ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ Balderas for Democracy
Kanalga Telegram’da o‘tish
2 875
Obunachilar
-424 soatlar
-87 kunlar
-5930 kunlar
Postlar arxiv
#መረጃ
የግፍ እስረኛው አቶ ስንታየሁ ቸኮል ላይ ፖሊስ በድጋሚ ይግባኝ ጠየቀባቸው!
/
በትላንትናው እለት አራዳ ምድብ የግዜ ወንጀል ችሎት በሀሰት ክስ የታሰሩትን አቶ ስንታየሁን ዋስ ቢላቸውም ፓሊስ ግን ይግባኝ እንደጠየቀባቸው ይታውሳል።
በዛሬው እለት ማለትም ነሀሴ 24/2014 ዓ.ም የይግባኝ ሰሚ ችሎት የስር ፍርድ ቤቱን ውሳኔ አፅንቶታል። ሆኖም ግን ለዋስትና የተጠየቀው ብር ከተከፈለ በኋላ ፖሊስ በድጋሚ ይግባኝ ለማለት ጉዳዩን ወደ ሰበር ሰሚ ችሎት ወስዶታል። በዚህም ምክንያት አቶ ስንታየሁን ፖሊስ ሳይፈታቸው ቀርቷል።
የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲው የድርጅት ጉዳይ ሀላፊ እና የስራ አስፈፃሚ አባል የሆኑት አቶ ስንታየሁ ከዚህ ቀደም በባህርዳር እና በፌደራል ፓሊስ ወንጀል ምርመራ ታስረው የነበሩና ሁለት ግዜ (የ30ሺህ እና የ100 ሺህ ብር) ዋስ ተፈቅዶላቸው የከፈሉ ቢሆንም ሳይፈቱ መቅረታቸው ይታወሳል። የአሁኑ ዋስትና ለሶስተኛ ግዜ የተፈቀደ ነው።
ፍትህ ለአቶ ስንታየሁ ቸኮል
#ኢትዮጵያ
አቶ ስንታየሁ ቸኮል ነገ ፍርድ ቤት ይቀርባል። መቶ ሸህ ብር ዋስ አምጣና ትፈታለህ ተብሎ ብሩ ከተከፈለ በኋላ እንደገና በሌላ ወንጀል እንፈልግሀለን ብለው መከራ እያሳዩት ነው። ፍትህ ለስንታየሁ ሁላችንም ድምጽ ልንሆነው ይገባል።
ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን
አዲስ አበባ
ጉዳዩ፡- የግፍ እስረኛ ስለሆነው ወጣት ቢኒያም ታደሰ አቤቱታ ስለማቅረብ
ወጣት ቢኒያም ታደሰ በአዲስ አበባ ከተማ ፓሊስ ክትትል ተይዞ 5 ቀን በአዲስ አበባ ወንጀል ምርመራ ታስሮ ቢቆይም ፍ/ቤት አልቀረበም፡፡ በቀጣይም ባልታወቀ ምክንያት ያለማንም ፍ/ቤት ትዕዛዝ አዋሽ አርባ ወስደው 40 ቀን ፍ/ቤት ሳይቀርብ ከታሰረ በኋላ በ41ኛው ቀን አዋሽ ሰባት ፍ/ቤት ቀርቦ በ14 ቀን ቀጠሮ ተጠይቆበታል፡፡
ይሁን እንጂ የቀጠሮ ቀኑ ሳይደርስ ባልታወቀ አካል ትእዛዝ ከአዋሽ ሰባት ወደ አባ ሳሙኤል እንዲመጣ ተደርጓል፡፡ እስከ ዛሬም መርማሪ ፖሊስ ሊያናግረው አልቻለም፡፡ አባሳሙኤል እስር ቤት ከመጣ አስር ቀን የሞላው ቢሆንም፣ ፍ/ቤት አልቀረበም በአጠቃላይ ሃምሳ ስድስት ቀን በግፍ ታስሮ ይገኛል፡፡
በርሃማ በሆነው በአዋሽ ሰባት እስር ቤት ታስሮ በቆየበት ጊዜ የደረሰበትን ኢ- ሰብዓዊ ድርጊቶችን ስንመለከት፡-
1ኛ. ሻወር በ40 ቀን ውስጥ 2 ጊዜ ብቻ እንዲወስድ መደረጉ፣
2ኛ. ያለቅያሬ ልብስ 40 ቀን እንዲቆይ መደረጉ፣
3ኛ. 40 ቀን ሙሉ ከእስር ቤት እንዳይወጣና ፀሐይ ብርሃን እንዳያገኝ ተደርጓል፡፡
4ኛ. ከጠበቃ ጋር፣ ከቤተሰብ ጋር፣ ከኃይማኖት አባት ጋር እንዳይገናኝ ተደርጓል፡፡
5ኛ. ለ15 ቀን ቁርስ፣ ምሳ፣ እራት አንድ አንድ ዳቦ ከውሃ ጋር ብቻ በማቅረብ የርሃብ ቅጣት ደርሶበታል፡፡
6ኛ. ከ15 ቀን በኋላ ደግሞ ለቁርስ አንድ ዳቦ ከሻይ ጋር፣ ምሳ እና እራት ሁለት ዳቦ ከወጥ ጋር እያቀረቡ ለ40 ቀን በረሃብ ቀጥተውታል፡፡
7ኛ. የስነልቦና እና የሞራል ውድቀት ደርሶበታል፡፡
በአጠቃላይ ህገ መንግስታዊ መብትና በሰብዓዊ መብቱ ተገፏል፡፡ ስለዚህ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የዜጎችን ሰብዓዊ መብት እና ደህንነት የመጠበቅ ግዴታ ስላለበት፣ አሁን ታሰሮ በሚገኝበት አባ ሳሙኤል እስር ቤት በመገኘት እንዲጎበኝና አስቸኳይ መፍትሔ እንዲሰጠው ፓርቲያችን ይጠይቃል፡፡
ከዚህ በፊት ሐምሌ 25/11/2014 ዓ.ም ለዚህ ተቋም ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ አቤቱታ ያስገባ ቢሆንም ምንም መልስ ያላገኘ መሆኑን እየገልፅን፣ ለሁለተኛ ጊዜ አቤቱታ ማቅረባችን ተረድታችሁ መልስ እንድትሰጡን በድጋሜ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
#ኢትዮጵያ
