም... ታራራም...ስልተ ምቱ ባመረ ዜማ የክራሩ ድምፅ መንቆርቆሩን ቀጥሏል። ልክ እንደ ፀሀይ ሁሉ ሰዓቷን ጠብቃ የኔዋም ፀሀይ የክራሩን ድምፅ ተከትላ የቤቷን መስኮቶች ከፈት አድርጋ  ወጣች። ሁለቱ አይኖቼ ቡዝዝ ብለው ከመስኮት ዳር ላይ ቆማ ካለችው ታይታ ከማትጠገበው ውብ እንስት አይኖች ላይ ይንከራተታሉ። ጣቶቼም ከወትሮ በተለየ ደም እስኪቋጥሩ ድረስ የዜማ አይነት እያሽጎደጎዱ ከክራሩ ጋር ትግል ገጥመዋል። ይገርማል! በህይወቴ ትልቋ የቀረችኝ  ሀብቴ ክራሬ እንደሆነች ቀድሜ ባውቅም ዛሬ ግን ይበልጡኑ ተረዳሁ። ከክራሬ በቀር የትኛው ዝናዬ የትኛውስ ሀብቴ የትኛውስ ነገሬ ነበር  ይህችን ከመሰለች ሞናሊዛ እንኳን ብታያት ከምትቀናባት ውብ ኮረዳ ፊት ለፊት ሊያቆመኝ የሚችል?  እንጃ ! ብቻ ዕድሜ ለክራሬ ! እድሜ ለአያቴ እንዳልል ይህቺን አንድ ክራር አውርሳኝ  አውላላ ሜዳ ላይ  ጥላኝ ከኮበለለች አመታት ተቆጠሩ። ብቻ ግን ነፍሷን ይማረውና ሴት አያቴ ገና ህፃን እያለሁ ነበር ወላጅ እናቴ  አዝላኝ ቤት ውስጥ ጉድ ጉድ ስትል  እሷ ግን ቁጭ ብላ ክራሯን ትከረክራለች።  እናቴም በድምፅ እያንጎራጎረች  ከግራ ወደ ቀኝ ሲላት ደሞ ከፊት ወደ ኋላ እየናጠችኝ አያቴን በድምፅ ስታጅብበት የነበረው ሁነት ሁሉ አሁን ድረስ አዕምሮዬ ላይ ተቀርፆ ልክ ዛሬ ላይ እንዳለ ሁሉ ጆሮዬ ላይ ያቃጭልብኛል። ዳሩ ግን ዛሬ ላይ አያቴ በህይወት ባትኖርም በወቅቱ ግን ክራሯን እና አስገራሚ የአዛዚያም ስልቷን ሁሉ ነበር አውርሳኝ  ላትመለስ የሄደችው።  እንደው ግን አሁን ላይ  አያቴ በህይወት ብትኖርና በቅፅበት ለአፍታ ቀና ብላ  ከቆምኩበት ቦታ ላይ አሻግራ ብታየኝ  ምን ትለኝ ይሆን ? ብዬ አሰብኩና ፈገግ አልኩኝ። <<  አፈር አባህ ብላ አንተ ልጋጋም ቂጥህን እንኳን በቅጡ ሳትጠርግ ጭራሽ ብለህ ብለህ አውላላ ሜዳ ላይ ከሴት ጋር ? በል ና እንጀራ ገዝተህልኝ ና >> የምትለኝ ይመስለኛል። 😁 ይቀጥል ወይስ ...........?🤔

እየሞከርኩኝ ነው ❗️❗️ አወቃችሁት ያ ልጅ በሱስ ተጠምዶ ወጣትነቱን ለሱስ ያስገዛው መውጣት እየፈለገ ግን ደግሞ ማደሪያውን በየጥጋ ጥጉ ያደረገ ሲነጋ ከወደቀበት ተነስቶ በፀፀት ውስጥ ሆኖ አልደግመ
እየሞከርኩኝ ነው ❗️❗️ አወቃችሁት ያ ልጅ በሱስ ተጠምዶ ወጣትነቱን ለሹሾ ያስገዛው መውጣት እየፈለገ ግን ደግሞ ማደሪያውን በየጥጋ ጥጉ ያደረገ ሲነጋ ከወደቀበት ተነስቶ በፀፀት ውስጥ ሆኖ አልደግመውም እያለ ለልሹ ቃል እየገባ መልሶ ደግሞ እያፈረሰ ያለው ልጅ  አዎ እሱ ልጅም እኮ በቻለው አቅም እየሞከረ ነው። ያቺስ ልጅ << ኧረ ዕድሜሽ እኮ ሄደ!  አታገቢም እንዴ ? ቆመሽ ቀረሽ እኮ >> እየተባለች የአላፊ አግዳሚው አፍ መፍቻ  የሆነችው ልጅ የልቧን እውነት ማንም ያልተረዳላት ልጅ አዎ እሷም ልጅ  እየሞከረች ነው።  እነዛስ ደግሞ << አትወልዱም እንዴ ? >>እያለ የሰፈሩ ሰው አላስቆም አላስቀምጥ እያለ የሚነዘንዛቸው እንደውም ልጅ መታቀፍ እያማራቸው ግን ደግሞ አልሆን ያላቸው ባለትዳሮች።  ያኛውስ ደግሞ ምስኪን አልሞላለህ ያለው አባት  ቤተሰቡን ለማስተዳደር ደፋ ቀና ቢልም እንደ ምኞቱ ያልሆነለት የእለት ጉርስ ይዞ ለመግባት የሚውተረተረው አዎ እሱ እራሱ  የልጆቹ ነገር ሆኖበት አማራጭ ስለሌለው ዛሬም እየሞከረ ነው። እነዛ ደግም ድንገት ባላሰቡት ባልጠበቁት አደጋ እና በሽታ ከጓደኞቻቸው ከወዳጆቻቸው ተነጥለው እቤት አልጋ ላይ የቀሩ የጠዋቷን ፀሀይ  መሞቅ አይደለም ማየት እንኳ ያቃታቸው የመዳናቸውን ቀን የሚጠባበቁት ብቻ ምኑ ቅጡ ሁሉም በተኛበት አልጋ ላይ እና በቆመበት ጫማ ላይ ሆኖ ሙከራውን አላቆመም። በእርግጥም ይሄ ድምፅ የብዙዎች ነው። ይህ ከብዙ በጥቂቱ ነው ሌላውን ግን ቤት ይቁጠረው። እየሞከርን ላለነው ሁሉ ፈጣሪ ሙከራችንን እና መሻታችንን አይቶ ከማይጠቅመን በቀር ሁሉን ይፈፅምልን። አይዞን ሙከራችን ግን አይቁም !! 🙏                            / ልጅ ወርቅነህ ....✍✍ /

"መሀረቤን?" ስትባሉ? “አላየንም!” የምትሉ ፡ ባትሆኑም፡ ልክ ናችሁ ¡ ያ'ይኑን እንባ ፡ መች አያችሁ ? ሰው ፊት ቆሞ ፡ ሆደ ቡቡ ከፍቶት ዓይኑ ፡ በመርጠቡ ጋርዶት ሊስቅ፡ በማሰቡ "የታል?"
"መሀረቤን?" ስትባሉ? “አላየንም!” የምትሉ ፡ ባትሆኑም፡ ልክ ናችሁ ¡ ያ'ይኑን እንባ ፡ መች አያችሁ ? ሰው ፊት ቆሞ ፡ ሆደ ቡቡ ከፍቶት ዓይኑ ፡ በመርጠቡ ጋርዶት ሊስቅ፡ በማሰቡ "የታል?" ብሎ፡ መሀረቡን በጨዋታ ፡ ሥም የልቡን የጠየቀው ፡ እንደ ወረት አጥቶስ ቢሆን ፡ እንባው ትኩረት? መሀረቤን? " ሲል ሲቃትት "ምን ሆኖ ነው?" እንደማለት የጣሩን ጥግ ፡ ለመፈለግ ካ'ይኖቹ ሥር  ፡እዥ ለመጥረግ ከመሀረብ እንደመቅደም ለ"አላየንም " መሽቀዳደም!? ናፍቆስ ቢሆን ፡ ያይን ምንጩን? ጥፍጥሬውን፡ ጥቁር ነጩን ፈልቅቆ አይቶ ፡ ለቅሞ ስቃይ የሚያዳውር ፡ ሙሾ ፈታይ የሚያጣፋ ፡ ጥለት ከላይ ናፍቆስ ቢሆን አስተዛዛኝ እኔን የሚል፡ አደግዳጊ ? "መሀረቤን !"፡ ባይ ፈላጊ መስሎስ እንደሁ፡ ያስተጋባው? እንጂማ ሰው፡ ለጥል ከእንባው መች ያንሰዋል ፡አይበሉባው!? እጅግ አይቶ ሆዱ ባብቶ ጭልም ቀኑ በርጥብ ዓይኑ እንዳይታይ ፡ በማሰቡ ቢያስፈልገው ፡መሀረቡ "ያያችሁ" ሲል ፡ ሲያስተጋባ ባታዝኑለት ፡ባትጠርጉ እንባ “አላየንም!” በጭብጨባ? #red-8

አባ ሞት ጉልበተኛ ምነው የማይነቃ ካንተ ጋ የተኛ ልብስ ገዝቶ ነበር እለብሳለሁ ብሎ አፈር ለበሰ አሉኝ - የገዛውን ጥሎ! አባ ሞት ሞገደኛ ምነው አያሳልፍ ደና መንገደኛ ! አያ ያንተስ ህልፈት ከራ
አባ ሞት ጉልበተኛ ምነው የማይነቃ ካንተ ጋ የተኛ ልብስ ገዝቶ ነበር እለብሳለሁ ብሎ አፈር ለበሰ አሉኝ - የገዛውን ጥሎ! አባ ሞት ሞገደኛ ምነው አያሳልፍ ደና መንገደኛ ! አያ ያንተስ ህልፈት  ከራስ አዋቀሰን ያን ጊዜ ያሳቅከን -  አሁን አስለቀሰን! ያን የሳቅ አለቃ - ወሰዶም አልመሰለው ሳቅ አማረው -  እግዜርም እንደሰው! (የሳቁ ፀሀይ - ነጻነት ወርቅነህ) ነፍስህን ይማርልን! -    -    -    /   /   -     -     - ኤልያስ ሽታሁን

ሰላም የግጥም ወዳጆች እንዴት ናችሁ 🥰👋 ተስፋ ቡና 5ኪሎ ብሔራዊ ሙዚየም ግቢ ውስጥ እጅግ ያማረ ቤት መክፈቱን በማስመልከት የግጥም ምሽት አዘጋጅቶላችኋል የፊታችን ቅዳሜ ጥር 9 ከ 11 :00 ጀ
ሰላም የግጥም ወዳጆች እንዴት ናችሁ 🥰👋 ተስፋ ቡና  5ኪሎ ብሔራዊ ሙዚየም ግቢ ውስጥ እጅግ ያማረ ቤት መክፈቱን በማስመልከት የግጥም ምሽት አዘጋጅቶላችኋል  የፊታችን ቅዳሜ ጥር 9  ከ 11 :00 ጀምሮ የግጥምና የሙዚቃ ድግስ ይኖረናል  ። መግቢያ በነፃ ሲሆን  ክፍት መድረክ ስላለ  የስነፅሑፍ ችሎታ አለን የምትሉ ስራዎቻችሁን ማቅረብ ትችላላችሁ።    

ወደ ተቀጣጠርንበት ቦታ ስትመጣ አኩርፋ ነበር። "ምን ሆነሻል?" አልኳት... "ቆይ እኔ ግንባራም ነኝ?" አለችኝ። ግንባሯን ለመጀመሪያ ግዜ አስተዋልኩት። ውስጤን እንዴት ልዋሸው? ፀጉሯ ሸሸት ስላለ ግንባራም ናት። 'ግንባር ግን ምን ያክል መጠን ሲኖረው ነው ነገሩን ለወጥ አድርጎ ግንባራም የሚያስብለው?.... ግን ደግሞ እከሌ ግንባር ቀደም ሚና ነው የተወጣው ተብሎ ይሞገስስ የለ?...ስንቱ ግንባራም ኳስ ተጫዋች አይደለ እንዴ መረቡን በቴስታ እየወዘወዘው ሰውን ሁሉ የሚያስፈነጥዘው? ለምን ግንባራምነት ስድብ ይመስላል... ወይ ግንባራም...' ምላሽ ጠፍቶብኝ ውስጤ ዘላበደ... "እ መልስልኛ?" አለች ... አንገቷን ስግግ እያደረገች "ቆይ ማነው እንዲ ያለው?" አልኩ ኮስተር ብዬ " አታውቀውም..." አለች እንዴት ቢደፍረኝ ነው እይነት ራሴን እየነቀነኩ.... ለመልሴ ፋታ ወሰድኩ። እንዴት እዳ ገባሁ ጎበዝ?! 'አዎ ግንባራም ነሽ' ብላት ገና አግብቻት ደርስበታለሁ ያልኩትን ሰማንያ እዛ ጋ እንደምቀደው ገባኝ። 'አይ ግንባራም እንኳን አይደለሽም' ብላት እውነቱን ውስጧ ስለሚያውቀው አሽሟጠጠኝ ብላ እንደምታስብ ቀድሜ ተረድቻለሁ። የሴት አስተሳሰብ ከባድ ነው....እንቆቅልሽ...እንቆቅልሽ በሉት። "ሀገር ልስጥሽ በቃ" ብለህ ካላለፍካት በስትቀር በዚም ብትገለብጠው በዛም ብትገለብጠው ነገሩ አንድ ሆኖ ተገኘዋለህ።....በአለም ላይ  ከኖረ ተባዕት ፍጡር ላፈቀራት ሴት ለሚመልሰው ነገር  ሳይጨነቅ ፈታ ብሎ ሲናገር የኖረው አዳም ብቻ ይመስለኛል... የት ትሄድብኛለች ብሎ ይጨነቃል? ለምሳሌ ሄዋን አዳምን "ግንባራም ነኝ?" ብላ ብትጠይቀው "ዝም በይ ግንብ ልሾ ....ያን ከመሰለ ገነት በጥብጠሽ አባረሽኝ መስሎኝ የምድርን እሾህ ስጠርግ የኖርኩት...." ብሎ ኩም ያደርጋት ነበር። አሁንም ይቺ ከፊቴ ያለችን እንስት አዳማዊ ስልትን በመጠቀም ኩም ላድርጋት ብል አይሆንም። ስለዚህ ነገሩን አቅጣጫ ማስለወጥ ግድ ይለኛል። "መልስልኛ ....ወይስ አንተም እንደዛ ነው የምታስበኝ?" አለች መጠነኛ ቁጣ ቀላቅላ " ዓይንሽ እንደምወድልሽ ታውቂያለሽ አይደል?" አልኳትና በሂደት የግንባር ነገር በዓይን ተፈታ። ሀሳቧን የገለበጥኩት እንደ ጎበዝ ፑል ተጫዋች ነው። ወንድ ልጅ ሆይ! ፍቅረኛህ "የተኳልኩት ኩል ያስጠላል?.." ብላ ከጠየቀችህ። "የእግርሽ ጥፍር ቀለም ያምራል" ብለህ ዞር ማለት አለብክ አራት ነጥብ....ለምን ብላችሁ እንዳትጠይቁ... ምክንያቴን ያወቀ ያውቀዋል። እንግዲ እንዲህም ሆኖ ከዚች ልጅ ጋ ዓመት አልዘለቅንም.... ዋሽታኝ ከሌላ ሰው ጋ ስትወሰልትብኝ ያዝኳት። በእኔ ላይ ከደረበችው ልጅ ጋ ያላትን ግንኙነት የሚያስረዱ ብዙ ምስሎች ከወዳጆቼ ከተላኩልኝ በኃላ ተከታትያት ለመጨረሻ ግዜ ሆቴል ውስጥ በፍቅር እየተመገቡ ሲጎራረሱ ያዝኳቸው... "እንዴት እንዲ ታደርጊኛለሽ..." ብዬ እየተንጨረጨርኩ ብዙ ከለፈለፍኩ በኃላ በመጨረሻም "ግንባራም..." ብዬ ሰደብኳት።እጅ ከፍንጅ ስለያዝኳት በሀፍረት ጎንበስ ብላ የነበረችው ልጅ ፍሬን እንደበጠሰ ሲኖትራክ በንዴት ተንደርድራ በወይን ጠርሙስ ልትፈነክተኝ ወደኔ ስትመጣ ሰዎች ያዟትና አገላገሉን።  ግንባራም የሚለው ስድብ ግን እንዴት እንደመጣልኝ አላውቅም። ሳላውቀው ይሄ የምትናደድበት ነገር ነው ብሎ ውስጤ አስቀምጦት ነበር መሰለኝ.... እኔ በእሷ ከተናደድኩት በላይ ተናደደች። ለአንድ ቀን ድንገት እንዲባርቅ ተቀባብሎ የተዘጋጀ መሳሪያ ይመስል እኔም ከምላሴ ቃሉ ሲባርቅ አልታወቀኝም። ሁላችንም አሁን ወዳጅ ካልነው ሰው ደካማ ጎን ላይ በሂደት የምንቃርመውና ለክፉ ቀን የሚሆን መስደቢያ ቃል  እናበጃለን መሰለኝ.... የቀኑ ቀን ከአፋችን ሲወጣ ግን አናገናዝበውም። እኔን ከሆቴሉ ሰዎች እያግባቡኝ ወጣሁ። "ቆይ እኔ ግንባራም ነኝ?" ብላ ልጁን እንደምትጠይቀው አልጠራጠርም። በዛው ተለያየን... Abrham F. Yekedas ጆይን / share   👇👇👇👇👇 @lij_werkneh_gitm @lij_werkneh_gitm @lij_werkneh_gitm

ባለመድሐኒት...2 ምሕረት ደግፍ|ኤልዔዘር ያ ባለመድኃኒት እኮ በእጆቹ መድሐኒት ሰጠኝ። ያውም እርሱ የመረጠውን። እኔ ይሄ ነው ያላልኩትን። እጆቹ እንዴት ያምራሉ! ለቅፅበት ቆሽሸው የሚያውቁ አይመስ
ባለመድሐኒት...2 ምሕረት ደግፍ|ኤልዔዘር ያ ባለመድኃኒት እኮ በእጆቹ መድሐኒት ሰጠኝ። ያውም እርሱ የመረጠውን። እኔ ይሄ ነው ያላልኩትን። እጆቹ እንዴት ያምራሉ! ለቅፅበት ቆሽሸው የሚያውቁ አይመስሉም። ምናለበት ዳበስ ቢያደርገኝ? ምናለበት ቁስሌን ቢጠርግልኝ? ምናለበት? መርዝ እንኳ ቢሰጠኝ ከመውሰድ ወደ ኋላ አልልም። የሚያድነኝ ይመስለኛል። ዛሬ እድል ቀንቶኝ ፊት ለፊት አገኘሁት። ነጭ ጋወን የደረበበት ጠይም ፊቱ ጥቁር ሰማይ ላይ የወጣች ጨረቃ አስመስሎታል። ጉንጮቹን የከበበው ፂም ለሰከንድ ፈገግ የሚልበት ጥርሱን ግርማ አላብሰውታል። ዘወትር አሻግሬ የማይበትን አስፓልት ተሻግሬ ወደ መድሐኒት መደብሩ ገባሁ። ፈገግ ብሎ ተቀበለኝ። ፈገግታው መድሐኒት ለመሸጥ የሚደረግ ሳይሆን ፍቅሬን ለመቀበል መስሎ ተሰማኝ። << ምን ልስጥሽ? >> አለኝ ከእኔ ፊት የነበረውን ሰው አስተናግዶ እንደጨረሰ (<< እ..እ..ፍቅር...አበባ...ቸኮሌት>> ምናለበት በሆነልኝ የቁም ሕልም ) << እ..እ..የራስምታት መድሐኒት >> << ለአንቺ ነው? >> አለኝ። ግንባሬን ነቀነቅሁለት። ጀርባውን አዙሮ ከአንደኛው መደርደሪያ ላይ መድሐኒት አንስቶ ሰጠኝ። በእጆቹ። አዎን በእነዚያ እጆቹ። የነበረኝ ጥልቅ ፍርሐት የለቀቀ መሰለኝ። ይሰማኝ የነበረው ደስታ ከድንጋጤ ጋር የተቀላቀለ መሆኑ ሕመምተኛ አስመስሎኛል። << ሕመም ሲሰማሽ 1 ፍሬ ውሰጂ >> አለኝ ፈገግ እያለ። ተቀብዬው ወጣሁ። የእጆቼን ጠረን ማግኋቸው። የራሴውን ጠረን ከመማግ በቀር ግን የተረፈኝ አንዳች ነገር አልነበረም። Telegram https://t.me/Elezerbooks

የታላቁ ሩጫ ቲሸርት የምትፈልጉ በ Inbox @lijwerkneh
የታላቁ ሩጫ ቲሸርት የምትፈልጉ በ Inbox @lijwerkneh

አወጣኋት ❗️ """"""""""""""""" ይኸው ከሄድሽ ወድያ.... ጀብዱ እንደ ፈፀመ፣ ልክ እንደ ወታደር አወጣኋት እያልኩ፣ አወራሁ ለመንደር የሰማኝ ሰው ሁሉ፣ አላምንም ይለኛል እውነት አወጣሀት
አወጣኋት ❗️ """"""""""""""""" ይኸው ከሄድሽ ወድያ.... ጀብዱ እንደ ፈፀመ፣ ልክ እንደ ወታደር አወጣኋት እያልኩ፣ አወራሁ ለመንደር የሰማኝ ሰው ሁሉ፣ አላምንም ይለኛል እውነት አወጣሀት? ብሎ ይጠይቀኛል ፧ ምን ብዬ ልመልስ..? ፧ አየሽ.............አወጣኋት ብልም አፌ የሚለውን፣ ልቤ ቢከጅልም ከልቤ አንቺን ማውጣት ፈፅሞ እኔ አልችልም። ፧ እናም ፧ ከልቡ አውጥቶሻል.... እረስቶሻል ቢሉሽ፣ እመኚኝ ውሸት ነው የቀዬው ሰውማ... የአፌን ነው እንጂ፣ የልቤን መች አየው ?                   / ልጅ_ወርቅነህ...✍✍ /    ጆይን / share   👇👇👇👇👇 @lij_werkneh_gitm @lij_werkneh_gitm @lij_werkneh_gitm

አንድ ባለመድሐኒት አለ ፤ እሱ የማያውቀኝ እኔ ግን የማውቀው። በየዕለቱ ሰላም አሳድረኝ የምለው እሱን ዐይቼ ከገባሁ በኋላ ነው። ከማታ ጸሎቴ ውስጥ የተካተተ ባለመድሐኒት። እርሱ። በቋንቋ አጠራሩ pharmacist ይሉታል። እኔ ግን ባለመድሐኒት ብዬዋለው። እኔን የሚያድን መድሐኒት ያለው እሱ ጋር ብቻ ይመስለኛል። አይገርምም! እንደቀልድ ዓመታት አለፉ ማለት ነው? አልኩ ለልሴ እንደሁልጊዜዬ ፊት ለፊት ካለው አስፓልት ወደ መድሐኒት መደብሩ አተኩሬ እያየሁ። እሱ አያየኝም። እኔ ከርቀት አየዋለሁ። ሁልጊዜም ሼል ላይ ነው። ታማሚ አይጠፋም። እሱም መድሐኒት በእጁ ሞልቶ የፈሰሰለት ነው። ከርቀት ማየት የሰለቸኝ እና ናፍቆት ያየለብኝ ቀን ያልታመምኩትን ታምሜ መድሐኒት ለመግዛት እሄዳለሁ እሱም በትህትና አስተናግዶ ይሸሸኛል። ይሄኔ ነው ፍቅሩ የሚብስብኝ። የገዛሁትን ሁሉ ቃሚው ቃሚው ይለኛል። ምናልባት ስታመም እሱ ጋር ይወስዱኝ ይሆናል ብዬ ይሆን እንጃ? ያንን ነጭ ጋወን ለብሶ ሳየው ፍክት እላለሁ። ውበቱን ብነግረው ምንኛ ደስ ባለኝ። ፍቅሬን ነግሬው ልቤን ባሳረፍኳት በወደድኩ ነበር። ግን አጠገቡ ስደርስ የመድሐኒት አሊያም የበሽታ ስም ይቀድመኝና እተወዋለሁ። ቆይ ግን እስካሁን ለምንድነው ሕመሜን ያልተረዳልኝ? እንጃ? Š ምሕረት ደግፍ|ኤልዔዘር ጆይን /join/         👇👇👇👇 @lij_werkneh_gitm @lij_werkneh_gitm @lij_werkneh_gitm

【ከ‘ሌላ ሰው’ 】 ‘ለዛሬ’ በጊዜ ውስጥ ትናንት የትዝታ ፣ ነገ ደግሞ የተስፋ ጎተራ ናቸው ። ካመለጠ ትናንት ያልመጣ ነገ ይሻላል ። በእጅ ያለ ዛሬ ግን ከሁሉም ይበልጣል ። ––– ዛሬ ሁሌም ያለ
【ከ‘ሌላ ሰው’ 】 ‘ለዛሬ’ በጊዜ ውስጥ ትናንት የትዝታ ፣ ነገ ደግሞ የተስፋ ጎተራ ናቸው ። ካመለጠ ትናንት ያልመጣ ነገ ይሻላል ። በእጅ ያለ ዛሬ ግን ከሁሉም ይበልጣል ። ––– ዛሬ ሁሌም ያለ እየመሰለ የማይደገም ተመልሶም የማይመጣ ላንድ አፍታ ለቅፅበት ታይቶ ዳርቻ ከሌለው የዘላለም ጠፈር ገብቶ የሚሰወር በትናንትና በነገ መሃል የተሸነቆረ እንቁ ነው። የዛሬ ሚስጥሩና ጉልበቱ ያለው ‘ አሁን ’ላይ ነውና ። ––– ‘ቅድም’ እና ‘በኃላ’ ግን ያለቦታቸው ዛሬ ውስጥ የተደነቀሩ የትናንትናና የነገ ሽርፍራፊዎች ናቸው ። (ገፅ : 36 –37) (ዶ/ር ምህረት ደበበ) መልካም ዛሬ!

አስደግማብኝ ነው...❗️ ለሰባት ጠንቋይ ልጅ ለደብተራ ምርኩዝ ጠጠር ገበጣ አርጋ ላኬር እጣው እርኩዝ "ይቺን ያየ" አስብላ መሬት ልታስገባ ደቼ ልታስበላ የስር ማሽ እንጉዳይ የኮከብ ቆጣሪ የነ መገ
አስደግማብኝ ነው...❗️ ለሰባት ጠንቋይ ልጅ ለደብተራ ምርኩዝ ጠጠር ገበጣ አርጋ ላኬር እጣው እርኩዝ "ይቺን ያየ" አስብላ መሬት ልታስገባ ደቼ ልታስበላ የስር ማሽ እንጉዳይ የኮከብ ቆጣሪ የነ መገን ቦቃ የነ ጥና ጠሪ እንደርቢ ቁጣ የአመድ ላይ ዘዋሪ ለመቃብር አፈር መንገድ ላይ ቀጣሪ መተተኛ ፍቅር ልብ ላይ ቀባሪ የቀን ስደተኛ አርጋኝ የሌት ዟሪ አቅሌን እያሳተች ምታስብለኝ እሪ አስደግማብኝ ነው*²... "በርሶ መጀን" ብላ የልቤ ሳይበቃት ልቦናየን በልታ ጨፌ እየነከሰች በጉልበት ተደፍታ ኩራቴን ልትነጥቀኝ ኮርታ ልትማታ ተማ'ታም ልትረታ ጥላዬን ጀማው ፊት መሬቱ ላይ ዘርታ "ያዙልኝ" እያለች በጠንቋይ ቱፍታ መለመላ ነፍሴን ወናየን ዘርግታ 'ታሞ ይኑር' ብላ እኔን አስወግታ እርጋታዬን ነጥቃ እኔን ከኔ አጣልታ በደብተራው ምርኩዝ ባስነካችው ኩታ እንዳነክስላት ጅስሜን አስመትታ ህልሜን እንዳልሰማ ልቤን አስደብታ አስደግማብኝ ነው "ናልኝ" ብላ ጠርታ የሆንኩ አንገት ደፊ የሆንኩት ከርታታ መለየት ያቃተኝ ቀኑንና ማታ አስደግማብኝ ነው*².. ለነ ጥላ ወጊ ለመጫኛ ነካሽ ለነ አፍዝ አደንግዝ ለዱር ቅጠል በጣሽ ላውልያ ለጠንቋዩ ለኑግ ቂጣ ቆራሽ ለመንገድ ገርጋሪ ለውቃቢ ዘራሽ ለገሃድ ስውሩ ለነ ጽናት አፍራሽ ለምድር ላየሩ ለየሎስ አጎንባሽ ለባህር ለየብሱ ለጠቋሪት ደጋሽ አስደግማብኝ ነው ወለም ያላለኝን ዘላለም የምታሽ አስደግማብኝ ነው...!                                              @ሰለሞን ሳህለ         ጆይን /join/         👇👇👇👇 @lij_werkneh_gitm @lij_werkneh_gitm @lij_werkneh_gitm

ትንሽዬ ነፍስ አለችኝ! ቢቻልማ ኖሮ ትዝብቱ ተቀብሮ ያለማሰላሰል ቃላት ሳይመሰል ማን ላይ ተብሎ እንጂ? ሁሉ መቅብጥ ይሻል እንደህጻን ቅጂ:: ፂሜ የከለላት ድምፄ ያሰለላት ክብሬ የደበቃት ክበቤ ያነቃት ቢቻላት የምትነፍስ ብትፈልግ የምትፈስ አለችኝ! ትንሽ ነፍስ! ህጻን ሆና የምትድህ ማይገባት መርቀቀህ ደስታ ቀበጥ እምቡጥ ቀምበጥ ፊት የሌላት ወይ ተከታይ ሁሉን ትልቅ አርጋ ምታይ ካገኘችው የማትስቅ ከምትስቀው የማትርቅ ለእቃቃ ምትነሳ ሰው ሳትፈራ የምትፈሳ ባለጌ ናት የማትባል የማይገባት ቃል አባባል ትንሽዬ ነፍስ አለችኝ! ሾሹ ገላ ቅፅበት ተድላ ኩርፊያ አይጣል ለምቦጭ መጣል የምትፈለግ የምወዳት የደብቅኳት የናፈቅኳት ስጎለመስ የተወችኝ ትንሽዬ ነፍስ አለችኝ::     ጆይን /join/         👇👇👇👇 @lij_werkneh_gitm @lij_werkneh_gitm @lij_werkneh_gitm

ናፍቆት በገደለኝ!! ልትቀብረኝ በመጣህ፣                 እኔም ባገኘዉህ፤ ለቀብር ለሰልስት በማታ በካርታ፣                 በመክብብ ጨዋታ፤ በምሽት በወጉ፣ ድንኳን ስጠብቁ፤ ደግሞ ተደጋግሞ ለአርባ ለሰማኒያ፣                   ከእኔ እንዳትጠፋ፤ ለተስካር ሙት አመት፣ ለሰባት ለአስራ ሁለት፤ ምነዉ በገደለኝ! ናፍቆት ሞት ቢሆነኝ፤ ሁሌ ሁሌ ሁሌ እንድታባብለኝ፤ ናፍቆት በገደለኝ!!                      ✍ ረድኤት ተረፈ ጆይን /join/         👇👇👇👇 @lij_werkneh_gitm @lij_werkneh_gitm @lij_werkneh_gitm

🌜🌜🌜🌜 . . .....ትዝ ይልሃል ያኔ እቅፍህ ከተኸኝ ተቀምጠህ ከጎኔ፤ በተመስጦ ሆነን ጨረቃን ስናያት፤ ልባችን ያለዉን በሚስጥር ስንነግራት፤ ትዝ ይልሃል አይደል....... ላልከዳህ ላትከዳኝ በስሟ ስንምል፤ ዛሬ ቀኑ ከፍቶ ቅናት ይሆን በደል፤ .....አመል አይሉት እድል፤ መሐላችን ጠፍቶ ተጓዝን ለየቅል፤ መገኘት ከፈለክ ከምንወደዉ ስፍራ .....እጠብቅሃለሁ ከጨረቃ ጋራ። ............................................. ✍ዔደን ታደሰ ጆይን /join/     👇👇👇👇 @lij_werkneh_gitm @lij_werkneh_gitm @lij_werkneh_gitm