cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qilingÂť, bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

Ihsan Media #Eth🇪🇹

#ለወቅታዊና_ኢስላማዊ_ጉዳዮች https://t.me/Ihsan_media_1 https://ummalife.com/ihsan_midea https://www.youtube.com/@ihsan_media1 🇪🇹🇪🇹🇪🇹 ለአስተያየትዎ: @Best4123_bot

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
813
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-37 kunlar
-6230 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

Photo unavailableShow in Telegram
አብዱልፈታህ አልሲሲ ለቀጠይ 6 ዓመታት የግብፅ ፕሬዚዳንት በመሆን ተመረጡ ታህሳስ 8/2016 ባለፉት ሁለት የግብፅ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫዎች አሸናፊ የነበሩት አብዱልፈታህ አልሲሲ በተከተታይ ለ3ኛ ጊዜ መመረጣቸውን የሀገሪቱ ምርጫ ባለስልጣን ይፋ አድርጓል፡፡ ባለፈው ሳምንት በተጠናቀቀዉ የግብፅ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ላይ አብዱልፈታህ አልሲሲ የመራጮችን ከ 90 ከመቶ ድምፅ በማግኘት ዉድድሩን በመምራት ላይ መሆናቸዉ ሲዘገብ ነበር። በዚህም የግብፅ ብሔራዊ ምርጫ ባለስልጣን ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት አብዱልፋታህ አልሲሲ ከምርጫው 89 ነጥብ 6 በመቶ ድምፅ በማግኘት ለቀጣይ 6 ዓመታት ሃገሪቱን በፕሬዚዳንትነት እንደሚመሩ ተረጋግጧል፡ በዚህ ምርጫ ላይ 67.3 ሚሊየን ሰዎች ወይንም ከአጠቃላይ ድምፅ ለመስጠት ከፈቀዱ ተመዝጋቢዎች ዉስጥ 44.7 ሚሊየን ዜጎች ድምፃቸዉን ሰጥተዋል ተብሏል። በግብፅ አንድ ፕሬዚዳንት ለሁለት የስልጣን ዘመን ብቻ እንዲቆይ የሚያስገድደዉን ህግ ያሻሻሉት ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ አልሲሲ፤ በዚህም ከ2014 እና 2018 የምርጫ ዉድድሮች በኋላ በ2024 ምርጫውን በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የሃገሪቱ ፕሬዚዳንት በመሆን መመረጣቸውን አልጀዚራ ዘግቧል። #ለወቅታዊና_እስላማዊ_ጉዳዮች Join us 🇵🇸🇵🇸🇵🇸 https://t.me/Ihsan_media_1 https://ummalife.com/ihsan_midea https://www.youtube.com/@ihsan_media1 ለአስተያየትዎ: @Best4123_bot
Hammasini ko'rsatish...
👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
የከረም ሻሎም መተላለፊያ ወደ ጋዛ ሰብአዊ ድጋፎችን ለማስገባት ተከፈተ 79 ሰብአዊ ድጋፍ የጫኑ ተሽከርካሪዎችም በዚሁ መተላለፊያ በዛሬው እለት ወደ ጋዛ መግባታቸውን ነው ሬውተርስ የግብጽ ቀይ መስቀልን ጠቅሶ የዘገበው። እስራኤል ከጥቅምት 7ቱ የሃማስ ጥቃት በኋላ መተላለፊያውን መዝጋቷ ይታወሳል። የከረም ሻሎም መተላለፊያ ከራፋህ የድንበር መተላለፊያ በበለጠ ሰብአዊ ድጋፎችን ወደ ጋዛ ለማስገባት ያስችላል ተብሏል። እስራኤል መተላለፊያውን ለመክፈት መወሰኗ በጋዛ አስቸኳይ ድጋፍ ለሚሹ ሚሊየኖች ለመድረስ እንደሚያስችል ታምኖበታል። #ለወቅታዊና_እስላማዊ_ጉዳዮች Join us 🇵🇸🇵🇸🇵🇸 https://t.me/Ihsan_media_1 https://ummalife.com/ihsan_midea https://www.youtube.com/@ihsan_media1 ለአስተያየትዎ: @Best4123_bot
Hammasini ko'rsatish...
👍 1
ታላቅ ሃገር ታላቅ አየር ሃይል! የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዶክተር ዓቢይ አሕመድ የኢትዮጵያ አየር ኃይል የሠው አልባ የአየር ምድብን መርቀው ከፈቱ፡ ዶክተር ዓቢይ አሕመድ በከሠዓት áˆ˜áˆ­áˆ ግብሩ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ለመጀመሪያ ጊዜ ያሰለጠናቸውን እጩ መኮንኖች፣ የአውሮፕላን ጥገና ሙያተኞችን እና ፓይለቶችን እንደሚያስመረቁ ይጠበቃል። 88ኛው የኢትዮጵያ አየር ሃይል የምስረታ በዓል በልዩ ልዩ  ዝግጅቶቾ ቀጥሏል። Join us 🇵🇸🇵🇸🇵🇸 https://t.me/Ihsan_media_1 https://ummalife.com/ihsan_midea https://www.youtube.com/@ihsan_media1 ለአስተያየትዎ: @Best4123_bot
Hammasini ko'rsatish...
👍 2
Photo unavailableShow in Telegram
ፑቲን የምእራባውያን ማእቀብ አይበግረንም አሉ 06/2016 ዓ.ል. የምእራባውያን ማእቀብ ወደ ፊት እንዳንጓዝ አይጋርደንም አሉ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን፡፡ አሁን የተደራጀ የጦር መሳሪያ እና ጥሩ ብቃት ላይ እንገኛለን ወደ ፊት ለመጓዝ የሚያስፈራን ነገር የለም ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፡፡ የወታደሮቻችን አቅም የኢኮኖሚ ጥንካሬያችን እና ሩሲያዊ ትስስራችን በቀላሉ አይናድም ሲሉም አስታውቀዋል ፑቲን፡፡ ፕሬዝዳንቱ በዚህ ሳያበቁ በቀጣዩ ምርጫ አሸንፈው እስከ 2030 በክሬምሊን ከቆዩ የጠነከረችዋ እና ሉዓላዊ የምትሆነዋን ሩሲያን እፈጥራለሁ ማለታቸው ተሰምቷል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት 660ኛ ቀኑን አስቆጥሯል፡፡ Join us 🇵🇸🇵🇸🇵🇸 https://t.me/Ihsan_media_1 https://ummalife.com/ihsan_midea https://www.youtube.com/@ihsan_media1 ለአስተያየትዎ: @Best4123_bot
Hammasini ko'rsatish...
እስራኤል በስህተት የራሷን ዜጎች መግደሏን ገለጸች ጄይሉ ቲቪ ታህሳስ 6/2016 ለፍልስጤም ነጻነት እንደሚዋጋ የሚገልጸው ሀማስ ከ70 ቀናት በፊት በእስራኤል ላይ ያልተጠበቀ ጥቃት ማድረሱን ተከትሎ በአካባቢው ጦርነት ተቀስቅሷል። ይህን ተከትሎም እስራኤል የአጸፋ እርምጃ የጀመረችው ዘመቻ አሁንም የቀጠለ ሲሆን እስካሁን 19 ሺህ ፍልስጤማዊያን ተገድለዋል። በሐማስ የታገቱ እስራኤላዊያንን ለማስለቀቅ በሚል እግረኛ ወታደሮቿን ወደ ጋዛ የላከችው እስራኤል በስህተት ሶስት ዜጎቿን እንደገደለች ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ የእስራኤል ጦር ሶስቱን እስራኤላዊንን የገደለው በስህተት ጠላት መስለውት እንደሆነ አስታውቋል፡፡ በስህተት ተገደሉ የተባሉት ሶቱ እስራኤላዊያን የ28፣ የ26 እና የ22 ዓመት ወጣቶች ናቸው የተባለ ሲሆን ከ70 ቀን በፊት በሐማስ ታግተው እንደተወሰዱ ተገልጿል፡፡ ይህን ተከትሎም በርካታ ሀገራት እና እስራኤላዊያን የሀገሪቱን ጦር ድርጊት የተቹ ሲሆን የታገቱ ዜጎች በድርድር እንዲለቀቁ ግፊት በማድረግ ላይ ናቸው፡፡ እስራኤልን ኮንነው አስተያየት በመስጠት ላይ የነበሩ የቱርክ ፓርላማ አባል በልብ ህመም ህይወታቸው አለፈ የእስራኤል ጦር አስከሬን ሳይሆን ዜጎቻችንን ከነ ህይወታቸው ያምጣልን ሲሉ በርካታ ዜጎች በማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ በስፋት እየጻፉ ናቸው ተብሏል፡፡ ለእስራኤል የቀጥታ የጦር መሳሪያ ድጋፍ በማድረግ ላይ ያለችው አሜሪካ አሁን ላይ እስራኤል በጋዛ የተኩስ አቁም እንዲደረግ ጠይቃለች። ፕሬዝዳንት ባይደን ከሰሞኑ ባደረጉት ንግግር እስራኤል ያላት ዓለም አቀፍ ድጋፍ እየቀነሰ ነው፣ የተኩስ አቁም እንዲደረግ ለጠቅላይ ሚንስትር ኔታንያሁም ነግሬዋለሁ ብለዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን ጨምሮ በርካታ የዓለማች ሀገራት እስራኤል የተኩስ አቁም እንዲታወጅ ግፊት በማድረግ ላይ ሲሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በጦር ወንጀል እንዲጠየቁ በመወትወት ላይ ናቸው፡፡ እስራኤል በበኩሏ ከ70 ቀን በፊት በሐማስ ታግተው ከተወሰዱ ዜጎች ውስጥ 70 ዜጎች እስካሁን እንዳልተለቀቁ አስታውቃለች፡፡ #ለወቅታዊና_እስላማዊ_ጉዳዮች Join us 🇵🇸🇵🇸🇵🇸 https://t.me/Ihsan_media_1 https://ummalife.com/ihsan_midea https://www.youtube.com/@ihsan_media1 ለአስተያየትዎ: @Best4123_bot
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
ጦርነት ሱዳንን ወደ "መቅሰፍታዊ" ረሀብ እየመራት መሆኑ ተገለጸ ታህሳስ 5/2016 ተመድ እንደገለጸው 2/3 የሚሆነው የሀገሪቱ ህዝብ ወይም 30 ሚሊዮን ህዝብ የምግብ እርዳታ እንደሚፈልግ ገልጿል ጦርነት ሱዳንን ወደ "መቅሰፍታዊ" ረሀብ እየመራት መሆኑ ተገለጸ። በሱዳን፣ በጦርነት ቀጣና ወስጥ ያሉ ሰዎች በሚቀጥለው የበጋ ወቅት ከፍተኛ የረብ አደጋ ሊያጋጥማቸው እንደሚችል ተመድ አስጠንቅቋል። በጦርነት በደቀቀችው ካርቱም ውስጥ ያሉ ነዋሪዎች በጥቂት የእለት ከእለት ምግቦች ቀናቸውን እየገፉ ናቸው። ተመድ እንደገለጸው 2/3 የሚሆነው የሀገሪቱ ህዝብ ወይም 30 ሚሊዮን ህዝብ  የምግብ እርዳታ እንደሚፈልግ ገልጿል። እንደ ተመድ ከሆነ ይህ ቁጥር በፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች እና በሱዳን ጦር መካከል ግጭት ከመቀስቀሱ ከሚያዝያ አጋማሽ በፊት ከነበረው በእጥፍ ጨምሯል። በሀገሪቱ የምርት ወቅት 18 ሚሊዮን ሰዎች የምግብ እርዳታ እንደሚፈልጉ ተመድ ገልጿል። በተወሰነ የሀገሪቱ ክፍል 20 በመቶ የሚሆነው ቤተሰብ መቅሰፍታዊ ለሆነ የረሀብ አደጋ መጋለጡን ተከትሎ የረሀብ አደጋ በመንግስት ታውጇል። የደብሊውኤፍፒ ካንትሪ ዳይሬክር ኢዲ ሮዌ "ብዙ ቀጥር ያላቸው ሰዎች የእለት ምግባቸውን ለማግኘት እየታገሉ ነው፤ ነገሮች ካልተቀየሩ ይህን ማድረግ የማይችሉበት ከባድ አደጋ አለ" ብለዋል። ጦርነቱ የሱዳን ዋና ከተማ ከርቱምን አውድሟል፤ በዳርፉር የጎሳ ግጭት ተቀስቅሶ ግድያ እንዲፈጸም ምክንያት ሆኗል። ሁለቱ የጦርነቱ ተፋላሚዎች እርዳታ ለተጎጅዎች እንዳይደርስ በማስተጓጎል እርስበርሳቸው ይካሰሳሉ። #ለወቅታዊና_ጉዳዮች Join us 🇵🇸🇵🇸🇵🇸 https://t.me/Ihsan_media_1 https://ummalife.com/ihsan_midea https://www.youtube.com/@ihsan_media1
Hammasini ko'rsatish...
👍 2
ሱራ: አል-ከህፍ ቃሪእ: ተውፊቅ ሳይጝ #ጁሙዓህ
Hammasini ko'rsatish...
❤ 1
የአሜሪካና ኢራን የቀይ ባህር ፍጥጫ ታህሳስ 5/2016 በቴህራን የሚደገፉ የሃውቲ ታጣቂዎች በቀይ ባህር በሚጓዙ መርከቦች ላይ ጥቃት ማድረሳቸው ይታወሳል የሀገሪቱ መከላከያ ሚኒስትር ሞሀመድ ሬዛ አሽቲያኒ አሜሪካ በቀይባህር የሚጓዙ መርከቦችን ለመጠበቅ በሚል ከተለያዩ ሀገራት የሚውጣጣ ቡድን ለማዋቀው ማሰቧን አጥብቀው ተቃውመውታል። ዋሽንግተንና አጋሮቿ ወደ ቀይባህር የጋራ ግብረሃይል ከላኩ “ከባድ ችግር” ይገጥማቸዋል ሲሉም አስጠንቅቀዋል ሚኒስትሩ ኢስና ለተሰኘው የኢራን መገናኛ ብዙሃን በሰጡት ማብራሪያ ቴህራን ስለምትወስደው እርምጃ ያሉት ነገር የለም። “ማንም እኛ ከፍተኛ የበላይነት በያዝንበት ቀጠና መሰል እንቅስቃሴ ማድረግ አይችልም” ማለታቸው ተዘግቧል። የአሜሪካ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ጃክ ሱሊቫኒ ባለፈው ሳምንት አሜሪካ በቀይ ባህር የሚጓዙ መርከቦች ደህንነትን ለማስጠበቅ የሚረፋ የባህር ሃይል ወታደራዊ ግብረሃይል ለማቋቋም ከሌሎች ሀገራት ጋር ንግግር እያደረገች መሆኗን መግለጻቸው ይታወሳል። ዋሽንግተን ከዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰችው በኢራን የሚደገፉ የየመን ሃውቲ ታጣቂዎች በቀይ ባህር በሚጓዙ መርከቦች ላይ የሚሳኤልና ድሮን ጥቃት መፈጸማቸውን ተከትሎ ነው። ለሃማስ አጋርነታቸውን የገለጹት የሃውቲ ታጣቂዎች እስራኤል በፍልስጤማውያን ላይ የምታደርሰውን ጥቃት ካላቆመች ከቴል አቪ ጋር ግንኙነት ባላቸው መርከቦች ላይ ጥቃት እንደሚያደርስ መዛቱ ይታወሳል። ቡድኑ የየትኛውም ሀገር መርከብ ወደ እስራኤል የሚያቀና ከሆነ በሚሳኤል እመታዋለው ማለቱም አይዘነጋም። ከወር በፊት የብሪታንያን መርከብ ያገቱት የሃውቲ ታጣቂዎች በቅርቡ የኖርዌይ ሰንደቅ አላማ የምታውለበልብ መርከብን በክሩዝ ሚሳኤል መምታቱም የአለማችን 10 በመቶ የንግድ መተላለፊያ የሆነውን ቀይ ባህር ውጥረት ውስጥ ከቶታል። አሜሪካ እና ፈረንሳይም በቀይ ባህር ሊፈጸም ለሚችል ጥቃት የባህር ሃይላቸውን በተጠንቀቅ እንዲቆም ማድረጋቸውን ነው ሬውተርስ የዘገበው። የሃውቲዎች ዛቻና ጥቃት እንዲሁም የዋሽንግተን የጋራ ወታደራዊ ግብረሃይል የማሰማራት ውጥን የእስራኤልና ሃማስ ጦርነትን አድማስ እንዳያሰፋው ተሰግቷል። #ለወቅታዊና_እስላማዊ_ጉዳዮች Join us 🇵🇸🇵🇸🇵🇸 https://t.me/Ihsan_media_1 https://ummalife.com/ihsan_midea https://www.youtube.com/@ihsan_media1
Hammasini ko'rsatish...
Ihsan Media #Eth🇪🇹

#ለወቅታዊና_ኢስላማዊ_ጉዳዮች

https://t.me/Ihsan_media_1

https://ummalife.com/ihsan_midea

https://www.youtube.com/@ihsan_media1

🇪🇹🇪🇹🇪🇹 ለአስተያየትዎ: @Best4123_bot

👍 1