cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qilingÂť, bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

🇸🇦 SUNNAH MEDIA 🇸🇦

🇸🇦ቅድሚያ ለተውሂድ🇸🇦 🕋ቁርአን እና ሀዲስ🕋 ✍️የሰሀቦች ታሪክ⚔️🛡️🏹 ✍️ የሰለፎች ታሪክ ✍️የኡለሞች ታሪክ📝 👑የሙስሊም_መንግስታት_ ታሪክ⚔️ ⚔️የሙጃሂዶች_ታሪክ🛡️

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
9 134
Obunachilar
-324 soatlar
-357 kunlar
-22430 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

⛳️ ጁመዓ!!  ⛳️       , 🍃እናንተ ያመናችሁ ሆይ በአርብ ቀን ወደ ስግደት  በተጠራ ግዜ አላህን ወደ ማውሣት ሂዱ  መሸጥንም ተው ይህ የምታውቁ ከሆነ ለናንተ በላጭ ነው። ,  《ሡረቱል ፦ አል ጁሙአህ》                                                                                             በላጭ ቀናቹ የጁመዐ ቀን ነው   ረሡል ሠለላሁ አለይሒ ወሠለም "ፀሀይ ከወጣችባቸው ቀናቶች ሁሉ በላጩ ቀን የጁመዐ ቀን ነው ረሡል ሠለላሁ አለይሒ ወሠለም , ~ከላይ ያለፋት መለኮታዊ ንግግሮች በኢስላም ከሌሎች ቀናቶች ለይቶ  ለጁመአ ለት  የሠጠውን ደረጃ ያሣዩናል ይህን የተከበረ ቀን በምን መልኩ ማሣለፍ እንዳለብን ከነብዩ ሠለላሁ አለይሒ ወሠለም ዘንድ የመጡት በማውሣት እንተዋወስ ወደ መልካም ነገር ያመላከተ    እንደሠሪው ያክል መንዳ ያገኝበታል ። , =•የጁመአ ለት ሡብሒ ሠላት ያለው ደረጃ ,አላህ ዘንድ በላጩ ሠላት የጁመአ ቀን ሡብሒ በጀመአ መስገድ             《📚ሢልሢለቱ ሰሒህ》 ~ጁመአ ለት ሡብሒ ሠላት ላይ     ምንምን ሡራ ይቀሩ ነበር ?   , ~የአላህ መልዕክተኛ ሠለላሁ አለይሒ ወሠለምበጁመአ ሡብሒ ላይ   《አሊፍ ላም ሚም ተንዚሉ: ሠጅዳ》 እና   「ሀል አታ አለል ኢንሣኒ」               ይቀሩ ነበር       《📚ቡሀርና ሙስሊም》 , 🔺 በጁመአ ቀን ሠለዋት ማውረድ      ያለው ጥቅም ∴ , ~የጁመአ ቀን እና ማታ በኔ ላይ   ሠለዋትን አብዙ,በይሀቅይ ~በላጭ ቀናቹ የጁመአ ቀን ነው የዛ ቀን:     "አደም ተፈጠረ "ሞተ "ጡሩንባ ይነፋል "በህይወት ያለ ሁሉ ይሞታል በኔ ላይ ሠለዋትን አብዙ ሠለዋታቹ በኔ ላይ    የምትቀረብ ናት "    ~አስሀቡ ሡነንነወውይ        📚ሰሒህ ብለውታል 🚿የጁመዓ ቀን ገላን መታጠብ                                        አንደኛቹ ወደ መስጂድ ሢመጣ ገላውን ይታጠብ ,       《📚ቡሀርና ሙስሊም 》 , የጁመአ ቀን ሽቶ መቀባት ፣ ጥሩውን መልበስ ፣ረጋ ብሎ ሣይጣደፍ ወደ መስጂድ መሔድ በሁጥባ ወቅት ዝም ብሎ ማዳመጥ  ያለው ጥቅም ~የጂመአ ቀን የታጠበ, ሽቶ ካለውና ከተቀባ ,ጥሩ ልብስ የለበሰ , ወደ መስጂድ ሢሔድ በተረጋጋ መንፈስ ከሔደ ,ከተመቸውና ከሠገደ ,አንድንም ሠው ካላስቸገረ , ኢማሙ ሚንበር ላይ  ከወጣበት እስኪሠገድ ድረስ ዝም ያለ  በሁለት ጁመአዎች መሀል ያለውን ወንጀል ይማርለታል " , 🕐በግዜ መስጂድ መሔድ,የጁመአ ቀን መላይካዎች የመስጂድ በር ላይ ይቆማሉ ከዛ መጀመርያ ቀድሞ የሚገባውን ይፅፋሉ : መጀመርያ መስጊድ የሚገባው ግመል እንደሠጠ ከሱ ቀጥሎ ከብት ከሡ ቀጥሎ በግ ከዛም ዶሮ ከዛም እንቁላል ኢማሙ ሚንበር ላይ ሢወጣ መዝገቡን ዘግተው ሊያዳምጡ ይገባሉ  "        《📚ቡኸርና ሙስሊም 》 🚫 የጁመአ ቀን የተከለከሉ ነገሮች  ❗️ ኢማሙ ሁጥባ ሢያደርግ ማንኛውም አይነት ንግግር ክልክል ነው በመልካም ማዘዝም ከመጥፎ መከልከልም  ቢሆን  "ለጎደኛህ የጁመአ ቀን ኢማሙ ሁጥባ እያደረገ ዝም በል ካልከው ውድቅ የሆነ ነገር ሠርተሀል "ቡሀርና ሙስሊም አህመድ "ውድቅን ነገር የሠራ ከጁመአው ምንም ነገር የለውም "    የሚል ጨምረው ዘግበዋል , ~ዘግይቶ መስጂድ መምጣት እና ሠዎች አዛ ማድረግ "ረሡል ሠለላሁ አለይሒ ወሠለም ሁጥባ እያደረጉ አንድ ሠው በሠዎች ጀርባ ላይ እየተረማመደ ሢመጣ "ተቀመጥ! ሠዎችን አስቸገርክ" አሉትኝ , አላህ የተጠየቀውን ነገር የማይመ ልስባት አንድ ወቅት አለች #በጁምአእለት አንድ ሠአት አለች እሧን ሠአት አንድ ሙስሊም የሆነ ባርያ አያገኛትም  እሡ የሚሠግድ ሢሆን አላህን አንዳች ነገር አይጠይቀውም የሠጠው ቢሆን እንጂ " 《 ቡኻር እና ሙስሊም 》 , ~ ያቺ ሠአት መቼ ናት? በዚህ ዙርያ ኡለሞች የተለያየ አመለካከት ሠንዝረዋል ከሙስሊም በተዘገበ ሀዲስ ኢማሙ ሁጥባ ከጨረሰበት ሠላት እስኪሰገድ ያለው ክፍተት ነው "አቡ ዳውድ እን ነስእይ በዚህ መልኩ ዘግበዋል , ~ከጁመአ የመጨረሻው ወቅት ላይ ፈልጓት "በሌላ ዘገባ "ከአስር ቡሀላ والله اعلم وصلى الله على نبينا محمد وعلى آله وأصحابه وسلم
Hammasini ko'rsatish...
✍ብዙ ጀነት መግቢያ መንገዶች ተመቻችተውልን ይህን ማድረግ እንኳ ከበደን......አጂብ‼️ የአላህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ «ከየግዴታ (ፈርድ) ሶላት በሗላ አየተል ኩርሲይን (ከሱረቱል በቀራ አንቀፅ 255-256) የቀራ የሆነ ሰው ጀነት ከመግባት ምንም አይከለክለውም ሞት እንጂ።» ነሳዒይ ዘግበውታል
Hammasini ko'rsatish...
🔷  ሱፍይና አሕባሾች የዼንጤ ድልድዮች       በአሁኑ ጊዜ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ዼንጤዮች ጌታዋን የተማመነች ጊደር ጅራትዋን ውጪ ታሳድራለች እንደሚባለው የልብ ልብ ተሰምቷቸው እየዘመቱ ነው ። የአክፍሮት ዘመቻቸው በዋነኝነት ቀብር አምላኪዮችን ትኩረት ያደረገ ነው ።       ኢስላም ከጅምሩ የተዋጋው ኩፍር ቢኖር ቀብር አምልኮትን ነው ። የሚያሳዝነው ግን አሕባሽና ሱፍዮች ቀብር አምልኮትን ኢስላም አድርገው ለማህበረሰቡ በማቅረብ ዘጠና ከመቶ የሚሆነው ሙስሊም ቀብር አምላኪ እንዲሆን አድርገውታል ።      አሕባሽና ሱፍዮች ይህን ቀብር አምልኮ የሚቃወምን ከእስልምና የሚያስወጣ ተግባርና ክልክል መሆኑን የሚያስተምሩ የተውሒድ ሰዎችን ካፊር ይላሉ ። ማህበረሰቡ የዚህ አይነቱን አስተምሮ እንዳይሰማ በዚህ የተውሒድ ዳዕዋ የተሰማሩ የነብያት ወራሾችን ወሀብዮች በማለት እንደጭራቅ እንዲታዩ ያደርጋሉ ። ከዚህ አልፎ ተርፎ የተለያዩ አጋጣሚዮችን በመጠቀም እድሉን ሲያገኙ በማሳሰር በማስገረፍ የቻሉትን ይሰራሉ ።      የሱፍይና የአሕባሽ መሪዮች ወሀብዮች ከአባታችሁ የወረሳችሁትን እምነት ሊያስለቅቁዋችሁ ነው በምትችሉት ታገሏቸው ብለው የተውሒድ ሰዎችን እንዲገሉ ያበረታቱዋቸዋል ። ሞራል ይሰጡዋቸዋል ። ምስኪኖቹ የቀብር አምላኪዮች እስልምናችንን ሊያጠፉብን ነው ብለው የህይወት ዋጋ እስከመክፈል ራሳቸውን ያዘጋጃሉ ።     አላህን በብቸኝነት ተገዙ የሚሉ ዱዓቶችን ከከሀዲያን የበለጠ ይጠላሉ ።‼ የሚሉትን ለመስማት ቀርቶ ማየት አይፈልጉም ። 124 ሺህ ነብያት ሊዋጉት የተላኩበትን ቀብር አምልኮ ኢስላም ነው ብለው የነብያት ተከታዮችን ይዋጋሉ ። ነብዩ የተወጉለትን ፣ ደማቸው የፈሰሰለትን ፣ የተራቡለትና የተጠሙለትን ፣ የተሰደዱለትን ፣ ሶሓቦች የሞቱለትን ፣ ሰባ ሰማኒያ ቦታቸው የተወጉለትንና የተሰየፉለትን ተውሒድ ኩፍር ነው ይላሉ ። ‼     በተቃራኒው ያወገዙትና ኩፍር ነው ያሉትን ቀብር አምልኮ ኢስላም ነው ይላሉ ።      ይህ የሱፍይና የአሕባሽ መሪዮች አስተምሮና ተግባር ለዼንጤዮች ወርቃማ እድል ሆኖላቸዋል ። ይህን ክፍተት ተጠቅመው ቀብር አምላኪ ምስኪኖች ጋር ቀርበው እናንተ ሞቶ የበሰበሰን ከምታመልኩ ዒሳ ጌታ ነው ብላችሁ ለምን አትድኑም ቀናቶችን ከፋፍላችሁ ቁጭ ብላችሁ ጫት በመቃም እድሜያችሁን ከምትጨርሱ የሙታን መንፈስ እያመለካችሁ የሲኦል ከምትሆኑ እየሱስ ጌታ ነው ብላችሁ ለምን አትድኑም ይሏቸዋል ። ‼     ምስኪኖቹ አንድ ቀን ተውበት አድርገው ወደ አላህ ተመልሰው ዘላለማዊ ሕይወት የሚወርሱበትን እድል ትተው የዘላለማዊ ጀሀነም መሆንን ይመርጣሉ ።      ዒሳ ሁሉን ቻይ የሆነው ጌታ ኣደምን ያለ አባትና እናት ፣ ሓዋን ያለ እናት እንደፈጠረው ሁሉ ያለ አባት ከእናት ብቻ ሁን በሚለው ቃሉ ፈጥሮ ነብይ ያደረጋቸው መሆኑን የሚያስተምረውን ኢስላም ትተው በመርየም ማህፀን ውስጥ ማንኛውም ህፃን የሚያልፈውን ሂደት አልፈው ተረግዘው የተወለዱትን ዒሳን ፈጣሪ ብለው ይከፍራሉ ።     እነዚህ ምስኪኖች ዒሳ በመርየም ማህፀን ውስጥ ከረጋ ደም ጀምሮ የነበሩ ሂደቶችን አለረፈው ደሙ ስጋ ሆኖ ፣ ስጋው አጥንት ለብሶ ፣ ስጋና አጥንቱ ቅርፅ ይዞ የተለያየ የሰውነት ክፍል እንደ ልብ ፣ ሳንባ ፣ ጉበት ፣ ኩላሊት ፣ ዐይን ፣ ጆሮ ፣ አፍና አፍንጫ ፣ ጭንቅላትና አእምሮ ፣ እጅና እግር ፣ ሴልና ነርቭ ፣ የውስጥ ሜካኒካል ክፍልና የአእምሮ ኤሌክትሪካል ክፍል ተሟልቶለት ሙሉ ሰው እስኪሆኑ ፍጥረተ ዓለሙን ማን ነበር የሚያስተናብረው ? ‼     ብለው መጠየቅ አልቻሉም ። እየሱስ ጌታ ነው ሲባሉ እሺ ብለው ተቀበሉ ። ለዚህ የዳረጋቸው ከሱፍያና አሕባሽ የወረሱት የሙታን መንፈስ አምልኮት ነው ።      እነዚህ የሱፍይና አሕባሽ መሪዮች ወሀብዮችን በሚያስጠቁቁበት ልክ ከዼንጤ አያስጠነቅቁም ። ዼንጤ ልጆቻቸውን ሲከፍር ዱላ ይዘው አይወጡም ። እምነታችሁ ተነጠቀ አይሉም ። ዐቂዳችሁ ተነካ አይሉም ። በምትችሉት ታገሏቸው አይሉም ። የእነርሱ ወኔ በነብያት ወራሽ የተውሒድ ሰዎች ላይ ነው ።      ለዘህ ነው እነዚህ አካላት የዼንጤዮች ድልድዮች ናቸው ያልኩት ። የአሕባሽና ሱፍዮች የኩፍር ተግባር ነው ምስኪን ቀብር አምላኪያንን ወደ ከፋ ኩፍር ይዟቸው የሚሄደው ።       በጣም የሚያሳዝነው ነሲሓዎች ከእነዚህ ጋር ነው አንድ ነን ብለው ከኢኽዋንና ሱፍይ እንዲሁም አሕባሽ ጋር አንድነት በመፍጠር እኛ የኢትዮዽያ ሙስሊሞች ነን ያሉት ።‼      በየአካባቢያችሁ ያሉትን የነሲሓ ዱዓቶችን ዳዕዋ አዳምጡ የቀብር አፈር በጥብጦ መጠጣት ፣ በአንዬ ፣ ዳንዬ ፣ አልከስዬ ፣ ቃጥባርዬ ፣ አብሬትዬ ፣ አባድርዬ ፣ ሾንክዬ ፣ ሸከና ሑሰይንዬ ፣ ጀማ ንጉስዬ ፣ ከረምዬ ቀብር ላይ ጠዋፍ ማድረግ ከእስልምና የሚያወጣ ሽርክ ነው የሚል የለውም ።      ይህን ካሉ ከሱፍይና አሕባሽ እንዲሁም ኢኽዋን ጋር ስለሚጣሉ ። እየአንዳንዱን ወልይ ተብለው የሚመለኩ መሻኢኾችን ስም ጠርተው እዱኝ ፣ አክብሩኝ ፣ አሽሩኝ ፣ እጄን ያዙኝ ዋስ ጠበቃ ሁኑኝ ማለት ኩፍር ነው አይሉም ። የአንድነት  ስምምነቱን ስለሚያፈርስ ። በጥቅሉ ሽርክ ከባድ ወንጀል ነው ይላሉ ። ተውሒድ የነብያት ዳዕዋ ነው ይላሉ ። በዚህም ተከታዮቻቸውን ይሸውዳሉ ። የቱ ምን አይነቱ ተግባር ሽርክ እንደሆነ በዝርዝር አይናገሩም ።      በመሆኑም ሰለፍዮች ሆይ ኡማውን ከቀብር አምልኮና ከአክፍሮት ሀይላት ለማዳን ያለባችሁ ሀላፊነት ከምን ጊዜውም የከበደ ነው ። ከዚህ ጎን ለጎን ይህን የነብያት ተልእኮ ለዱንያዊ ጥቅም ብለው በመተው በኢስላም የሚነግዱትን ነሲሓዎችንና የእንጀራ አባታቸው ኢኽዋኖችን እንዲሁን እንባ ጠባቂዮቻቸው የሙነወር ልጅና ግብረአበሮቹ ማንነት ለሱናው ማህበረሰብ ግልፅ ማድረግ ሌላው ትልቅ ሀላፊነት መሆኑን መዘንጋት የለባችሁም ።        አላህ ዲኑን ይረዳል ተውሒድም የበላይ ይሆናል ። https://t.me/bahruteka #Share #Comment 👇👇👇👇👇 @Abu_Umer4 https://t.me/Abu_Umer1 https://t.me/Abu_Umer1
Hammasini ko'rsatish...
ባህሩ ተካ - Bahiru Teka

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته قناة رسمية لمحاضرات ودروس الأستاذ بحرو تكا (أبو عبيدة) الدعوة السلفية በአላህ ፈቃድ በዚህ ቻናል የአማርኛ ትምህርቶችን እንዲሁም አጫጭር የአረብኛና የአማርኛ ፁሁፎችን እንለቃለን ከዚህ ቻናል ውጪ ከሌላ ቦታ ተወስደው ለሚለቀቁ ኦዲዮዎች እውቅና አልሰጥም

https://telegram.me/bahruteka

👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
አያቹ ወላጆች ልጆችን ቲቪ ፊልም የማሳየት መጨረሻ!! ነገ ደግሞ እናቱን ሲገል አይተው እናታቸውን ካልገደልን ይላሉ። ወላጆች ሆይ አሏህን ፍሩ ለራሳቹ ዲንን ባትማሩ ራሱ ልጆቻቹን ዲን አስተምሩንጂ ፊልም ቲክቶክ ገለመሌ አታሳዩ ኢላሂ ምን አይነት ጊዜ ላይ ደረስን ዛሬ እንደቀልድ ልጆች ናቸው ይጫወቱ እያልን የምንተወዉ ነገር ነገ ዋጋ ሊያስከፍለን ይችላል የምናሳያተውን ነገር የምናሰማቸውን ሁሉ ከእድሜያቸው ጋር የሚመጥንና የሚረዱት መሆን ግድ ይለዋል እቺ እናት ነገ የራሷ ልጆች እርስበርስ ላለመተራረዳቸው ወይም ሌላ ሰው ላለመደረዳቸው ዋስትና የላትም አላህ የስቱር😢አንቺን እንኳን ልጅሽን አተረፈልሽ እናቶችንም አባቶችንም መምከር የምፈልገው ቃናን ከቤታችሁ አጥፉ ከሀይማኖታችንም ከባህላችንም ጋር የማይሄድ ትውልድ ገዳይ ቻናል ነው #Share #Comment 👇👇👇👇👇 @Abu_Umer4 https://t.me/Abu_Umer1 https://t.me/Abu_Umer1
Hammasini ko'rsatish...
👍 1
አሏህ ሆይ በሙስሊም እህቶቼ ላይ የሚጫወትን ወንድ ህይወታቸውን የሚያበላሽ ወንድ በዚና የሚያቆሽሻቸውን ወንድ ወዳንተ በተውበት ሚመለስ ከሆነ ምርጥ ባሪያህ አድርገው ያጠፋውንም ስህተት የሚያስተካክል አድርገው ካልሆነ ግን በዱኒያም በአኼራም አሳማሚን ቅጣት ቅጣው። 💔እህ የስንቱን ህይወት አጨለመ እህ💔 እህቶችም አብሽሩ እሺ ያጠፋቹትን ጥፋት ከከባባድ ወንጀል ቢመደብም አሏህ አዛኝ እና መሀሪ ስለሆነ በተውበት ራሳቹን አፅዱ ቀሪ ህይወታቹንም ምርጥ እንስት ለሌሎች ተምሳሌት የምትሆን ዲናን የተማረች በኒቃብ የተዋበች ሰለፊይ እንስት በመሆን አሳልፋ። #Share #Comment 👇👇👇👇👇 @Abu_Umer4 https://t.me/Abu_Umer1 https://t.me/Abu_Umer1
Hammasini ko'rsatish...
👍 3
የ”አል ናቅባ” ክስተት እና የጋዛው ጦርነት  ፍልስጤም በክርስትና፣ እስልምና እና አይሁድ እምነት ተከታዮች ዘንድ እንደ ቅዱስ ስፍራ የሚቆጠር፤ በኦቶማን ቱርኮች ቁጥጥር ሾር የነበረ አካባቢ ነው። የኦቶማን ቱርክ ግዛት መፈራረስን ተከትሎ ብሪታንያ አካባቢውን ማስተዳደር መጀምሯ ይታወሳል። በሁለተኛው የዓለም ጦርነት በአይሁዳውያን ላይ ከተፈጸመው የጅምላ እልቂት በኋላ መጠለያ አገር ፍለጋ ወደ መካከለኛው ምሥራቅ የሚገቡት አይሁዶች ቁጥር እየጨመረ ሲሄድም በብሪታንያ ላይ ጫናው ይበረታል። ይህም ፍልስጤም የሚደግፉ የአረብ ሀገራትና እስራኤልን ጦር ማማዘዙ ይታወሳል። እስራኤል የመጀመሪያውን የአረብ - እስራኤል ጦርነት አሸንፋ ግንቦት 14 1948 እንደ ሀገር መመስረቷን ማወጇም አይዘነጋም። በነጻነት አዋጁ ማግስትና ከዚያ ቀጥለው በተካሄዱ ጦርነቶች ከ700 ሺህ በላይ ፍልስጤማውያን ከቀያቸው እንዲወጡ ያደረገችበት ክስተት በፍልስጤማውያን ዘንድ “አል ናቅባ” ወይም “መቅሰፍት” እየተባለ ይጠራል። ከ1948ቱ ጦርነት በኋላ የተፈናቀሉ ፍልስጤማውያን ወደ ቀደመ ቤታቸው እንዲመለሱ ሳይፈቀድላቸው በሊባኖስ፣ ሶሪያ እና ዮርዳኖስ ስደተኛ እንዲሆኑ ተገደዋል። ይህ ታሪካዊ ክስተትም የፍልስጤማውያን የነጻነት ትግል መሰረት ሆኗል። ፍልስጤማውያን ከ76 አመት በፊት ያጋጠማቸው ታሪካዊ ክስተት አሁንም እንዳልቆመ ይናገራሉ። የጥቅምት 7ቱን የሃማስ ጥቃት ተከትሎ እስራኤል በጋዛ እየወሰደችው ያለውን ጥቃት ሽሽት ከ1 ነጥብ 7 ሚሊየን በላይ ፍልስጤማውያን ከቀያቸው ተፈናቅለዋል። ይህም ከ1948ቱ የ”አል ናቅባ” ክስተት በእጥፍ ጭማሪ ያለው ነው የሚሉት ፍልስጤማውያን፥ ጦርነቱ ቆሞ ወደቤታቸው ቢመለሱ እንኳን ለመኖሪያ እንዳይሆን መፈራረሱን ያነሳሉ። የመንግስታቱ ድርጅት በቅርቡ ባወጣው መረጃም ጋዛን መልሶ ለመገንባት ቢያንስ 16 አመታት ያስፈልጋል ማለቱ አይዘነጋም። እስራኤል ከ76 አመት በፊት ፍልስጤማውያንን ከቀያቸው አፈናቅላ እንደሀገር ከተመሰረተች በኋላ የመሬት ወረራዋ እንዳልቆመም ነው ተደጋግሞ የሚነሳው።  á‹¨1967ቱ የስድስት ቀናት ጦርነት የፍልስጤማውያንን ዌስትባንክ እና ምስራቅ እየሩሳሌም፣ የሶሪያን የጎላን ኮረብቶች እንዲሁም የግብጽ ሲናይ በርሃን (በ1984 እስክትመልሰው ድረስ) በቁጥጥሯ ሾር አስገብታለች።  እስራኤል ከአረቦች ጋር ያደረገቻቸውን አራት ታላላቅ ጦርነቶች የሚያወሱ ተንታኞች የጋዛው ጦርነት አላማ ሃማስን የመደምሰስ  አላማ አለው ቢባልም ዋነኛ ትኩረቱ የመሬት ወረራ ነው ይላሉ። Al Ain #Share #Comment 👇👇👇👇👇 @Abu_Umer4 https://t.me/Abu_Umer1 https://t.me/Abu_Umer1
Hammasini ko'rsatish...
Abu Umer Ibnu Sadik Manhaj Salaf Is My Way(መንሀጀ ሰለፍ መንገዴ ናት)

#ቁርአንእናሀዲስ #ቅድሚያ_ለተውሂድ_እና_ለሱና #የሰለፊይ_ኡስታዞች_ሙሀደራዎች ፡ ፡ ፡ ፡ #የተለያዩ_ዲናዊ_ፅሁፎች #የደጋግ_የቀደምቶች_ታሪክ

ለምን እንሰስታለን... ቀልድና ፌዝ እዚህ ግባ የማይባሉ ነገራቶች በተፖሰቱ ጊዜ ፅሁፉ እንኳን በቅጡ ሳናነበው ሰማያዊ ሪአክት ኬር እንገጫለን .... ጠቃሚ ነገር ለሕይወት መርህ የሆኑ ዲናዊ ነገር በተፖሰተ ጊዜ ወይ አንብበን ብቻ እናልፋለን አለያ ግን አንብበን ሰማያዊ እንኳን ሳንገጭ ላሽሽ እንላለን የማንከፍልበት ላይክ እንሰስታለን እንዴ ሚገርመው ነገር ፌመስ የሆነ አካል እዚህ ግባ የማይባል ነገር ሲፖስት ግን በላይክና በሼር እያበረታታን ግን ምርጥ መካሪ የሆኑ ወንድም እህቶች ግን ወርቃማ ፅሁፋቸው ሲያቀርቡልን ላይኩን ይከብደናል ሼር ማድረግ ቢያቅተን /ቢከብደን ኮመንት ላይ ገብተን ሜንሽን ፎሎወር በመጥራት እሱም ካቃተን ላይኩን አንሰስት እነዚህ ተግባሮች በምንጠቀም ጊዜ ጠቃማ ፅሁፉ / ፖስቱ ተደራሽነቱ የሰፋ ይሆናል አንተ አንቺ ብቻ አንብበሽ እፍን አናድርገው ለወንድም እህቶቻችንም እንዲደርስ እናድርግ Copy #Share #Comment 👇👇👇👇👇 @Abu_Umer4 https://t.me/Abu_Umer1 https://t.me/Abu_Umer1
Hammasini ko'rsatish...
Abu Umer Ibnu Sadik Manhaj Salaf Is My Way(መንሀጀ ሰለፍ መንገዴ ናት)

#ቁርአንእናሀዲስ #ቅድሚያ_ለተውሂድ_እና_ለሱና #የሰለፊይ_ኡስታዞች_ሙሀደራዎች ፡ ፡ ፡ ፡ #የተለያዩ_ዲናዊ_ፅሁፎች #የደጋግ_የቀደምቶች_ታሪክ

👍 2
#ሕይወትህ_ውስጥ_ያሉ_3_የሰው_ዓይነቶች ናቸው 1- ቅጠል ሰዎች 2- ቅርንጫፍ ሰዎች 3- ሥር ሰዎች #ቅጠል_ሰዎች እነዚህ ሰዎች ወቅት ጠብቀው ወደ ሕይወትህ የሚመጡ ሰዎች ናቸው። ደካማ ስለሆኑ ልትደገፍባቸው አትችልም። የሚመጡት የሚፈልጉትን ለመውሰድ ሲሆን ነፋስ በመጣ ወቅት ይሸሻሉ። እነዚህ ሰዎች የሚወዱህ ደኅና በሆንክበት ጊዜ ሲሆን ነፋስ ባገኘህ ወቅት ይተውሃል። #ቅርንጫፍ_ሰዎች ጠንካሮች ናቸው ግን ሕይወት ከባድ ስትሆን ይሰበራሉ፤ ብዙ ክብደትም መሸከም አይችሉም። የተወሰኑ ወቅቶች ላይ አብረውህ ይሆናሉ፣ የበለጠ ከባድ ሲሆን ግን ይሄዳሉ። #ሥር_ሰዎች እነዚህ ሰዎች ለመታየት ብለው ነገሮችን አያደርጉምና እጅግ ጠቃሚ ሰዎች ናቸው። በከባድ ጊዜ ስታልፍ እንኳ አጋዦች ናቸው። ውኃ ያጠጡሃል፤ ያለህበት ቦታ አያስጨንቃቸውም፣ እንዲሁ እንደሆንከው ይወዱሃል። ሁሉም ሰው አብሮህ አይቆይም። ወቅቱ ምንም ሆነ ምንም ሳይቀያየሩ የሚቆዩት የሥር ዓይነት ሰዎች ብቻ ናቸው። Copy #Share #Comment 👇👇👇👇👇 @Abu_Umer4 https://t.me/Abu_Umer1 https://t.me/Abu_Umer1
Hammasini ko'rsatish...
Abu Umer Ibnu Sadik Manhaj Salaf Is My Way(መንሀጀ ሰለፍ መንገዴ ናት)

#ቁርአንእናሀዲስ #ቅድሚያ_ለተውሂድ_እና_ለሱና #የሰለፊይ_ኡስታዞች_ሙሀደራዎች ፡ ፡ ፡ ፡ #የተለያዩ_ዲናዊ_ፅሁፎች #የደጋግ_የቀደምቶች_ታሪክ

👍 2
ሱሪ ከለበሰች በእርግጥ ረከሰች ኒቃብ ከለበሰች በእውነት ተከበረች @Abu_Umer1 @Abu_Umer1
Hammasini ko'rsatish...
👍 4
ልጆችሽ በመልካም ነገሯ የሚከተሏት እናት ነሽ ወይስ ከዚ በተቃራኒ ነሽ?...........ወላጆች የልጆቻቸው የመጀመሪያ ትምህርት ቤት ናቸው ይባላል specially እናት!...... ልጅሽ አንቺ ያደረግሽውን ሁሉ ማድረግ ትፈልጋለች ፣ አለባበስሽን፣አሰጋገድሽን፣አመጋገብሽን፣ሀታ ለባልሽን ያለሽን ሁኔታ ሁሉ ካንቺ ነው ኮፒ የምታደርገው። ባልሽን የምትገላምጪው ከሆነ እሷም ትገላምጠዋለች ፣ ኻዲሞቻችሁን በቤት ውስጥ የምታነውሪ የምትሳደቢ ከሆነ እሷም ሁለተኛ እናት ሆና ለምትንከባከባት በእጇ ለምታሳድጋት ኻዲም ጥሩ አመለካከት አይኖራትም።............የጥፍር አሰራርሽ ፣የፀጉርሽ ሁኔታ ፣የልብሶች አመራረጥ ላይ በደንብ ትኩረት ልታደርጊ ይገባል። ልጆችን ማስተካከል የሚቻለው ገና በለጋ እድሜያቸው ነው ስለዚህማ ለልጆቿ በመልካም ነገር ምሳሌ የምትሆን እናት ሁኚ! ........አንተም አባትዬው የውመል ቂያማ የአለማቱ ጌታ ፊት ስትቆሙ "ምግብ እያመጣ ይመግበኝ ነበር ፣ ዱንያዊ ፍላጎቴን ብቻ ያሟላልኝ ነበር እንጂ ዲኔን አላስተማረኝም " ብለው ሚስትክና ልጆችክ ክስ እንዳያቀርቡብክ የአላህን ሃቅ ተጠንቀቅ ያ አኺ!! By✍ Faiza #Share #Comment 👇👇👇👇👇 @Abu_Umer4 https://t.me/Abu_Umer1 https://t.me/Abu_Umer1
Hammasini ko'rsatish...
Abu Umer Ibnu Sadik Manhaj Salaf Is My Way(መንሀጀ ሰለፍ መንገዴ ናት)

#ቁርአንእናሀዲስ #ቅድሚያ_ለተውሂድ_እና_ለሱና #የሰለፊይ_ኡስታዞች_ሙሀደራዎች ፡ ፡ ፡ ፡ #የተለያዩ_ዲናዊ_ፅሁፎች #የደጋግ_የቀደምቶች_ታሪክ