cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

ማቲ ሸገር - Mati Sheger®

ስለ ፍትህ ስለ እኩልነት እና ስለ ዲሞክራሲ

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
1 836
Obunachilar
-324 soatlar
+97 kunlar
+730 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

በ4 ቢሊዮን ብር የሚገነባው የቅዱስ ያሬድ ሙዚየም⁉ ቅዱስ ያሬድ ድጓ፣ ጾመ ድጓ፣ ምዕራፍ፣ ዝማሬና መዋሥዕት የተሰኙትን 5 የዜማ መጻሕፍት የደረሱ ታላቅ ኢትዮጵያዊ ሊቅ ናቸው፡፡ ብቸኛው የግእዝ ሥነ ጽሑፍ መስራች እንደሆኑም ይነገራል፡፡ ለእኚህ ኢትዮጵያዊ ሊቅ የሕይወት ታሪካቸውን የሚዘክር ሙዚየም በታላቁ ራስ ዳሽን ተራራ ላይ በ4 ቢሊዮን ብር ወጪ ሊገነባ ነው፡፡ የፕሮጅክቱ ሰብሳቢ ጋዜጠኛ ጥበቡ በለጠ ቅዱስ ያሬድ የመጀመርያው የዜማ ሊቅ ብቻ ሳይሆን በድርሰትም የመጀመርያው መሆናቸውን ገልጾ በስማቸው የሚገነባው ሙዚየም የቅኔ ትምህርት፣ የዝማሬ ትምህርትና በርካታ ዘርፎችን የሚያካትት እንዲሁም ብዙ ሊቃውንትን የሚያፈራ መሆኑን ተናግሯል፡፡ ጋዜጠኛው አክሎም የአካባቢው ገበሬ ፕሮጀክቱን ስለወደደው 6 ሄክታር መሬት መስጠቱን ገልጿል፡፡ በዚህ ሙዚየምም የአሁኑ ትውልድ የራሱን አሻራ የሚያሳርፍበት ታሪካዊ፣ ሀይማኖታዊ እና ሀገራዊ ፋይዳ እዳለውም ጨምሯል፡፡ እነቅዱስ ላሊበላ በ12ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የሰሩት አስከዛሬ ላለው ትውልድ እንደጠቀመ ሁሉ እኛም ይሄንን በመስራት ለቀጣይ ትውልድ ትልቅ መሰረት የምንጥልበት ነውም ብሏል፡፡ በታላቁ ራስ ዳሽን ተራራ በደብረ ሐዊ ገዳም አቅራቢያ በሚገነባው ሙዚየም ውስጥ አንዱ የሆነው ህንፃ ቤተክርስቲያን የኖህ መርከብን ቅርጽ የሚይዝ መሆኑንም የፕሮጀክቱ ዋና አርክቴክት መኮንን ወርቁ ተናግረዋል፡። የፕሮጀክቱ አጠቃላይ ይዘትም አካባቢውን የዋጀ እና በዋሻ መልክ የሚገነባ ሲሆን በዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ታግዞ የሚከወንም መሆኑንም አርክቴክቱ አንስተዋል፡፡ ሙዚየሙ በስማቸው የሚገነባላቸው ሊቁ ባለቅኔ የዜማ አባት ቅዱስ ያሬድ መጻሕፍትን በጣዕመ ዜማ ደርሰዋል፡፡ መዝሙረ ዳዊትን ጨምሮ ሌሎችንም ቅዱሳት መጻሕፍትን በዜማው ያመሠጠሩ ታላቅ ኢትዮጵያዊ ሊቅ ናቸው፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሰፊ የአገልግሎት ድርሻ ያላቸው ግእዝ፣ ዕዝልና አራራይ የዜማ ዓይነቶች የቅዱስ ያሬድ የዜማ ድርሰቶች ናቸው፡፡ #ማቲ_ሸገር የቴሌግራም ቻናል:- T.me/matiosbirhanu
Hammasini ko'rsatish...
👍 1
👇👇👇👇👇
Hammasini ko'rsatish...
ዛሬ 7 ነው የቅድስት ስላሴ አመታዊ እለት‼ ቅድስት ስላሴ በበረከቱ ይጎብኛችሁ🙏 አሜን🙏
Hammasini ko'rsatish...
7👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
ቅዱስ ሲኖዶሰ ከሐምሌ 22 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2016 ዓ.ም ለመነኮሳት ምህላ አወጀ⁉ " ውሎ ማደር፣ ወጥቶ መግባት በአንዳንድ የሀገራችን አካባቢዎች ስጋት ከሆነ ሰነባብቷልና በእውነት የሚለምኑትን ሁሉ የሚሰማ እግዚአብሔር መተላለፋችንን ይቅር እንዲለን፣ ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም፣ ለቤተ ክርስቲያናችን ፍቅር አንድነት፣ ለሕዝባችን ደኅንነት እንዲሰጥልን ከአንድነት ገዳማት ኅብረት በቀረበው ጥያቄ መነሻነት ምሕላ ማወጅ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ በሁሉም የሀገራችን ክፍልና በሌሎችም አህጉራተ ዓለም የምትገኙ መነኰሳትና መነኰሳይያት ከሐምሌ 22 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2016 ዓ.ም. ድረስ ለሰባት ተከታታይ ቀናት በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሃይማኖታዊና ቀኖናዊ ትውፊት መሠረት የገዳማት ኅብረቱን ጥሪ ተቀብላችሁ የምሕላ ጸሎት እንድታደርሱ፣ በጤና ችግር ምክንያት ካልሆነ በስተቀር እስከ ዕርበተ ፀሐይ በመጾም ሱባኤ እንድትይዙ፣ ቋሚ ሲኖዶስ በኅብረተ መንፈስ ቅዱስ ከአደራ ጋር ያሳስባል፡፡" #ማቲ_ሸገር የቴሌግራም ቻናል:- T.me/matiosbirhanu
Hammasini ko'rsatish...
👍 5 1
02:06
Video unavailableShow in Telegram
በቅርቡ በቅዱስ አባታችን በረከታቸው ይደርብንና በአቡነ ጴጥሮስ የህይወት ታሪክ ላይ ያጠነጠነ ፊልም ተሰርቶ ለእይታ ሊበቃ መሆኑን ሰምተናል‼ እስኪ ሃሳባችሁን አካፍሉኝ #ማቲ_ሸገር T.me/matiosbirhanu
Hammasini ko'rsatish...
6.94 MB
👍 4
Photo unavailableShow in Telegram
ጀፒ እውነት ውሸት ነበር የመሰለኝ ማመን ይከብዳል ነብስህ በሰላም ትረፍ ወንድሜ😭 RIP😭
Hammasini ko'rsatish...
😢 4
አሁን በኤፍ ኤም አዲስ 96.3 በቀጥታ ስርጭት እከሰታለሁ‼
Hammasini ko'rsatish...
👍 3👎 1
እጅግ ድንቅና ስኬታማ ነበረ🙏 በዛሬው የማህበራችንን 8ተኛ መደበኛ ጉባኤ ማጠቃለያ ኮንፈረንስ በደመቀ እና ባማረ ሁኔታ አካሂደናል‼ ማህበራችን በብዙ ውጣውረዶች ውስጥ በስኬት ጎዳና በመጓዝ ለከተማችን ወጣት ድምጽ በመሆን ያገለገለ ድንቅ ተቋም ነው በዛሬው እለትም በዚህ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ሚና ለነበራቸው የቀድሞ አመራሮች እውቅና ሰተናል። ይህንን ፕሮግራም ያማረና የደመቀ እንዲሆን አስተዋጽኦ ያበረከታችሁ አካላት ሁሉ ምስጋናችን ትልቅ ነው🙏 ማቲ ሸገር የቴሌግራም ቻናል:- T.me/matiosbirhanu
Hammasini ko'rsatish...
👍 4🏆 2 1
ጾመ ሐዋርያት ሰኔ 17 ይጀምራል ።ሁሉም ክርስቲያን ሊጾመው የሚገባ ከ7ቱ የአዋጅ አጽዋማት አንዱ ነው‼
Hammasini ko'rsatish...
👍 2
ለቅዱሳን ሐዋርያት የተገለጡላቸው ልሣናት (ቋንቋዎች) የታወቁ፣ ሰዎች የሚግባቡባቸው ቋንቋዎች ናቸው፡፡ ይሁንና የመንፈስ ቅዱስን ስጦታ ማቃለል የሚወድ ሰይጣን በየዘመናቱ በመ*ናፍቃንና በሀሰተኛ ሰባኪያን እያደረ አጋንንታዊ ጩኸትን ከመንፈስ ቅዱስ ስጦታ ጋር በማምታታት ብዙ አላዋቂዎችን፣ ማገናዘብ የማይችሉ ሰነፎችን አታሏል፤ ወደፊትም ያታልላል፡፡ መንፈስ ቅዱስ ግን ለሰው የሚጠቅም፣ ለአገልግሎት የሚውል ቋንቋን እንጅ አረፋ የሚያስደፍቅ አጋንንታዊ ጩኸትን አይገልጽም፡፡ መ*ናፍቃኑ በየአዳራሹ የሚዘባርቁት ትርጉም አልባ ጩኸት በብልሃት የተፈጠረ ተረት እንጅ የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ አለመሆኑን ለመረዳት መጽሐፍ ቅዱስ በልዩ ልዩ ልሣናት (ቋንቋዎች) መናገርን በተመለከተ ከሚያስተምረን እውነትና ከቤተክርስቲያን ትውፊት አንጻር በሚከተለው መልኩ መገምገም ይገባል፡፡ ለሐዋርያት ቋንቋዎች ለምን ተገለጡላቸው? ቅዱሳን ሐዋርያት ቋንቋዎች የተገለፁላቸው ስለሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስና የቤተክርስቲያን ትውፊት ያስረዳናል፡፡ በዋነኛነት የልሣናት (ቋንቋዎች) መገለጥ ዓላማ ደቀመዛሙርቱ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ወንጌልን ለማስተማር ሲዘዋወሩ ሁሉንም በየቋንቋው ማስተማር እንዲችሉ ነው፡፡ ለዚያም ነው ሐዋርያት በየሀገሩ ቋንቋ በመንፈ ስቅዱስ ስጦታ በተናገሩ ጊዜ ከየሀገሩ የተሰበሰቡ አይሁድ “እንግዲህ በየሀገራችን ቋንቋ ሲናገሩ እንዴት እንሰማቸዋለን?” (ሐዋ. 2፡8) ያሉት፡፡ በተቃራኒው መ*ናፍቃኑ ተገለጠልን እያሉ የሚዘባርቁት ጩኸት ግን ተዘዋውሮ ለማስተማር የሚሆን አይደለም፡፡ አማርኛ ብቻ የሚናገር ሰው ሌላ ልሣን (ቋንቋ) ተገልጾለት በኦሮምኛ፣ በትግርኛ፣ በሲዳምኛ፣ በጉራጊኛና በመሳሰሉት ቢያስተምር ነው የሐዋርያት ዓይነት ልሳን ተገለፀ ማለት የሚቻለው፡፡ ይህም ቋንቋ በመለማመድና ትንሽ ቃላትን በመናገር ሳይሆን የመጻሕፍትን ምስጢር ሳያዛቡ በሙሉ መረዳት በሌሎች ቋንቋዎች ማስተማርን ይጠይቃል፡፡ ስለሆነም የመ*ናፍቃኑ ማምታቻ የሰይጣን አሠራር መሆኑ በዚህ ይታወቃል፡፡ በሁለተኛ ደረጃ ለሐዋርያት ቋንቋ የተገለጸው መገለፁ ተዓምር ነውና ሰዎች ተዓምሩን አይተው ወደ ጽድቅ መንገድ እንዲመጡ ለመርዳት ነበር፡፡ “ሁሉም ተገረሙ፤ የሚሉትንም አጡ” (ሐዋ. 2፡12) እንዲል፡፡ “አሁንም ቋንቋ መናገር ለማያምኑ ሰዎች ለምልክት ነው” (1ኛ ቆሮ. 14፡22) እንደተባለ ምልክት (ተዐምር) የሆነው፣ የሚሆነው የሚሰማ የሚታወቅ ቋንቋ መናገር እንጂ መ*ናፍቃኑ በየአዳራሹ እንደሚያደርጉት ያለ ትርጉም አልባ የጩኸት ጋጋታ አይደለም፡፡ ረጋ ብለው መናገር የማይችሉትን፣ ትርጉሙን የማያውቁትን፣ ሰዎችም የማይረዱትን የአ*ጋንንት ጩኸት መጮህ በምንም መልኩ ተዐምር ሊባል አይችልም፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ልሳናት ሲገለጡላቸው በእሳት አምሳል የተከፋፈሉ ልሣናት ለሁሉም ተገልጠውላቸዋል፡፡ እንግዲህ አእምሮ እንደሌላቸው ሆነው የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ በአ*ጋንንታዊ ጩኸት የሚያቃልሉ መ*ናፍቃን የእሳት ልሳናትንም በማስመሰል እንዲሰጣቸው አለቃቸውን (ዲያብሎስን) ይጠይቁት ይሆን!? በአጠቃላይ በዓለ ጰራቅሊጦስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ በተነሳ በኀምሳኛው ቀን፣ በክብር በምስጋና ወደሰማይ ባረገ በአሥረኛው ቀን በፍቅር ጉባኤ፣ በአንድነት መንፈስ ለተሰበሰቡ ለ120ው ቤተሰብ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ መገለጡን፣ ዓለምን ዞረው የሚያስተምሩበት የልሣን (ቋንቋ) ስጦታ መቀበላቸውን የምናዘክርበት ከኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ዘጠኝ ዐበይት በዓላት አንዱ ነው፡፡ለሐዋርያት በእሳትና በነፋስ አምሳል የተገለጠ መንፈስ ቅዱስን የምንዘክረው እንዳለፈ ታሪክ ብቻ ሳይሆን ዛሬን ጨምሮ ለዘለዓለም የቤተክርስቲያን መሪ፣ ምስጢራትን አክባሪ፣ የቅዱሳት መጻሕፍት ምስጢርና ትርጓሜ ገላጭ፣ በአጠቃላይ የቤተክርስቲያን ጠባቂ መሆኑን በመረዳት ነው፡፡ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ዛሬም ዕለት ዕለት በቤተክርስቲያን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም ሊያከብር፣ ሊለውጥ፤ በጥምቀት ወደ ቤተክርስቲያን ማኅበር የሚቀላቀሉትን ህጻናትና ምዕመናን ሊያነፃና ሊያከብር፤ ለእውነተኛ መምህራን የቅዱሳት መጻሕፍትን ምስጢርን ሊገልጽ፣ የመሳሰለውንም አገልግሎት ሊያከብር ይወርዳል፤ በእምነትም እናየዋለን፡፡ ከመንፈስ ቅዱስ ጸጋ የተነሳ ቅዱሳን ሐዋርያት የተለያዩ ሀገራት ቋንቋዎች ስለተገለጡላቸው የወንጌልን ብርሃን በዓለም ለማስፋፋት ቻሉ፡፡ የተገለጡላቸው ቋንቋዎችም ሰው የሚሰማቸው፣ ለመግባባት፣ ለትምህርትና ለጸሎት የሚሆኑ የታወቁ ቋንቋዎች ናቸው፡፡ የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ የሚያቃልሉ መ*ናፍቃን ግን ይህን ለሐዋርያት የተገለጸ እውነተኛ ቋንቋ ትርጉም ከሌለው አ*ጋንንታዊ ጩኸት ጋር በማምታታት ብዙዎችን ያታልላሉ፡፡ አዕምሮ እንደሌላቸው ሆነውም በማይገባቸው ጩኸት የማይረዱትን ይናገራሉ፡፡ እንግዲህ ምን እንላለን? የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ ያለ ዓላማ የሚገለጥ አይደለም፡፡ ለሐዋርያት ጸጋን የሰጠ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ማስተዋሉን ያድለን፡፡ የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የድንግል ማርያም አማላጅነት፣ የቅዱሳን መላእክት ተራዳኢነት፣ የጻድቃን፣ የሰማዕታት፣ የቅዱሳን ሐዋርያት፣ የቅዱሳን አበው መነኮሳት፣ የቅዱሳት አንስት፣ የደናግላንና የቅዱሳን ሁሉ ምልጃና ቃል ኪዳናቸው ባለንበት ከሁላችን ጋር ይሁን ይቆየን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ ይሴባሕ ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን ወአሜን ለይኩን ለይኩን፡፡
Hammasini ko'rsatish...
👍 2 2
Boshqa reja tanlang

Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.