cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

Yene Tube®

Ko'proq ko'rsatish
Mamlakat ko'rsatilmaganTil ko'rsatilmaganKategoriya ko'rsatilmagan
Advertising posts
712Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Обуначиларнинг ўсиш даражаси

Ma'lumot yuklanmoqda...

በአድዋ ከተማ ሚያዚያ 4/ 2013 ዓ.ም፣ ሰኞ ረፋዱ አካባቢ የኤርትራ ወታደሮች በከፈቱት ተኩስ ነዋሪዎች እንደተገደሉና እንደቆሰሉ ተገልጿል። በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የአክሱምና የማእከላይ ዞን ጸጥታ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ተኩሱ በኤርትራ ወታደሮች መፈፀሙን አረጋግጠው ቢያንስ አንድ ሰው እንደሞተ ሲገልጹ፤ ነዋሪዎች በበኩላቸው ስምንት ሰዎች መሞታቸውን ይናገራሉ።ስሙ እንዳይገለጽ የጠየቀው የአክሱም ሆስፒታል ዶክተር ከትናንት ረፋድ ጀምሮ እስከ ከሰአት 20 የቆሰሉ ሰዎች ከአድዋ እንደመጡ ለቢቢሲ ተናግሯል።አለም አቀፉ ድንበር የለሽ የሐኪሞች ማህበር ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ከአድዋ ሆስፒታል እንዳመጣቸው የሚናገረው ይህ ዶክተር "ሁለት ሴቶች የሚገኙባቸው 20 ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች እያከምን ነው" ብሏል። [BBC] @Yene_Tube_Official
Hammasini ko'rsatish...
ሀብታቸውን በትክክል ያላስመዘገቡ 10 የመንግሥት ተሿሚዎች ለጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ተላልፈው ሊሰጡ መሆናቸው ተገለፀ፡፡ የፌደራል የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን የህዝብና አለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ አዲስ ለማ ለአሐዱ እንዳሉት በ2013 ዓ.ም ኮሚሽኑ የሀብት ማስመዝገብ እና የተመዘገበን ሀብት የማጣራት ስራ ሰርቷል፡፡ ሀብታቸውን በትክክል ያላስመዘገቡ 10 የመንግሥት ተሿሚዎች ስም ዝርዝርን የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ተጨማሪ ምርመራ እንዲያደርግባቸው ለማስተላለፍ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በተጨማሪ የተመዘገበን ሀብት የማጣራት ስራ በዋናነት የሙስና ተጋላጭነትን እንደሚቀንስ ያነሱት ዳይሬክተሩ፤ በቀጣይ የሚሰሩ ስራዎችን አጠናክረው እንደሚያስቀጥሉም ተናግረዋል፡፡ [አሐዱ ራድዮ] @Yene_Tube_Official
Hammasini ko'rsatish...
🙈🙈🙈🙈🙈🙈🙈አረ የፎቶ አነሳስ እስታይል እዩልኝ 🤭🙄 እነዚን እና የአርቲስቶችን ፎቶ ለማየት እንዲሁም የአርቲስቶቻችንን መረጃ ማግኘት ከፈለጋችሁ Join our channel Join👇👇👇👇 https://t.me/joinchat/RWerTUTKCAF4F1RE
Hammasini ko'rsatish...
🔥🔥JOIN🔥🔥
👁‍🗨 Preview
🔥🔥🔥 Open 🔥🔥🔥
🙈🙈🙈🙈🙈🙈🙈አረ የፎቶ አነሳስ እስታይል እዩልኝ 🤭🙄 እነዚን እና የአርቲስቶችን ፎቶ ለማየት እንዲሁም የአርቲስቶቻችንን መረጃ ማግኘት ከፈለጋችሁ Join our channel Join👇👇👇👇 https://t.me/joinchat/RWerTUTKCAF4F1RE
Hammasini ko'rsatish...
ድምጽን ብቻ በመጠቀም የኮቪድ 19 ተጠቂዎችን የሚለየው መተግበሪያ የሰዎችን ድምጽ ብቻ በመጠቀም የኮቪድ ተጠቂዎችን ለመለየት የሚያስችል በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዘ መተግበሪያ መሰራቱ ተሰማ፡፡ ይህ መተግበሪያም 80 በመቶ የደረሰ ትክክለኝነት እንዳለውም ተሰምቷል፡፡ እንደሚታወቀው ኮቪድ 19 የሚያሳየው ምልክት ከሰዎች ሰዎች የተለያየ በመሆኑ ተጠቂዎችን መለየት እጅግ አስቸጋሪ ነው፡፡ አንድ ሰው የጉሮሮ መከርከር፣ ሙቀት፣ ሳል ወይም የማሽተትና የመቅመስ ችግር ሲስተዋልበት የኮቪድ ምርመራ ማድረግ እንዳለበት ይመከራል፡፡ ይህንን ችግር የተመለከተው ቮካሊስ የተሰኘ ኩባንያ የኮቪድ ተጠቂዎችን ለመለየት የሚያስችል ድምጽንና የሞባይል መተግበሪያን የሚጠቀም ቴክኖሎጂን አበልጽጓል፡፡ ይህን ቴክኖሎጂ የተለየ የሚያደርገው ነገር በአንድ በቫይረስ የተጠቃም አካባቢ የሚገኙ ሰዎችን ለመለየት ሁሉንም ሰዎች ወደ ጤና ተቋም ማምጣት አስፈላጊ ቢሆንም ቴክኖሎጂው ልየታውን ለማድረግ ሰዎች ባሉበት ሆነው በድምጻቸው ብቻ ቫይረሱ በውስጣቸው መኖሩንና አለመኖሩን መለየት የሚያስችል መሆኑ ነው፡፡ ቴክኖሎጂው ይህን ለማድረግ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን ይጠቀማል፡፡ ቮቻሊስ የተሰኘው ድርጅት ከሰዎች ድምጽ ጋር የተያያዙ ሰፊ መረጃዎችን የሰበሰበ ሲሆን የቴክኖሎጂ ተቋሙ የህመም ስሜት የሚሰማቸው ሰዎች የሚኖራቸውን ድምጽ ሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የተሰበሰበውን የድምጽ መረጃ በመጠቀም የሚለይ ቴክኖሎጂን አበልጽጓል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ይህ ቴPከኖሎጂ በአሜሪካ፣ቺሊ፣ኢንዶኖዢያ፣ ደቡብ አፍሪካ እና ሉክሰምበርግ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ ቮካሊስ የተሰኘው መሰረቱን እስራኤል ያደረገው ተቋም በ2019 የተመሰረተ ሲሆን በያዝነው አመት በህንድ ሙባይ 2000 ታካሚዎችን በመመርመር ነው ስራውን የጀመረው፡፡ 👉 @Yene_Tube_Official
Hammasini ko'rsatish...
የጢስ ዓባይ ባህር ዳር የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ መስመር ምሰሶ ስርቆት ተፈፀመበት! ከጢስ ዓባይ የውሃ ኃይል ማመንጫ ወደ ባህር ዳር የተዘረጋው ባለ 132 ኮሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ መስመር ምሰሶ ላይ ስርቆት ተፈፀመ፡፡ ከሰኞ ምሽት ጀምሮ በተፈፀሙ ስርቆቶች ስምንት ምሰሶዎች ወድቀዋል፡፡ ይሁንና በአካባቢው ኃይል እንዳልተቋረጠ ማረጋገጥ ተችሏል፡፡ ምሰሶዎቹ በመውደቃቸው ከኃይል ማመንጫው በባህር ዳር ወደ ብሔራዊ የኃይል ቋት ይላክ የነበረ እስከ 30 ሜጋ ዋት ኃይል መላክ አልተቻለም፡፡ ችግሩንም በየደረጃው ለሚገኙ የመስተዳድር አካላት እንዲያውቁት የተደረገ ሲሆን የወደቁትን ምሰሶዎች በመጠገን ወደነበሩበት ለመመለስ የጥገና ስራ ተጀምሯል፡፡ Via EEPCo @Yene_Tube_Official
Hammasini ko'rsatish...
በኒጀር የተሞከረ መፈንቅለ መንግስት መክሸፉ ተገለጸ! በመፈንቅለ መንግስት ሙከራው የተሳተፉ በርካታ ግለሰቦች መያዛቸውን የሀገሪቱ መንግስት አስታውቋል።መፈንቅለ መንግስቱ የተሞከረው አዲሱ ተመራጭ ፕሬዝደንት ቃለ መሀላ ሊፈፅሙ ሁለት ቀናት ሲቀሯቸው ነው፡፡ Via Al ain @Yene_Tube_Official
Hammasini ko'rsatish...
በእነ አቶ ጃዋር የህክምና ጉዳይ፤ የፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር እና የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ፍርድ ቤት ቀርበው እንዲያስረዱ ትዕዛዝ ተሰጠ! የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከእነ አቶ ጃዋር መሐመድ የህክምና ጉዳይ ጋር በተያያዘ የፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር እና የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ችሎት ፊት ቀርበው እንዲያስረዱ ትዕዛዝ ሰጠ። ፍርድ ቤቱ ዛሬ ትዕዛዙን የሰጠው በተከሳሽ ጠበቆች የቀረበለትን አቤቱታ ከመረመረ በኋላ ነው። የተከሳሽ ጠበቆች አቤቱታ የቀረበለት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የጸረ ሽብር እና የሕገ መንግስታዊ ጉዳዮች ችሎት፤ “የፍርድ ቤቱ ውሳኔ እንዳይከበር ሚና ነበራቸው” ያላቸውን የፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ተወካዮችን ከዚህ ቀደም በነበረው ውሎው አስጠርቶ ጠይቋል። ተከሳሾች ወደ ህክምና ተቋም በመሄድ ላይ ባሉበት ወቅት፤ የነበሩበት ተሽከርካሪ “በመንገድ ላይ ታግቶ እንዲቆም አድርገዋል” የተባሉ ኃላፊ ደግሞ ለዛሬ ረቡዕ መጋቢት 22፤ 2013 እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር። የችሎቱን ትዕዛዝ ተቀብለው ዛሬ ችሎት ፊት የቀረቡት የፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን የፈጥኖ ደራሽ ኃይል አዛዥ ኢንስፔክተር መገርሳ ገሙ በዕለቱ የሆነውን ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል። እነ አቶ ጃዋር ወደ ላንድ ማርክ ሆስፒታል ሲወሰዱ አጅበዋቸው እንደበር የጠቀሱት አዛዡ፤ አፍሪካ ህብረት አካባቢ ሲደርሱ ተከሳሾቹ ያሉበት ተሽከርካሪ እንዲቆም በስልክ ትዕዛዝ እንደተላለፈላቸው ተናግረዋል። Via Ethiopian Insider @Yene_Tube_Official
Hammasini ko'rsatish...
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ትናንት በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የሰጡት ምላሽ ከአውድ ውጭ መወሰዱን አስታወቁ፡፡ መግለጫውን ተከትሎ የኢትዮጵያና የኤርትራ ህዝቦች በፌዴሬሽን ሊዋሃዱ ነው በሚል በዚህ ጉዳይ ላይ መንግስት ምን አቋም አለው የሚል ጥያቄ ቀርቦ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ለቀረበው ጥያቄም የተሰጠው ምላሽ አንዳንድ መገናኛ ብዙኃን በተለየ አውድ ማቅረባቸውን ነው የገለጹት፡፡ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ለኤርትራውያን ወገኖች ጉዳዩ ከአውድ ውጭ መወሰዱን እንዲያውቁ አሳስባለሁ ብለዋል፡፡የኢትዮጵያ መንግስትም ሆነ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለኤርትራ ሉዓላዊነት የማይናወጥ አቋም አላቸው ነው ያሉት፡፡እኔም በግለሰብ ደረጃ የኤርትራን ሉዓላዊነት አከብራለሁ ያሉት ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፣ ለተፈጠረው ብዥታ ይቅርታ እጠይቃለሁ ብለዋል፡፡ ምንጭ፡-የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር @Yene_Tube_Official
Hammasini ko'rsatish...
በዚ ድብርታም ሰአት የተገኘ ምርጥ እና አዝናኝ ቻናል መሳቅ ብቻ በቻናላችን :- - ሜም - ቪዲዮ 100% ምናምን ብዬ አልሰክስባችሁም 101 % ትደሰቱበታላችሁ :: ብቻ ከናንተ ሚጠበቀው Join ማለት ብቻ ማየት ማመን ነው 👇👇👇👇👇 👉 @sakbecha 👈 👉 @sakbecha 👈 👉 @sakbecha 👈
Hammasini ko'rsatish...
Join
Join
Join
JOIN