uz
Feedback
« Abdurhman Oumer» عبد الرحمن بن عمر ዓብዱረሕማን ዑመር

« Abdurhman Oumer» عبد الرحمن بن عمر ዓብዱረሕማን ዑመር

Kanalga Telegram’da o‘tish

والسّلام على من اتبع الهدى «ሰላምም ቀጥተኛውን መንገድ በተከተለ ሰው ላይ ይኹን፡፡» [ ሱረቱ ጣሀ - 47 ] በአላህ ፈቃድ የኢስላም የሱና ትምህሮቶች ይተላለፍበታል።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali « Abdurhman Oumer» عبد الرحمن بن عمر ዓብዱረሕማን ዑመር analitikasi

« Abdurhman Oumer» عبد الرحمن بن عمر ዓብዱረሕማን ዑመር (@abdurhman_oumer) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 11 795 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 7 693-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 847-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 11 795 obunachiga ega bo‘ldi.

29 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -9 ga, so‘nggi 24 soatda esa 7 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 12.06% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 5.71% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 1 422 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 674 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 0 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
والسّلام على من اتبع الهدى «ሰላምም ቀጥተኛውን መንገድ በተከተለ ሰው ላይ ይኹን፡፡» [ ሱረቱ ጣሀ - 47 ] በአላህ ፈቃድ የኢስላም የሱና ትምህሮቶች ይተላለፍበታል።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 30 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

11 795
Obunachilar
+724 soatlar
+87 kunlar
-930 kunlar
Postlar arxiv
ልብ ሰላም ሲሆን ለሰሀቦች፤ ለሰለፎች (ለደጋግ ቀደምቶች) ለሱና ሰዎች በአጠቃላይ እና ለሁሉም ሙስሊሞች ጥሩ እይታ ያወርሳል። قال الحافظ ابن رجب الحنبلي - رحمه الله - فأفض
ልብ ሰላም ሲሆን ለሰሀቦች፤ ለሰለፎች (ለደጋግ ቀደምቶች) ለሱና ሰዎች በአጠቃላይ እና ለሁሉም ሙስሊሞች ጥሩ እይታ ያወርሳል። قال الحافظ ابن رجب الحنبلي - رحمه الله - فأفضل الأعمال سلامة الصدر من أنواع الشحناء كلها وأفضلها السلامة من شحناء أهل الأهواء والبدع التي تقتضي الطعن على سلف الأمة وبغضهم والحقد عليهم واعتقاد تكفيرهم أو تبديعهم وتضليلهم ثم يلي ذلك سلامة القلب من الشحناء لعموم المسلمين وإرادة الخير لهم ونصيحتهم وأن يحب لهم ما يحب لنفسه 📚لطائف المعارف ١٣٩ አል-ሐፋዝ ኢብኑ ረጀብ አል-ሐንበሊ (አላህ ይምረህ) እንዲህ ብለዋል፦ ከሁሉም በጎ ሥራዎች የላቀው ልብን ከጥላቻ ዓይነቶች ሁሉ ማጽዳት ነው። ከዚህም በላጩ የቢድዓና የስሜት ባለቤቶችን ጥላቻ (የሆነውን) ከልብ ማስወገድ ነው። ይህች (የቢድዓና የስሜት ባለቤቶች ጥላቻ) ደጋግ ቀደምቶች ሰለፎች ላይ መተቸት፣ መጥላትን፣ በእነሱ ላይ ማቄምን፣ እንዲሁም እነሱን ካፊር ወይም የፈጠራ ባለቤቶች የጥመት ሰዎች ናቸው ብሎ ማመንን የምታስከትል ናት። (የምታስከትል ከሆነቸው መራቅ ነው።) ከዚያም በደረጃ የሚከተለው የልብ ሰላም ለሁሉም ሙስሊሞች ከቂም ልብን ማጽዳት፣ ለእነሱ መልካም ነገር መመኘት፣ ምክር መስጠት፣ እንዲሁም ለራሱ የሚወደውን ለእነሱም መውደድ ነው። 📚ለጧኢፉል መዓሪፍ 139

+1
የኢኽዋኖች ቅርቃር ውስጥ መግባትና ኢስላምን መስእዋት ማድረግ አድስ አይደለም። ግን ሁል ጊዜ የሆነ ነገር በሰሩ ቁጥር በዛው እለት ብቻ ይጮኽባቸዋል እንጅ ሌላ ጊዜ ዞረው ለዲኑ የሚለፉ ሲመስሉና የሆነ ነገር ሲያሳዩ ልቡ ቅልጥ የሚል ብዙ ሰው አለ። መፍትሔ፦ «የሰለፍያን ተርቢያ መማርና በጥሞና ማጥበቅ ነው በዱንያም በአኸይራም ከችግር ከውዝግብ ነፃ የሚያደርገው።» የኢኽዋን አል ሙስሊሙን ከበርካታ ከባባድ ችግሮቻቸው ውስጥ ዋና ችግራቸው፦ በጥሩ የሚያዛቸውን ከመጥፎ የሚከለክላቸውን (ትችቱን በማየት) ሰለፍይን ይጠላሉ። ማታለሊያ ስልጣን የሰጣቸውን ያሞጋገሳቸውን ያቀፋቸውን ካፊርም ቢሆን አቅላቸውን እስከሚስቱ ልቀቅ ይላሉ። ስልጣኗን እውቅናዋን ለማግኘት ኩፍርም በመናገርና ሙስሊሙን በመገበርም ቢሆን ምንም ያደርጋሉ። ወጡ ሲባሉ የሚወድቁትም ለዛ ነው። ኢስላምን በመክዳታቸው ሌላን ወደው እውነተኞችን በመጥላታቸው ባላሰቡት መልኩ ውርደትን ይኮናነባሉ። ወላእና በራኣቸው በጣም የሞተና ቁጣን የሚያመጣ ነው። ሰውን በዋናው ማነቆው በመንሀጁ በዓቂዳው አይመዝኑም። አለቀ! እናስተውል፦ የፈለገ ጠንካራና ተቺ ቢሆን እውነተኛ ሰው ውድቀትህን አይቶ አይጥልህም። ሚሊየን ደገፈህ ብሎ ደግሞ አይፈራህም። ያኛው ከስርህ ብዙ ህዝብ እንዳስከተልክ ስላወቀ የሚያቀርብህ የሚላላስህ ግን አንተን ሳይሆን ከላይህ ላይ ያለውን ለሱ የሚጠቅመውን ነገር ለመቋደስ ነው። ስለዚህ በነፃ ማስረከብ ወይም መቀማት እንጅ “ሰጥቶ መቀበል” ከሚባለው ድርድር እንኳ የሚመደብ አይደለም በየትኛውም ሀገር ያለው የኢኽዋኖች ትርፍ! ስለዚህ ኢኽዋኖች ሆይ ንቁ። ከሁሉም በላይ ወደ መንሀጀ ሰለፍ ተመለሱ። ሙሉ በሙሉ አጥብቃችሁ በየቂን ያዙት። ከዛ እናንተ በምትጠብቁት ሳይሆን ባላሰባችሁት አላህ የበለጠ ሊሰጣችሁ ይከጀላልና።

قال العلامة ابن باز رحمه اللّٰه: من حفظ وقته بذكر اللّٰه و قراءة القرآن وصحبة الأخيار والبعد عن صحبة الغافلين يطيب قلبه و يلي
قال العلامة ابن باز رحمه اللّٰه: من حفظ وقته بذكر اللّٰه و قراءة القرآن وصحبة الأخيار والبعد عن صحبة الغافلين يطيب قلبه و يلين. [ 📚مجموع الفتاوى : ( 244  ) ]   ┉┅━••••••❀🌺❀•••••••━┅┉ አል ዓላመህ ኢብኑ ባዝ (ረሒመሁላህ) እንዲህ ብለዋል፦ {{አላህን በማውሳት ቁርኣንን በመቅራት መልካም ሰዎችን በመጎዳኘት ከዘንጊዎች በመራቅ ጊዜውን የጠበቀ ሰው ልቡ ጥሩ ይሆናል እንዲሁም ይለሰልሳል።}} 📚መጅሙዑል ፈታዋ ( 244 ) ]

❒ ‏قال العلامة عبدالرحمن السعدي رحمه الله : ‏أفضل انواع الشكر الإكثار من ذكر الله 📗 المواهب الربانية【(١٣١)】📘 አል ዓላመህ ዓብዱረህማን አስ-ሰዕዲይ (ረሒመሁላህ) እንዲህ ብለዋል፦ «ከምስጋና አይነቶች በላጩ አላህን ማውሳት (ዚክር) ማብዛት ነው።» 📚አል መዋሂብ አር-ባንየህ 131 ❒ ‏قال ابن القيم رحمه الله تعالى : فمن كان مشغولاً بالله وبذكره ومحبته فى حال حياته، وجد ذلك أحوج ما هو إليه عند خروج روحه إلى الله . 📗 ‏طريق الهجرتين 【(308)】 አል ኢማም (ረሒመሁላህ) እንዲህ ብለዋል፦ {{በሕይወት ዋኑ በአላህ እና እሱን በማውሳት በውደታው ተጠምዶ የኖረ ሠው፤ ሩሑ በምትወጣበት ጊዜ ያንን (መጠመዱን) ከምንም በላይ ለእሱ የሚያስፈልገው ሆኖ ያገኘዋል።}} 📚ጦሪቁል ሂጅረተይን 308 http://t.me/Abdurhman_oumer

ጥሩነት ለራስ ነው የግድ ውዳሴን አይጠብቅም! — የእራስን ሁኔታ በመልካም ለማቆየት መጣር ያስፈልጋል። እኔ መልካም ነኝ ወይስ አይደለሁም ብለን ራሳችንን ለመገንባት መጣር እንጅ በመልካም ለመቀጠልና
ጥሩነት ለራስ ነው የግድ ውዳሴን አይጠብቅም! — የእራስን ሁኔታ በመልካም ለማቆየት መጣር ያስፈልጋል። እኔ መልካም ነኝ ወይስ አይደለሁም ብለን ራሳችንን ለመገንባት መጣር እንጅ በመልካም ለመቀጠልና ለመጠንከር የግድ ምስጋና መጠበቅ አያስፈልግም። ምስጋናና አድናቆት ካላገኘን መበሳጨት ፅናት ማጣት ተስፋ መቁረጥ ውስጥ አለመግባት ግደታ ነው። ለወቀሳ ላለመጨነቅ የሚፈልግ ሰው በሚሰራው ስራ አድናቆት ምስጋና አለመጠብቅ አለበት። ጥሩነት ለራስ ነው ማር የሚጣፍጠው ለራሱ ነው፤ እሬትም የሚማረረው ለራሱ ነው።

ኢኽዋኖችም ሌሎችም መንሀጅ ያልተየላቸው ሰዎች በህሜትና በማነወር ያልተለየላቸው የግል ወንጀልና በአደባባይ በዳዕዋ የተሰነቀረ አለመለየት ነው። - የተፃረራቸውን አካል የግል ወንጀል አፈላልገው ካገኙ
ኢኽዋኖችም ሌሎችም መንሀጅ ያልተየላቸው ሰዎች በህሜትና በማነወር ያልተለየላቸው የግል ወንጀልና በአደባባይ በዳዕዋ የተሰነቀረ አለመለየት ነው። - የተፃረራቸውን አካል የግል ወንጀል አፈላልገው ካገኙ ደስታቸው ነው፤ ካልሆነ ዋሽተውም ቢሆን ቢለጥፉበት ወይም አጠጋግተው ቢያነውሩት ደስታቸው ነው። ይሄን ነው ግን በሸሪዓ የተከለከለው። - በእነርሱ ላይ ሲሆን አምነውበት፣ ጥሩ ነው ብለው በዳዕዋ ያስገቡትን አካሄዳቸውን ወይም ለሠው ያሰራጩትን ሲተቹ ግን ሀሜተኛ ወይም የሆነ ከአደብ ውጭ የሆነ ነገር እንደተተገበረ አድርገው ለማሳየት ይጥራሉ። ይሄ ደግሞ የተፈቀደው ነው። በመሆኑም ሰዎችን ባለባቸውም ሆነ በሌለለባቸው እንዲህ እኛ ባለብን ሌሎችን ወንጀል ከመርዘኛው ሀሜትና ሰውን ለማነወር ከመጣር እንጠንቀቅ ደዕዋን ለመጠበቅ በዳዕዋ ላይ የተደረገን አካሄድ በፍትሕ ለመግለፅ ስም መነሳትም ካለበት ስሙን ጠቅሶ በማስጠንቀቅ ሂደት ወደኋላ ማለት ከያስፈልግም ይሄም ይቅር እንባባል የሚባባሉበት አይደለም።

ሰውን በግንዛቤው መዝኑ በተለይ እነዚህን ሪከርዶች በጥሞና ስሟቸው ጥሩ ግንዛቤ ትይዛችሁ።

+1
👆👆👆 🔈#የሸይጧን መግቢያዎች ክፍል 9 እና ለዳዒዎች ምክር   አዘጋጅ:- ሸይኽ ዶ/ር ሑሰይን ቢን ሙሀመድ አስ-ስልጢ ክፍል የኪታቡን PDF ለማግኘት https://t.me/shakirsultan/1432 🔶በደቡብ ክልል በጉራጌ ዞን በቡታጅራ ከተማ ኹለፋ አል-ራሺዲን መስጂድ የተሰጠ ኮርስ። 🎙በኡስታዝ ሻኪር ቢን ሱልጣን (ሀፊዘውላህ) 🌐 https://t.me/shakirsultan

ዋና ሀብታም ድሀ በመሆን አይደለም ጥሩ አካሄድን መላበስ ነው። አካሄዱ ጥሩ ሰለፍይ የሆነን አካል ሀብታም ስለሆነ ብቻ ለማነወር የሚፈልግ ወሬም የለው እንደው ዝም ነው።
ዋና ሀብታም ድሀ በመሆን አይደለም ጥሩ አካሄድን መላበስ ነው። አካሄዱ ጥሩ ሰለፍይ የሆነን አካል ሀብታም ስለሆነ ብቻ ለማነወር የሚፈልግ ወሬም የለው እንደው ዝም ነው።

ስንቶች አሉ በጣም ታገለው ለዲን ደክመው ማነም ሳያውቃቸው ከአላህ ብቻ አስመዝግበው ከዱንያ (ከዚህች ምድራዊ ህይወት) የሚሰናበቱ!? t.me/Abdurhman_oumer/11124
ስንቶች አሉ በጣም ታገለው ለዲን ደክመው ማነም ሳያውቃቸው ከአላህ ብቻ አስመዝግበው ከዱንያ (ከዚህች ምድራዊ ህይወት) የሚሰናበቱ!? t.me/Abdurhman_oumer/11124

«መውሊድ በሸሪዓ ሚዛን» በጥሞና አድምጡት 🎙 በሸይኽ ዓብዱልሓሚድ ያሲን አሰለፍይ አስልጢይ አል`ለተሚይ ( ሐፊዞሁሏህ! )

➸ ‛‛በኢስላም ውስጥ ሰርጎ ገብ የሆነው መውሊድ ብዥታዎቹ እና መልሶቻቸው!’’ ✍ዝግጅት፦ ሸይኽ ዩሱፍ አህመድ ( ሐፊዘሁላህ )

ስለ መጅሊስ ሁኔታ ግንዛቤ! በብዙዎች ዘንድ በዓቂዳም በጭቆናም ይሄኛው መጅሊስ ይሻላል ተብሎ ነው የሚታሰበው በሌላ በኩል ደግሞ ሀቅ እንዳይነገር መጅሊሱ ይጨቁነናልና በማለት ጨቋኝነቱን አረጋግጠው ግን ጨቋኝነት ካለበትማ ሁሉም ህዝብ ሊያውቀው ይገባል ብሎ የተሻለ አለመምጣቱን ላልነቃው ህዝብ ከማሳወቅ ይልቅ ጭቆናውን አሁንም ጥፋቶችን የሚቃወሙ ሰዎችን ለማስፈራራት ብቻ ይጠቀሙበታል። ምን አይነት ስሌት ነው የአህባሽን መጅሊስ በውንብድናውና በጥመቱ ከተጸየፍነው ሌላኛውም እንደዛው ከሆነ “ብዙ ጥመቶችና ውድመቶች ካሉበት” የተከፈለው መስእዋትነት ተከፍሎ ከዚህ ብክለት ህዝቡን ለመጠበቅ ሁኔታውን ማሳወቅና መጋፈጥ ሲገባ ሌላ መለኪያ ድሮ የተጸየፍነውን ጭቆና ለዛሬው ሲሆን እንደ ማስፈራሪያ መጠቅም፤ የትላንቱ ጭቆና ሊገረሰስ የሚገባው አባገነንነት ከሆነ የዛሬው ጭቆና ማስፈራሪያ ተደርጎ ለተመሳሳይ ነገር ሁለት የተለያዩ መስፈሪያዎች መጠቀም ግልፅ ጥመት ማለት ይሄ ነው። የአሁኑ መጅሊስ እንደ ድሮው ቢሆንም ማስፈራሪያ ተደርጎ ይታፈንበታል እሱን ለህዝብ ማጋለጥ የለም የሚል አባባል ይመስላል። በጭቆናው ተመሳሳይ ከሆነማ በሌላ መልኩ ስናየው ይሄ ሊከፋ ነው አኻ! ለምን? እንዳውምኮ በአህባሹ መጅሊስ ከአህባሾች ውጭ ያሉት ሁሉም ለተውሒድ ለሱና ይታገሉ ነበር። ሁሉም በአንድ ጠላቱን አውቆ በአንድነት ሲታገል፣ የጥንክርና ወኒ ተላብሶ እጅ እየጨበጠ ሁሉም ወደ ጥንክርና (ወደ ጠንካራው አካሄድ) ይጣራ እንደነበር የሚታወቅ ነው፤ ጥንክርና ሰጥቶን ነበር ማለት ነው። ዛሬ ግን የተሻለ መጥቷል በሚል ተታሎ በመጅሊስ ስም አንዱ ከአንዱ በመደበላለቁ እየሟሟ ጥመትን የመቃወም ፍላጎቱ እየሞተ ነው። ከእነ ኢልያስ አህመድ ጀምሮ ከዛ በኋላ ያሉት ሁሉ እየዘቀጡ የመጡት በዚሁ ምክንያት ነው። ስለሆነም እያሟሟ ሰውን ወደ ጥመት እያስገባ መምጣቱ የሚታወቅ ከመሆኑም ጋር ጭራሽ ይጨቁናል እና መስጅዳችሁን እንዳትቀሙ እየተባለ መጨቆኑ ከራሱ ከመጅሊስ ደጋፊዎች እየተረጋገጠ ከሆነ፤ ክፋቱ ከዛኛው በልጦ እንዳረፈ እያረጋገጡ ነው። ጭቆና አለው ግን እሺ እንጋፈጠው ህዝቡ ይወቀው ህዝቡ የኔ በሚለው ተኩላ አይበላ ወይ ካልሆነ ጭቆናውን ጥመቶቹን ያስተካክል?? አይ አይደለም የሀቅ ሰዎችን ማስፈራራሪያ ይሁን በጭቆናውም እንዲቀጥል በአንድ በኩል እሱን እያደፋፈርን ሱንዮችን እያስፈራራን እናሳይ የሚባል አካሄድ አለ። በሌላ በኩል ጥሩ ነው እያልን እየደሰኮርን ወደሱ እንጣራ የሚል የለየለት ዲንን አሳልፎ የመሸጥ ቅጥረኝነት ነው። ልብ በሉ ቀስ በቀስ መጥፎነቱ የሚብስበት ለኢስላም ለሱናው መሟሟት መዳከም ሰበብ እየሆነ ጭቆናውም እየባሰ ስለሚሄድ እንጅ ውጤቱ እየተሻሻለ ቢመጣ ለኢስላም ለሱናው ጥሩ ቢሆን ኖሮኮ ሙስሊሞች በመጅሊስ ላይ ጥሩ አመለካከት ሊኖራቸው ተገቢ ይሆን ነበር። — t.me/Abdurhman_oumer/12513

ሁሉም ራሱን ማስተካከል ትቶ ወደ ሌላ ሲጠቁም ጊዜ፤ ሐቅ መታወቅ እንደማይቻል ሲመስል አያሳዝናችሁም ወይ? ሆኖም ምንምኳ በማስመሰል በቃላት እሽቅድድምና በቲፎዞ ቢሸፈንም እውነታው ከግብስብስ ተለይቶ
ሁሉም ራሱን ማስተካከል ትቶ ወደ ሌላ ሲጠቁም ጊዜ፤ ሐቅ መታወቅ እንደማይቻል ሲመስል አያሳዝናችሁም ወይ? ሆኖም ምንምኳ በማስመሰል በቃላት እሽቅድድምና በቲፎዞ ቢሸፈንም እውነታው ከግብስብስ ተለይቶ መታወቁ አይቀርም። ምናልባት ከትላት ዛሬ ከዛሬ ነገ ውስብስብነቱ ቢበረታም ዱዓ ከማድረግ ጋር የትኛውም የተሸፈነ እውነት ለተሸፈነባቸው ሰዎች ሳይገለጥ አይቀርም። ከተገለጠላቸው በኋላ ያልተቀበሉት እራሳቸውን ነው የሚጎዱት አላህ ማነንም እውነታውን ሳያሳውቅ አይቀጣም። በመሆኑም ዱዓእ ያስፈልጋልና በነጋ በመሸ ዘዴ በመፈለግ እንደት ራሳችንን አጉልተን ሌሎችን በተንኮል አንኳሰን እናሳይ በሚል አላማ የሚረብሹትን አላህ የሚገባቸውን ይስጣቸው እንደት እውነታ ቦታው ላይ ይቀመጥ ብለው የሚታገሉትን አላህ ይርዳቸው። ሀቅ እንዲለይለት ለፈለገ በትንሹ ጥቆማ - እገሌ ለእኔ ምን አድርጎልኛል ወይስ ምን አድርጎብኛል የሚለውን የግል ጉዳይ ሚዛን ውስጥ ባለማስገባት ወይስ በሆነ ነገር ቅርቤ ነው ወይስ ሩቅ ሳትሉ እገሌ እኔን የሚተቸኝ በጥፋት ላይ ስለምጠነክር ያ ሰላም ነስቶት ነው ወይ በማለት የሚደግፈኝስ ለግሉ ወይስ በጥፋት ላይ ስለማልስማማ ለሐቅ ብሎ ነው የሚደግፈኝ? የሚለውን በማስተዋል ይሁን። በሐቅና በባጢል ዘመቻ ሲደረግ ማነው ከልብ በሚገባ የእውነት ተሰምቶት መሆኑን ልብ በሚያሽር የሚታገለው? ወይስ በወቅቱ እነሱን የሚያስደስተው የሚለውን በማየት ይሁን። ወይስ ንግግሩ የጥፋት ሰዎች እንዲተቹን እንዲመቻቸው አድርጎ የሚናገረው ማን ነው? ወይም መልእክታቸው በስውር እንዲተላለፍ የሚያደርገው ማነው? የሚሉ መለያዎችን መታጠቅ ያስፈልጋል። ካወቃችኋቸው በኋላ በአንድ ጊዜ አትራቋቸው ታገሷቸው አስታሟቸው ጠቁማቸው ከዛ በኋላ በእርግጠኝነት የወቃሽ ወቀሳ ሳትፈሩ ወስኑ።

በድሆች የሚገኘው ደረጃ 📌 ‏قال ابن معاذ - رحمه الله: «حبُّك الفقراء مِن أخلاق المرسلين وإيثارك مجالستهم مِن علامات الصَّالحين وفـرارك منهم مِن علامات المنافقين». 📘 فيض القدير للمناوي【(١٠٩/١)】 ኢብኑ ሙዓዝ (ረሒመሁላህ) እንዲህ ብሏል፦ [ ድሆችን መውደድህ ከመልእክተኞች ስነ-ምግባር ውስጥ ነው፤ እነሱንም ጋር መቀማመጥ መምረጥህ ከጥሩ ሰዎች ምልክቶች ውስጥ ነው፤ ከእነሱ መሸሽህ ከሙናፊቆች ምልክቶች ውስጥ ነው። ]

አቡ ደርዳእ ረዲላሁ ዓንሁ እንዲህ ይላሉ፦ «ከምፈራው ሁሉ ሒሳብ ላይ በቆምኩ ጊዜ በጣም የምፈራው በእርግጥም አውቀሃል ባወከው ነገር ምን ሰራህ?» መባልን ነው። 📚አኽላቁል ዑለማእ ሊል አጁሪይ

እርግጥ ነው ውድድር ባይኖር (ጆይን ፎሎውና ላይክ ፍለጋ እንዲሁም ሊፍት ፍራቻ ባይኖር) ከእኛ ውስጥ የማይጠናከር የማይለፋ ሊኖር ይችል ነበር። ማጠናከሩ ጥሩ ሆኖ ሳለ ስራ ተቀባይነት እንዲያገኝ ግን
እርግጥ ነው ውድድር ባይኖር (ጆይን ፎሎውና ላይክ ፍለጋ እንዲሁም ሊፍት ፍራቻ ባይኖር) ከእኛ ውስጥ የማይጠናከር የማይለፋ ሊኖር ይችል ነበር። ማጠናከሩ ጥሩ ሆኖ ሳለ ስራ ተቀባይነት እንዲያገኝ ግን በምድር ላይ ቀሪ የሆነችዋን እውቅናና ለማስደመም ፈልጎ ሰው እንዳይሸሸው ተፈርቶ ሳይሆን የአላህን እዝነት ጀነትን ፈልጎና ቁጣውን እሳትን ፈርቶ በየቂን መስራት ነው። قال سفيان الثوري رحمة الله:« لو أن اليقين استقر في القلب، كما ينبغي لطار فرحا وحزنا وشوقا إلى الجنة أو خوفًا من النار». 📜↲ (حلية الأولياء» لأبي نعيم (۱۷/۷) اليقين روح الأعمال وعمودها ولبها، ومنزلته من الإيمان منزلة الروح من الجسد، رزقنا الله اليقين، وجعلنا من أهله بمنه وكرمه

በውስጥ መስመር እንደት ነው የሚሰራው? እያላችሁ የምትጠይቁ የማያዳግም አጭርና ግልፅ በቂ የሆነ የመጨረሻ መግለጫ 👉 ተንታኝ፣ አማካሪ እና ጸሐፊ! — • በድምጽም ሆነ በጹሑፍ የቀረቡ የሌሎችን ሀሳቦች በመተንተን፣ ጥንካሬዎችን እና ድክመቶችን በመጠቆም፣ እንዲሻሻሉ ማገዝ። • መጻፍ ለማይችሉት ወይም ለማይመቻቸው ድርሰት (ጹሑፍ) ማቅረብ። • ሌሎችም ጉዳዮችን ማማከርና ለማቅለል ማገዝ። የምታሰሩት ሲኖር ብቻ አናግሩ