cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

ጠበቃ/የህግ አማካሪ⚖️

ማንኛውም አይነት የህግ ምክር ሲፈልጉ @Getsh_bot

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
763
Obunachilar
+324 soatlar
+47 kunlar
+2030 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

በኢንሹራንስ ኢንዱስትሪው በኩል ረዘም ላለ ጊዜ ሲጠበቅ የነበረው አዋጅ የሚኒስቴሮች ምክር ቤት ሊቀርብ እንደሆነ ተስምቷል።   እንደ ዋዜማ የመረጃ ምንጭ ከሆነም፣ በቀጣዮቹ ሳምንታት ለካቢኔ ይቀርባል ተብሎ የሚጠበቀው ረቂቅ፣ የአገሪቷ የኢንሹራንስ ድርጅቶችን አስመልክቶ የሚቆጣጠራቸውን አካል ከብሄራዊ ባንክ አስወጥቶ ሌላ እነርሱን ብቻ የሚመለከት ተቆጣጣሪ ተቋም ለማቋቋም ያለመ እንደሆነ ተሰምቷል።   በዓለም ባንክ አማካኝነት ከስድስት ዓመታት በፊት የተጀመረው የዚህ አዋጅ አስፈላጊነት ጥናት፣ የውጪ ኩባንያዎች ወደ አገር ቤት እንዲገቡ ምክረ-ሃሳብ እንደማያቀርብ ግን ምንጩ ጠቅሰዋል።  በዓለም ባንክ እና በብሄራዊ ባንክ ባለሙያዎች አማካኝነት ተረቆ አልቋል የተባለው ረቂቅ አዋጅ ላይ፣ የግል ኢንሹራንስ ድርጅት የቦርድ አባላትም ይሁኑ ከፍተኛ የአስተዳደር ኀላፊዎች ሃሳብ እንዳልተጠየቁ ያወሱት አንድ የዋዜማ ምንጭ፣ ‘የሚንስትሮች ምክር ቤት ከተመለከተው በኋላ እናወያያችኋለን’ መባላቸውን ለዋዜማ ነግረዋታል።     ከወራት በፊት የተሾሙት የባንኩ ገዢ ማሞ ምህረቱም፣ ይህ ተቋም እንዲቋቋም ጠንከር ያለ ግፊት ሲያደርጉ መቆየታቸውን ዋዜማ ተረድታለች። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ፣ በያዝነው ወር መገባደጂያ ይህንኑ ተቋም ለማቋቋም እና ከቀጣዩ በጀት ዓመት ጀምሮም የኢንሹራንስ ኩባንያዎቹ በዚህ ተቋም ስር እንዲሆኑ መወሰኑም ተሰምቷል። በዚህ አዋጅም፣ ግማሽ ክፈለ-ዘመን ለሚሆን ጊዜ የኢንሹራንስ ሴክተሩን ሲመራ የነበረው ብሄራዊ ባንክ፣ የመቆጣጠር ኀላፊነቱ የሚያበቃ ይሆናል።     የአገሪቷ የኢንሹራንስ ድርጅቶች፣ ካለፉት ጥቂት ዓመታት ወዲህ፣ የኢንሹራንስ ንዑስ ፋይናንሺያል ኢኮኖሚው በብሄራዊ ባንክ ቁጥጥር ስር መሆኑ ሊኖራቸው ይችል የነበረውን ዕድገት እንደገደበባቸው በተለያዩ መድረኮች ሲወተውቱ ሰንብተዋል። እንደ ኢንሹራንስ ኩባንያዎቹ አመራሮች እና ክፈለ-ኢኮኖሚውን በቅርበት እንደሚያውቁት ባለሙያዎች ገለፃ፣ ከሦስት ዐሥርታት በላይ የቆየው ይህ የቁጥጥር መስመር፣ አዳዲስ የኢንሹራንስ ድርጅቶች ወደ ክፈለ-ኢኮኖሚው እንዳይገቡ ከማገዱ ባለፈ፣ ተጨማሪ የኢንሹራንስ አገልግሎቶችን ለማቅረብ እጅጉን እንደገደባቸው ይናገራሉ። የባንኮች ቁጥር ሲጨምር፣ የኢንሹራንሶች ዕድገት ለማዝገሙም፣ ክፈለ-ኢኮኖሚው በብሄራዊ ባንክ ስር መሆኑ እንቅፋት ሆኖ መቆየቱም ይነሳል።     ልክ የዛሬ ዓመት፣ አዲስ አበባ ውስጥ በተካሄደ አንድ አሕጉር አቀፍ ስብሰባ ላይ በተናጋሪነት የተገኙት የብሄራዊ ባንክ ምክትል ገዢ ዶ/ር ሰለሞን ደስታ፣ የአገሪቷ የኢንሹራንስ ክፍለ-ኢኮኖሚ ለውጪ የኢንሹራንስ ድርጅቶች ክፍት እንደሚደረግ ተናግረው ነበር። ከዚህ በተጨማሪም፣ ለረዥም ጊዜ የኢትዮጵያ ዜግነት ብቻ በነበራቸው ባለሃብቶች ተይዞ የቆየው ኢንዱስትሪው፣ ከሦስት ዓመታት በፊት የባህር ማዶ ዜግነት የያዙ ትውልደ ኢትዮጵያውያንም እንዲሳተፉበት የሚያስችል አዋጅ በሕዝብ እንደራሴዎች እንዲፀድቅ መደረጉ ይታወሳል። ©ዋዜማ @ethiolawyer1 http://t.me/Ethiopianattorney1
Hammasini ko'rsatish...
ጠበቃ እና የህግ አማካሪ ⚖️

ምስጢራዊነቱን በጠበቀ ሁኔታ ለመወያየት እና ለመጠየቅ ከፈለጉ ከዚህ ግሩፕ በተጨማሪ @getsh_botን ይጠቀሙ

👍 4
✅ብታውቁት የስጦታ ውል አፈፃፀም ሥነሥርዓት የማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ መብትን የሚሰጥ ስጦታ ውል በግልጽ በሚደረግ ኑዛዜ አሠራር ዓይነት ካልተደረገ ፈራሽ እንደሆነ በፍትሃብሄር ሕግ አንቀጽ 2443 ላይ ተመላክቷል፡፡ግልጽ ኑዛዜ የሚደረገው ኑዛዜ ተናዛዡ እየተናገረ ማናቸውም ሌላ ሰው ወይም ተናዛዡ ራሱ የሚጽፈው ሲሆን ሕጋዊ አፈፃፀም ሥረዓቱም በፍትሃብሄር ሕግ ቁጥር 881 ላይ ተመላክቷል፡፡ የግልጽ ኑዛዛ አደራረግ ሕጋዊ ሥርዓት፡- 1. ኑዛዜው በተናዛዡ እና በአራት ምስክሮች ፊት ተነቦ ይኸው ሥርዓት መፈፀሙ በኑዛዜ ሰነዱ ላይ መጠቀስ አለበት፤ 2. ኑዛዜው የተደረገበት ቀን በኑዛዛው ሰነድ ላይ መጠቀስ አለበት፤ 3. ተናዛዡ እና አራቱም ምስክሮች ወዲያውኑ ፊርማቸውን ወይም የአውራ ጣት ምልክታቸውን በኑዛዜው ሠነድ ላይ ማኖር አለባቸው የስጦታ ውል በውልና ማስረጃ ያልተደረገ ቢሆንም በፍታብሄር ሕግ ቁጥር 2443 እና 881 መሠረት የግልጽ ኑዛዜ አደራረግ ሕጋዊ ሥርዓትን ተከትሎ ከተዘጋጀ በሕግ ፊት የፀና ይሆናል፡፡ ©AACAG @ethiolawyer1 @Getsh_bot ለጥያቄዎ http://t.me/Ethiopianattorney1
Hammasini ko'rsatish...
ጠበቃ እና የህግ አማካሪ ⚖️

ምስጢራዊነቱን በጠበቀ ሁኔታ ለመወያየት እና ለመጠየቅ ከፈለጉ ከዚህ ግሩፕ በተጨማሪ @getshbotን ይጠቀሙ

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ ደንበኞቻችን እና የጠበቃ/ህግ አማካሪ ቻናላችን አባላት በሙሉ እንኳን ለ1445ኛው ዓ.ሂ ኢድ አል አድሃ/አረፋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ።።።።።።።።። መልካም ይሁንላችሁ ኢድ-ሙባረክ!! http://t.me/Ethiopianattorney1
Hammasini ko'rsatish...
ጠበቃ እና የህግ አማካሪ ⚖️

ምስጢራዊነቱን በጠበቀ ሁኔታ ለመወያየት እና ለመጠየቅ ከፈለጉ ከዚህ ግሩፕ በተጨማሪ @getshbotን ይጠቀሙ

3👍 1
✍ የፌደራል የመንግሥት ሰራተኞች ረቂቅ አዋጅ - የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እየተወያየበት የሚገኘው የፌዴራል መንግሥት ሠራተኞች ረቂቅ አዋጅ የሠራተኞችን ሕገመንግሥታዊ መብቶች ይጥሳል የሚል ትችት እንደቀረበበት ሪፖርተር ዘግቧል። የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ቋሚ ኮሚቴው አባላት፣ አዋጁ ዝቅተኛ የደመወዝ ወለልን አለመወሰኑ፣ በደመወዝ ቦርድ ውስጥ የመንግሥት ሠራተኞች ተወካዮች በአባልነት አለመካተታቸው፣ የመንግሥት መስሪያ ቤት የበላይ ሃላፊዎች ሠራተኞችን ወደ ሌላ ቦታ አዛውሮ የማሠራት ሥልጣን መያዛቸውና የወሊድ ፍቃድ በሦስት ወራት ብቻ መገደቡ ተገቢ አለመኾኑን ለፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ሚንስቴር ሃላፊዎች መግለጣቸውን ዘገባው አመልክቷል። የመንግሥት መስሪያ ቤቶች የሥራ አመራር ጉባዔ የዲስፕሊን ጥሰት የፈጸሙ ሠራተኞችን የማባረር ሥልጣን መያዙንና፣ ሠራተኞች የይግባኝ አቤቱታቸውን ለፍርድ ቤት እንዳያቀርቡ የሚከለክል እንደኾነ በመግለጽ የቋሚ ኮሚቴው አባላት ተችተዋል ተብሏል። የሲቪል ሰርቪስ የሚሰጠዉን ምዘና አንድ የመንግስት ሰራተኛ በተከታታይ ሁለት ጊዜ ከመካከለኛው ዉጤት በታች ካገኘ በችሎታ ማነስ ምክኒያት ከስራዉ ሊሰናበት የሚችልበት አይነት ይዘትም አዋጁ በውስጡ አካቷል። የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የሰዉ ሀብት ልማት ፣ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በፌደራል መንግስት መንግስት ሰራተኞች ረቂቅ አዋጅ ላይ ዉይይት አካሂዷል። የሲቪል ሰርቪስ ህጎች ዴስክ ሃላፊ አቶ መስፍን ረጋሳ በረቂቅ አዋጁ ላይ የተደረጉ ማሻሻያዎችን እና ዝርዝር ጉዳዮችን አቅርበዋል። ሃላፊዉ በማብራሪያቸዉ በዉድድር የተመሰረት የስራ እድገት ፣ ቅጥር ፣ ድልድል እና ዝዉዉር እንዲደረግ በአዋጁ መሰረት በፈተና የሚደረግ ሲሆን በዚሁ ምዘና መሰረት አንድ የመንግስት ሰራተኛ በተከታታይ ሁለት ጊዜ ምዘናዉን ሁለት ጊዜ ከመካከለኛው ዉጤት በታች ካገኘ በችሎታ ማነስ ምክኒያት ከስራዉ ሊሰናበት እንደሚችል ደንግጓል ማለታቸዉን ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ሰምቷል። በረቂቅ አዋጁ የደሞዝ እርከን ፣ የደሞዝ ጭማሪ ፣ ጥቅማጥቅም እና ማበረታቻ ስርዓት ራሱን ችሎ ተደንግጓል ያሉ ሲሆን ከሌሎች ሀገራት በተወሰደ ልምድ የሜሪት እና ደሞዝ ቦርድ ተቋቁሟልም ብለዋል። ይህ ቦርድ የመንግስት ሰራተኞች ከደሞዝና ክፍያ ጋር የተያያዘ ስርዓቱን ነጻና ገለልተኛ የሲቪል ሰርቪስ ስርዓት በመመሪያው በተደነገገው መሰረት እንዲተገበር እንዲሁም ጉዳዮቹን ተመልክቶ ለሚኒስትሮች ም/ቤት የዉሳኔ ሃሳብ እንደሚያቀርብም አስረድተዋል። ከዚህ በተጨማሪ የመንግስት መስሪያቤቶች ቅጥር ከመፈጸማቸዉ በፊት ለሰራተኞች የብቃት ማረጋገጫ ስልጠና ሰጥተዉ በዉጤቱ መሰረት ቅጥሩ እንዲጸና ያዝዛል። እንዲሁም ለሰራተኞች የደረጃ እድገት ፣  የትምህርት እና የዉጪ እድሎችን በሚመለከትም በምን መልኩ እንደሚገኙ በአዋጁ ተደንግጓል ብለዋል። አዋጁ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ ተመርቶ በዝርዝር ዉይይት ይደረግበታል። ©wazema/Dagu @ethiolawyer1 @Getsh_bot ለጥያቄዎ http://t.me/Ethiopianattorney1
Hammasini ko'rsatish...
ጠበቃ እና የህግ አማካሪ ⚖️

ምስጢራዊነቱን በጠበቀ ሁኔታ ለመወያየት እና ለመጠየቅ ከፈለጉ ከዚህ ግሩፕ በተጨማሪ @getshbotን ይጠቀሙ

😢 2👍 1
ሰኔ 3፣ 2016 የህዝብ በዓላት እና የበዓላት አከባበርን ለመወሰን የወጣው አዋጅ በዛሬው እለት ፀደቀ፡፡ የፀደቀው አዋጅ በልማድ ሲከበር የቆየውን ግንቦት 20 ብሔራዊ በአልነቱ አስቀርቷል፡፡  የሰማዕታትን ቀን /የካቲት 12/ እና የብሔር ብሔረሰቦች ቀን ህዳር 29 መስሪያ ቤቶች ክፍት ሆነው ታስበው መዋላቸው ይቀጥላሉ፡፡ ምክር ቤቱ የህዝብ በዓላትና የበዓላትን አከባበር መወሰን የወጣውን ረቂቅ አዋጅ በአንድ ድምፅ ተአቅቦና በአብላጫ ድምፅ አፅድቆታል፡፡ በአገር አቀፍ ደረጃ የሰንደቀ ዓላማ ቀን የመከላከያ ቀን ፣ የሴቶች ቀንና ሌሎችም በዓላት ታስበው የሚውሉ ናቸው ተብሏል፡፡ አንድ አባል በበኩላቸው የብሔር ብሔረሰቦችን በዓል ተከብረው ከሚውሉ በአላት ውስጥ ለምን አልተካተተም ምክንያቱም ኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦች አገር ነች የሚል ጥያቄ አንስተዋል፡፡ ለጥያቄዎቹ ምላሽ የሰጡት የጤና ፣ ማህበራዊ ልማት ፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ከኮሚቴ ሰብሳቢ ወርቅሰሙ ማሞ አንድ በአንድ እንዲከበርና ታስቦ እንዲውል የሚያደርገው የሚያመጣው ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ተጠንቶ ነው ብለዋል፡፡ አዋጁ ተከብረው በሚሉ ብሔራዊ እና ሃይማኖታዊ በዓላት ለሕዝብ አገልግሎት ክፍት መደረግ አለባቸው ያላቸውን ተቋማትን ዝርዝር አስቀምጧል፡፡ በዚህም የእለት ከእለት ኑሮ አስፈላጊ የሆኑ የውሃ ፣ የመብራት ፣ የስልክ እና መሰረታዊ አገልግሎቶች የጤና ተቋማትና መድሃኒት ቤቶች ለሕዝብ ደህንነት አስፈላጊ የሆኑ የደህንነት ተቋማት የእሳት አደጋ ፣ መከላከል አገልግሎትና የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎቶች እንዲሁም ነዳጅ ማደያዎች ክፍት ሆነው እንዲውሉ በአዋጁ ተቀምጠዋል፡፡ ዛሬ የፀደቀው አዋጅ የዘመን መለወጫ በዓል በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አስተባባሪነት እንዲከበርም ያዛል፡፡ ©sheger fm @ethiolawyer1 @Getsh_bot ለጥያቄዎ http://t.me/Ethiopianattorney1
Hammasini ko'rsatish...
ጠበቃ እና የህግ አማካሪ ⚖️

ምስጢራዊነቱን በጠበቀ ሁኔታ ለመወያየት እና ለመጠየቅ ከፈለጉ ከዚህ ግሩፕ በተጨማሪ @getshbotን ይጠቀሙ

የአከራይና ተከራይ ህጋዊ ውል ምዝገባ ወቅት የመኖሪያ ቤት አከራይና ተከራይ ማሟላት ያለባቸው መረጃዎች ሰኔ 1/2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ የአከራይና ተከራይ ህጋዊ ውል በምዝገባ ወቅት ማንኛውም የመኖሪያ ቤት አከራይና ተከራይ ማሟላት ያለባቸው መረጃዎች፤- 👉በህግ አግባብ የተዘጋጀ የመኖሪያ ቤት ውል ሰነድ 👉የአከራይና ተከራይ የነዋሪነት መታወቂያ ፣ የመስሪያ ቤት መታወቂያ ፣ መንጃ ፍቃድ ፣ ፓስፖርት ፣ የጠበቃ ፍቃድ ፣ የሰራተኞች ጡረታ መታወቂያ ፣ የዩኒቨርሲቲ ወይም ኮሌጅ ተማሪ የሙያ ስራ ፍቃድ ኦርጅናል ኮፒ ፤ 👉የመኖሪያ ቤት ውሉ የሚመዘገበው በወኪል ከሆነ ህጋዊ ውክልና የሁለት ምስክሮች የታደሰ መታወቂያ ኦርጅናል ኮፒ፤ 👉አከራይ የመኖሪያ ቤቱን ለማከራየት የሚያስችል መብት እንዳለው የሚያሳይ ህጋዊ ሰነድ :- - የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ - ሰነድ አልባ ይዞታዎች መሆኑን ከሚመለከተው አካል ማስረጃ ወይም - በፍርድ አፈፃፀም የተሸጠ ንብረት ሰነድ ወይም የተከራየው ቤት በውርስ የተገኘ ሆኖ ስም ዝውውር ካልተፈፀመ የወራሽነት ማረጋገጫ ኦርጅናል እና ኮፒ ይዘው መገኘት እንዳለባቸው ከአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ @ethiolawyer1 @Getsh_bot ለጥያቄዎ http://t.me/Ethiopianattorney1
Hammasini ko'rsatish...
ጠበቃ እና የህግ አማካሪ ⚖️

ምስጢራዊነቱን በጠበቀ ሁኔታ ለመወያየት እና ለመጠየቅ ከፈለጉ ከዚህ ግሩፕ በተጨማሪ @getshbotን ይጠቀሙ

✅ጥያቄ ሰላም እንዴት ናቹ የሕግ አማካሪዎች በቅድሚያ  ሁሌም ለምትሰጡት መልካም አገለግሎት እጅግ በጣም ላመሰግን እወዳለው ሰቀጥል ጥያቄ ነበረኝ አንድ ሰራተኛ በ1አመት ውስጥ 16የእረፍት ቀናቶች ካሉት በየአመቱ ቀኑ ይጨምራል? 8አመት በግል ድርጅት ውስጥ ላገለገለ ሰራተኛ ምን ያህል የእረፍት ቀናቶች ይኖሩታል?የአመት እረፍትስ አሰሪው ሳያሰወጣው ቢቀር ሰራተኛው ይቃጠልበታል?ለምትሰጡኝ ምላሽ እጅግ በጣም አመሰግናለው ✅መልስ ለመጀመሪያው አመት 16 ቀን እረፍት ይኖረዋል ከዛ በየሁለት አመቱ አንድ ቀን እየጨመረ ነው የሚሄደው በምንም አይነት ሁኔታ ግን የዓመት እረፍት ከ 2 አመት በላይ አይራዘምም ይቃጠላል ስለሆነም ማንኛውም ሰራተኛ የሚኖረው የዓመት እረፍት በተገቢው ጊዜ የመጠቀም መብት ስላለው ከሁለት አመት በላይ ሳይጠራቀም የአመት እረፍትን መጠቀም ይገባል። @ethiolawyer1 @Getsh_bot ለጥያቄዎ t.me/Ethiopianattorney1 ይቀላቀሉን ወዳጅ ጓደኞቾን አድ ያድርጉ
Hammasini ko'rsatish...
ጠበቃ እና የህግ አማካሪ ⚖️

ምስጢራዊነቱን በጠበቀ ሁኔታ ለመወያየት እና ለመጠየቅ ከፈለጉ ከዚህ ግሩፕ በተጨማሪ @getshbotን ይጠቀሙ

የቤት አከራዮች ተከራዮችን ለማስወጣት የ2 ወር ማስጠንቀቂያ ጊዜ እንዲሰጡ የሚያስገድደው አዋጅ ከሰኔ 1 ጀምሮ ተፈጻሚ ይሆናል በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጋቢት 24  ቀን 2016 የጸደቀው 'የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1320/2016' ከሰኔ 1 ቀን 2016 ጀምሮ ተፈጻሚ እንደሚሆን ተገለጸ። አዲስ ማለዳ ከከተማ አስተዳደሩ ኮምኒኬሽን ቢሮ ባገኘችው መረጃ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ቅድስት ወልደጊዮርጊስ እንደገለጹት አዋጁ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር የተረጋጋ ፣ ግልፅነት እና  ተጠያቂነት ያለው እንዲሁም የአከራይ እና የተከራዮችን ጥቅም እና መሰረታዊ መብቶች ሚዛን በጠበቀ መልኩ ለመፈፀም የተደነገገ ነው። የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅን ለመተግበር የሚያስችል ውይይት ተካሄዷል። ስድስት ክፍሎችና 32 አንቀጾች ያሉት አዋጁ በውስጡ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል እና ዋጋ፣ የአስፈጻሚ አካላት ስልጣን እና ሌሎች ድንጋጌዎች እንደተካተቱበት አዲስ ማለዳ ማዘገቧ አይዘነጋም። በተጨማሪም የቤት አከራዮች ቅድመ ክፍያ መጠየቅ የሚችሉት የሁለት ወር ብቻ እንዲሆን የሚደነግግ ሲሆን ተከራዮችን ለማስለቀቅም የሁለት ወራት የዝግጅት ጊዜ እንዲሰጥ ያስገድዳል። ከዚህ ባለፈም መንግስት ማግኘት\ ያለበትን ግብር እንዲያገኝ እንደሚያስችል የምክር አባላት ገልጸው ነበር። (አዲስ ማለዳ) t.me/ethiopianattorney1 @ethiolawyer1 @Getsh_bot ለጥያቄዎ
Hammasini ko'rsatish...
ጠበቃ እና የህግ አማካሪ ⚖️

ለጥያቄዎችዎ @getshbotን ይጠቀሙ

👍 2
የብድርና የአደራ ውል ምን አይነት ሊሆን ይገባል? ***** 👉 የቃል እና የፅሁፍ ማስረጃ ከህግ አንጻር እንዴት ይታያል? አንዳንድ ሰዎች የዋህ ናቸው። ከነዚህ የዋሆች መሀል አቶ ጌታሁን አንዱ ይመስሉኛል። ምክንያቱም ሰኔ 5 ቀን 1997 ዓ.ም ለአቶ ታደሰ መኪና ገዝተን አብረን እስክንጠቀምበት ለጊዜው በአደራ አንተ ጋር ይቀመጥልኝ ብዬ በምስክር ፊት  መቶ ሰማንያ ሺህ ብር ቆጥሬ ሰጠሁት ነው የሚሉት። ከተወሰነ ጊዜ በኋላ አቶ ጌታሁን ገንዘቡን መልስልኝ ብለው ጠየቁት። አቶ ታደሰ ግን እንደሳቸው የዋህ አልነበረምና አልመልስም አላቸው። ይሄኔ አቶ ጌታቸው ‘‘ሕግ ባለበት አገርማ ብሬ ቀልጦ አይቀርም’’ ብለው አቶ ታደሰ ላይ ‘‘በአደራ የሰጠሁትን 180 ሺህ ብር ከነወለዱ ይመልስልኝ’’ የሚል ክስ አቀረቡ። የክሱ መጥሪያ የደረሳቸው አቶ ታደሰ  ለፌደራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በሰጡት መልስ አቶ ጌታቸው በአደራ የሰጧቸው ገንዘብ አለመኖሩንና በሕግ ተቀባይነት ያለው ማስረጃም አለማቅረባቸውን ጠቅሰው ተከራከሩ። ፍርድ ቤቱም የአቶ ጌታቸውን ምስክሮች አዳመጠና አቶ ታደሰ የተጠቀሰውን ገንዘብ መቀበላቸውን ስላረጋገጠ በየአመቱ የሚሰላ ሕጋዊ ወለዱ 9% ጨምረው የተቀበሉትን ገንዘብ እንዲከፍሉ ወሰነባቸው። ነገሩ በዚህ ቢቋጭ ጥሩ ነበር ሆኖም ግን ቀጠለ። አቶ ታደሰ ይግባኝ ለፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቢያቀርቡም ተቀባይነት ስላላገኙ በስር ፍርድ ቤት ውሳኔ ላይ የሕግ ስህተት ተፈጽሟል ይታረምልኝ ሲሉ ለፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሰበር አቤቱታ አቀረቡ። አቤቱታውም በአደራ ገንዘቡን መቀበሌን የሚያረጋግጥ በሕግ ተቀባይነት ያለው ማስረጃ ሳይቀርብብኝ ገንዘቡን እንድከፍል መወሰኑ ከሕጉ አግባብ ውጭ ነው የሚል ነበር። አቶ ጌታሁንም መጥሪያ ደርሷቸው ለሰበር ችሎቱ የስር ፍቤት የፈጸመው የሕግ ስህተት የለም ስለዚህ ውሳኔው ሊፀና ይገባል ሲሉ መልስ ሰጡ። ሰበር ችሎቱ የተከራካሪዎችን የፅሁፍ እና የቃል ክርክር እና አቤቱታ የቀረበበትን ውሳኔ ከሕጉ ጋር አገናዝቦ  መርምሮ የሰጠው  የመጨረሻው አስገዳጅ ፍርድ በየዋህነት በገንዘብ ጉዳይ ላይ ያልተጠነቀቅናቸው የሕግ ጉዳዮች ሚያስከፍሉትን ዋጋ የሚያሳይ ነው። 👉 ከአምስት መቶ ብር በላይ የዋህነትና ሰዎችን ማመን መልካም ነው። በገንዘብ ጉዳይ ግን መጠንቀቁ ይመከራል። በብድር ወይም በአደራ ገንዘብ ስትሰጥ ከብር 500 በላይ ከሆነ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል። ማድረግ ያለብን ጥንቃቄ ይሄ ነው። ገንዘቡን የምንሰጠው ሰው የፈለገ የቅርብ ጓደኛችን ቢሆን የእናትም ልጅ ቢሆን መጠኑን ጠቅሰን ገንዘቡን እንደሰጠነውና መስጠታችንንም ቢያንስ ሁለት ምስክሮች ማየታቸውን  ገንዘቡ መቼ እንዲመለስ እንደተስማማችሁ የሚጠቅስ ውል መፃፍና አበዳሪ/አደራ ሰጪም ሆነ ተቀባይ እንዲሁም ምስክሮች የፈረሙበትን ውል ለማስረጃ መያዝ ያስፈልጋል። ወረቀት የያዘውን ስለማይለቅና እንደ ሰው ቃሉን ስለማያጥፍ በሕግ  ፊት ከምስክር ቃል በላይ ይታመናል። 👉 ብድሩን እንዴት ማስረዳት ይቻላል እንደ አቶ ታደለ ገንዘቡ የተሰጠው ሰው አላውቅም ብሎ ቢክዳችሁና ፍርድ ቤት ብትሄዱ  ከ500 ብር በላይ የገንዘብ ብድርን ወይም አደራን ተበዳሪው ወይም አደራ ተቀባዩ ከካደ በፅሁፍ የሰፈረ የብድር ውል ወይም የአደራ ውል ካላቀረብን በምስክር ብቻ ለማስረዳት አንችልም። ያለው አማራጭ ፍርድ ቤቱ ፊት ተከሳሹ ቀርቦ ምሎ ገንዘቡም አለመውሰዱን እንዲያረጋግጥ መጠየቅ ብቻ ነው። አንዳንዱ ደግሞ ፈጣሪንም ሕግንም ስለማይፈራ ዓይኔን ግንባር ያድርገው ብሎ  ግጥም አድርጎ ነው ሚምለው። ፍርድ ቤት ደግሞ እንደምትጠይቀው የውል ግዴታ አይነት ሕጉ ተገቢ ያለውን ማስረጃ ካላቀረብክለት ምንም ሊያደርግልህ አይችልም። ገንዘብ በአደራ ስትሰጡ የታሸገ ከሆነ ከ500 ብርም በላይ ቢሆን በምስክር ፊት ከሰጣችሁ ምስክሮቹን አቅርቦ ማሰረዳት ይችላል። ሆኖም ቆጥራችሁ ከሰጣችሁት (ገንዘቡ ካልታሸገ)በሕጉ እንደ አላቂ የገንዘብ ብድር ስለሚቆጠር የተፃፈ ውል ከሌለ ገንዘባችሁን በፍርድ ቤት ከሳችሁ ማስመለስ አይቻልም። ምክንያቱም ሕጉ ከተጠቀሱት ማስረጃዎች ውጭ ሌላ አይነት ማስረጃ አይቀበልም። 👉 የትዳር አጋርን በሚመለከት በተጨማሪ ከ500 ብር በላይ ስታበድሩም ሆነ ስትበደሩ ወይም ዋስ ስትሆኑ የፅሁፍ ውል ማድረግ ብቻ ሳይሆን በተሻሻለው የፌደራሉ የቤተሰብ ሕግ መሰረት ካገባችሁ ሚስት ባሏን ባል ሚስቱን በውሉ መስማማቷ/ቱን  በውሉ ላይ በመፈረም ማረጋገጥ አለባ/በት። ካልሆነ በውሉ ላይ ስምምነቱን  ያልገለፀው ተጋቢ  ክስ አቅርቦ ውሉን ማስፈረስ ይችላል። አቶ ጌታቸውም በአደራ ቆጥሬ ሰጠሁ ያሉት ብራቸው እንደወጣ የቀረው በዚህ የተነሳ ነው። 👉 የሰበር ሰሚ ችሎቱ አስገዳጅ የሕግ ትርጓሜ ሰበር ሰሚ ችሎቱ ከላይ የጠቀስኳቸውን የገንዘብ አደራን እና ብድርን የሚመለከቱ የሕግ ድንጋጌዎች በመጥቀስ ‘‘አቶ ታደሰ ገንዘቡን አልወሰድኩም ብለው ከካዱ መቅረብ ያለበት የፅሁፍ ውል ነው። ይህ የፅሁፍ ውል ስላልቀረበና አመልካች ለጉዳዩ ተገቢነት ያለው ማስረጃ ባላቀረቡበት በምስክር ብቻ የስር ፍርድ ቤት 180 ሺውን ወስደዋልና ይክፈሉ ብሎ በመወሰኑ የሕግ ስህተት ስለፈፀመ ውሳኔውን ሽሬዋለሁ’’ በማለት አቶ ታደሰ በአደራ ተቀበሉ ተብለው የተከሰሱበትን 180 ሺህ ብር ሊከፍሉ የሚችሉበት ሕጋዊ ምክንያት የለም ብሎ የወሰነው። ውሳኔው የሰበር ውሳኔዎች ቅፅ 12 ላይ ታትሞ ወጥቷል። ለማንኛውም መሰል ጉዳዮች ሲያጋጥሙን አሁን ያለውን መተማመን ብቻ ሳይሆን በኋላ ሊያጋጥም የሚችለውን መካካድ በማሰብ ሕጋዊ ጉዳዮችን መጠንቀቅ ይመከራል። ©ከebc ፌስ ቡክ ገፅ @ethiopianattorney1 የመወያያ ግሩፕን ይቀላቀሉ ወዳጆችንም Add ያድርጉኝ @ethiolawyer1 @Getsh_bot ለጥያቄዎ
Hammasini ko'rsatish...
👍 6😁 1
✅ጥያቄ በአዲስ አበባ ከእጮኛዬ ጋር በማዘጋጃ ቤት ጋብቻ ልንፈፅም ፈልገን ነበር እና እንዴት ነው የጋብቻ ሰርተፍኬት የሚሰጠን አካል ጋር ቀርበን ጋብቻ መፈፀም የምንችለው? ✅መልስ እርስዎ ወይም እጮኛዎት ማለትም ከሁለት አንዳችሁ የአዲስ አበባ ከተማ የነዋሪነት መታወቂያ ካላችሁ የሲቪል/civil ጋብቻ ለመፈጸም በመንግስት አካል ፊት ቀርባችሁ መፈራረም ትችላላችሁ። (የአዲስ አበባ ከተማ የነዋሪነት ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 144/2015) @ethiopianattorney1 @ethiolawyer1
Hammasini ko'rsatish...
👍 1🤔 1
Boshqa reja tanlang

Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.