cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

HD Hawssa Daily ( VOH)

ወቅታዊና አዝናኝ መረጃዎች!በሐዋሣና አከባቢዉ!

Ko'proq ko'rsatish
Mamlakat belgilanmaganTil belgilanmaganToif belgilanmagan
Reklama postlari
193
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

Repost from VAMOS FIXED BETTING
የመኖሪያ ቤት ሽልማት ለባለ እድለኞች ከጊፍት ሪልስቴት፡፡ ሰላም ፍቅር ጤና እንዲሆንላቹ እየተመኘን በኢትዮጵያ የመኖርያ ቤት ግንባታ ዘርፍ ቀዳሚ ሆነን ለብዙ አመታት ለኢትዮጵያኖች በሚመጥን ሁኔታ ጥራቱን የጠበቀ real estate በመገንባት በታማኝነት እና በጥራት ስናስረክብ ቆይተናል፡፡ አሁን ደግሞ እድለኛ ለሆኑ 3 የአዲስ አበባ ወይም ከአዲስ አበባ ውጪ ለሚኖሩ ነዋሪዎች የመኖርያ ቤት አፓርታማ ልንሸልምዎ ዝግጅታችንን ጨርሰናል፡፡ 1ኛ እጣ ባለ 3 መኝታ ከነሙሉ እቃው፡፡ 2ኛ እጣ ባለ 2 መኝታ ከነሙሉ እቃው፡፡ 3ኛ እጣ ባለ 1 መኝታ ከነሙሉ እቃው፡፡ ቀጥሎ ላሉ 30 እድለኞች የ 1000 ብር ያልተገደበ የ ኢንተርኔት አገልግሎት ሽልማት ይኖረዋል፡፡ ይህ እጣ የሚቆየው እስከ ሰኔ 30 ሲሆን ሰኔ 30 ላይ በኮምፒዩተር እጣ አወጣጥ ዘዴ በመታገዝ እድለኞችን ሰኔ 30 ላይ በዚ ቻናል ላይ ይፋ የምናደርግ ይሆናል፡፡ ከእናንተ ሚጠበቀው ቻናላችንን መቀላቀል እንዲሁም ደግሞ ለዘመድ አዝማድዎ ለወዳጅዎ እድላቸውን እንዲሞክሩ ቢያንስ ለ60 ሰዎች ሼር በማረግ እንዲቀላቀሉ መጋበዝ ብቻ ነው፡፡ ከ 60 ሰው በላይ መጋበዝ እድልዎን ያሰፋል፡፡ መልካም እድል ከ ጊፍት ሪልስቴት፡፡ https://t.me/Gift_Real_Estate1 https://t.me/Gift_Real_Estate1
Hammasini ko'rsatish...
#ቲንክአቢሲኒያ_የቡናቁርስ_መረጃዎች 1፤የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በ81ኛው የአርበኞች የድል በዓል ላይ በመገኘት የአበባ ጉንጉን አስቀመጡ፡፡ 81ኛ ዓመት የኢትዮጵያውያን አርበኞች የድል በዓል እየተከበረ ነው። የአርበኞች የጀግንነት ታሪክ በአሁኑ ትውልድ በሁሉም መስክ ሊደገም ይገባል ሲሉም የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ መልዕክት አስተላልፈዋል። በአዲስ አበባ አራት ኪሎ በሚገኘው የድል ሀውልት እናትና አባት አርበኞችን ጨምሮ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት እየተከበረ ይገኛል።የድል ቀኑ ከዛሬ 81 አመት በፊት ሚያዝያ 27 ጀግኖች አርበኞች በዱር በገደል ተዋድቀው ፋሽስት ጣልያንን በማሸነፍ የኢትዮጵያን ድል ያበሠሩበት ዕለት ነው። 2፤ሃይማኖትን ሽፋን ያደረገ የጥፋት ድርጊት ለመፈፀም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 145 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ። በጎንደር የተከሰተውን ሃይማኖትን ሽፋን ያደረገ የጥፋት ድርጊት ለመድገም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 145 ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዳማ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ። በሀገራዊ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የተኮረ ከ2 ሺህ በላይ ወጣቶች የተሳተፉበት የምክክር መድረክ በአዳማ ከተማ ተካሄዷል። የአዳማ ከተማ ከንቲባ አቶ ሃይሉ ጀልዴ እንደገለጹት ፅንፈኛ ኃይሎች ሃይማኖትን ሽፋን በማድረግ በጎንደር የፈፀሙትን የጥፋት ድርጊት ለማስፋትና ትርምስ ለመፍጠር ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 145 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ነው ያስተወቁት። በተጨማሪም ዘጠኝ የአሸባሪው ሸኔ አባላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ጠቁመው ህዝቡን በብልሹ አሰራርና ሌብነት ያስመረሩ 69 አመራሮች ላይ ደግሞ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን ከንቲባው አክለው ተናግረዋል። 3፤በኢትዮጵያ ለመጀመርያ ጊዜ የአለም አቀፍ የእሳት አደጋ ሰራተኞችን ቀን ሊከበር መሆኑ ተነገረ። የእሳት እና የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግኑኝነት ባለሙያዉ አቶ ንጋቱ ማሞ እንደተናገሩት፣ ይህ ቀን መከበሩ የሰውን ህይወትና ንብረት ለመታደግ ሲሉ የህይወትና የአካል መስዋዕትነት ለሚከፍሉት ለአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ትልቅ የሞራል ስንቅ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በሌላ በኩል ህብረተሰቡና መንግስት የአደጋ መቆጣጠር ስራን በጥልቀት ተረድተው ለመደገፍና ተገቢውን ከበሬታ ለመስጠት ያስችላቸዋል ሲሉም አክለዋል፡፡ የእሳት አደጋ ሠራተኞች ቀን መከበር የጀመረው በፈረንጆቹ 1999 አውስትሪያሊያ ቪክቶሪያ ሊንቶን ውስጥ በተነሳው የሰደድ እሳት ቃጠሎ ምክንያት፣ የሰው ህይወትና ንብረት ለማዳን ሲሉ 5 የእሳት አደጋ ሰራተኞች በአሳዛኝ ሁኔታ ህይወታቸውን ማጣታቸው ከተሰማ በኋላ መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ 4፤የአውሮፓ ኅብረት በሩሲያ ላይ አዲስ ማዕቀብ እንዲጣል የውሳኔ ሃሳቦችን አቀረበ። ይህም በዓመቱ መገባደጃ ላይ የሩስያ ነዳጅ ወደ ህብረቱ አገራት እንዳይገባ አጠቃላይ እገዳን የሚጨምር ሲሆን እቅዱ የአባል ሀገራቱን ይሁንታ ያስፈልገዋል።ማዕቀቡ በጦር ወንጀል የተጠረጠሩትን ጨምሮ በግለሰቦች ላይ የሚጣሉ ማዕቀቦችንም ያካትታል። የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በሩሲያ ላይ ሊጣሉ ስለሚችሉ ተጨማሪ ማዕቀቦች በዚህ ሳምንት ከቡድን ሰባት (G7) የላቀ የአለም ኢኮኖሚ መሪ ሀገራት ጋር እንደሚነጋገሩ ገልፀዋል።ጦርነቱ ወደ ዩክሬን ጎረቤት ሊዛመት ይችላል በሚል ስጋት የአውሮጳ ህብረት ለሞልዶቫ ተጨማሪ ወታደራዊ ድጋፍ ለመስጠት ማቀዱን አስታውቋል። 5፤በድራማ በታጀበው ምሽት ሪያል ማድሪድ የፍፃሜ ተፋላሚ መሆኑን አረጋግጧል። የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የግማሽ ፍፃሜ የመልስ ጨዋታ በሳንቲያጎ በርናቦ ቀጥሎ ሲካሄድ ሪያል ማድሪድ በድምር ውጤት ማንችስተር ሲቲን 6 - 5 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የፍፃሜ ተፋላሚ መሆናቸውን አረጋግጠዋል ። የሪያል ማድሪድን የማሸነፊያ ግቦች ካሪም ቤንዜማ እና ሮድሪጎ ሁለት ግቦችን አስቆጥረዋል ። የማንችስተር ሲቲን ብቸኛ ግብ ሪያድ ማህሬዝ ከመረብ ላይ አሳርፏል ።ካሪም ቤንዜማ በዘንድሮ የውድድር አመት በ 58 ግቦች ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎን አድርጓል ። ሪያል ማድሪድ ለአስራ ሰባተኛ ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍፃሜ ተፋላሚ መሆናቸውን አረጋግጠዋል ። ሪያል ማድሪድ ሊቨርፑልን በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ ይገጥማል ። የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ ግንቦት 20 በፈረንሳይ ርዕሰ መዲና ፓሪስ የሚካሄድ ይሆናል ። መልካም የአርበኞች ቀን❗️
Hammasini ko'rsatish...
#HawassaUniversity በ2014 ዓ.ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች ምዝገባ #በኦንላይን ከግንቦት 01 እስከ 05/2014 ዓ.ም ድረስ እንደሚከናወን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል። የተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ የመግቢያ እና ሪፖርት ማድረጊያ ጊዜ ግንቦት 08 እና 09/2014 ዓ.ም በዋናው ግቢ እንደሆነ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡ ስለምዝገባ ሂደቱ ዝርዝር መረጃዎች በተቋሙ ድረ-ገጽ https://hu.edu.et እና በዩኒቨርሲቲው የማኅበራዊ ገጾች ይገለጻል ተብሏል፡፡ ተማሪዎች ወደ ተቋሙ ሲሄዱ ሊይዟቸው የሚገቡ፦ • የ12ኛ እና የ10ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ዋናውና ኮፒው • ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው • ጉርድ ፎቶግራፍ (4) • የሌሊት አልባሳት • የስፖርት ትጥቅ ትምህርት አቋርጣችሁ ለመልሶ ቅበላ ውጤታችሁ የሚያበቃችሁ ተማሪዎች አዲስ ከተመደቡ ተማሪዎች ጋር በመቅረብ በ2014 ዓ.ም የመጀመሪያ ሴሚስተር ለመልሶ ቅበላ ግንቦት 10 እና 11/2014 ዓ.ም ማመልከት እንደምትችሉ ተገልጿል፡፡ ከተጠቀሱት ቀናት ውጪ የሚመጡ ተማሪዎችን የማያስተናግድ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
Hammasini ko'rsatish...
የዩኒቨርሲቲዎችን ትክክለኛ ገፅ ብቻ በመከተል ከሀሰተኛ የዩኒቨርሲቲ ጥሪዎች እራሳችሁን ጠብቁ ፦ 👉 ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/DDUniv/ 👉 ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/Hawassa.University/ 👉 አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/Addis-Ababa-University-496255483792611/ 👉 ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/TheUniversityofGondar/ 👉 ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/bduethiopia/?ref=page_internal&mt_nav=0 👉 አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/ArbaMinchUniversityCCD/?_se_imp=0ueaW0ZojpEObV9zR 👉 ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/HRMUNIV/ 👉 ጅማ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/JimmaUniv/ 👉 አርሲ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=357578986410375&id=100064748293256 👉 ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ፦https://m.facebook.com/pages/category/Education-website/Wolaita-Sodo-University-246568056057804/ 👉 ዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/WachemoUniversity2008/ 👉 ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://www.facebook.com/265529850297666/posts/1845133279003974/?app=fbl 👉 መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://www.facebook.com/141864125910414/posts/4794315817331865/?app=fbl 👉 ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/pages/category/Education-website/Wollega-University-Corporate-Communications-2319182621440303/ 👉 አሶሳ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://www.facebook.com/234983083247967/posts/5141798579233035/?app=fbl 👉 ወራቤ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://www.facebook.com/2181225212102194/posts/3109977289226977/?app=fbl 👉 ቦረና ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/BoranaUniversityBRU/ 👉 ቀብሪድሃር ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/pages/category/Education/Kebri-Dehar-University-306587496533329/ 👉 ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/pages/category/Education/Jinka-University-178538809733160/ 👉 ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ፦ https://www.facebook.com/547073878695780/posts/5065885566814566/?app=fbl 👉 ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://www.facebook.com/1879460055640998/posts/3057857987801193/?app=fbl 👉 ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/WoldiaUniversity/ 👉 ወሎ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/WolloUniversity111/ 👉 ደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://www.facebook.com/1301588393256101/posts/5145148712233364/?app=fbl 👉 ኦዳቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/OBUEthiopia/ 👉 አምቦ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/AmboUniversityofficial/ 👉 ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/Mizan-Tepi-University-MTU-362390684253048/ 👉 ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://www.facebook.com/614590095253065/posts/5432186613493365/?app=fbl 👉 ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://www.facebook.com/979926502053136/posts/5129611493751262/?app=fbl 👉 ሰመራ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://www.facebook.com/336146983089022/posts/5029908297046177/?app=fbl 👉 ኮተቤ ፦ https://www.facebook.com/792405150779154/posts/5397052686981021/?app=fbl 👉 ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://www.facebook.com/100064618752509/posts/386404006856888/?app=fbl 👉 መቱ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://www.facebook.com/330316734055129/posts/1468350973585027/?app=fbl
Hammasini ko'rsatish...
Dire-Dawa University

Dire-Dawa University, Dire Dawa. 60,625 likes · 667 talking about this · 17,987 were here. Dire-Dawa University aspires to be a premium choice in Ethiopia and among the top ten Applied Science...

የዩኒቨርሲቲ ምደባ ይፋ ሆነ ሚያዝያ 17/2014 (ዋልታ) ትምህርት ሚኒስቴር የ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርሲቲ ምደባ ይፋ አደረገ። የ2013 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር ዐቀፍ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ መንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) የመግቢያ መቁረጫ ነጥብ ላመጡ ተማሪዎች ምደባ ተደርጓል። በዚህም መሰረት ተማሪዎች ከዛሬ ጀምሮ የተመደቡበትን ዩኒቨርሲቲ ለማየት በድረ ገፅ፡-https://result.ethernet.edu.et ፣ በSMS፡- 9444 እንዲሁም በቴሌግራም፡- @moestudentbot መጠቀም ይችላሉ ነው የተባለው። ተማሪዎች ከምደባ ጋር ተያይዞ ላላችው ማንኛውም ጥያቄ በድረ ገፅ https://complaint.ethernet.edu.et በማመልከት ጥያቄዎቻቸውን ማቅረብ እንደሚችሉ የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል። ዩኒቨርሲቲዎች እስከ ሚያዝያ 24 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ ተገቢውን ዝግጅት አድርገው የመጀመሪያ ዓመት አዲስ ገቢ ተማሪዎችን የቅበላ መርኃ ግብር የሚያሳውቁ በመሆኑ ተማሪዎች አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉም ሚኒስቴሩ ጥሪ አቅርቧል። ከዚህ በፊት በተገለጸው የመቁረጫ ነጥብ እና ከኦሮሚያ፣ አማራ፣ አፋር እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ተጨማሪ ተማሪዎች ምደባ የሚያስገኝላቸው ውሳኔ መተላለፉ ይታወሳል። ለፈጣን መረጃዎች፦ ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
Hammasini ko'rsatish...
WMCC

WMCC, Addis Ababa, Ethiopia. 685,104 likes · 33,565 talking about this. Walta Media and Communication Corporate

የ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት በድጋሜ እንዲታይ የሚጠይቅ ሰላማዊ ሰልፍ በደብረ ማርቆስ ከተማ ተደርጓል። የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ መሆንን ተከትሎ በርካታ ቅሬታዎች እና ተቃውሞች ከተለያዩ አካባቢዎች መሰማታቸውን ቀጥለዋል። ወደ አዲስ አበባ መርማሪ ቡድን የላከው የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ፤ በ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች የዩኒቨርሰቲ መግቢያ ጊዜ እንዲራዘም መጠየቁም ይታወቃል። የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ እና ሌሎች የሲቪክ ማኅበራት መንግስት በቀረቡ ቅሬታዎች ላይ አፋጣኝ እና ግልጽ ምላሽ እንዲሰጥ ጠይቀዋል። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በበኩሉ ከ20 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የተማሪዎች ቅሬታ ምላሽ መስጠቱን መግለጹ አይዘነጋም። በፈተናው ውጤት ላይ የሚነሱ ቅሬታዎች በተለይ ከአማራ ክልል አሁንም እየተሰሙ ነው። መምህራን፣ ተማሪዎች እና የተማሪዎች ቤተሰቦች የተሳተፉበትና የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤቱ በድጋሜ እንዲታይ የማጠይቅ ሰላማዊ ሰልፍ ዛሬ መጋቢት 15/2014 ዓ.ም በደብረ ማርቆስ ከተማ ተካሂዷል። የአማራ ተማሪዎች ማኅበር እና የአማራ ወጣቶች ማህበር ሰላማዊ ሰልፉን እንደጠሩት ታውቋል። በሁሉም የአማራ ክልል ከተሞች የፊታችን እሁድ መጋቢት 18/2014 ዓ.ም ሰላማዊ ሰልፍ እንዲካሄድ ጥሪ መደረጉም ተሰምቷል። ተማሪዎች በጦርነት ቀጠና ውስጥና ከተፈጠረባቸው የስነ ልቦና ችግር ሳይወጡ ፈተናውን እንደወሰዱ ግምት ውስጥ መግባት እንዳለበት አስተያየታቸውን ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ያደረሱ ተማሪዎች ገልጸዋል።
Hammasini ko'rsatish...
የ2013ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ማለፊያ ነጥብ ይፋ ሆነ። የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስቴር ዴኤታ ሳሙኤል (ዶ/ር) ለጋዜጠኞች የ12ኛ ክፍል መለቀቂያ ፈተና መቁረጫ ነጥብ ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። በሁለት ዙር ለተሰጠው የመልቀቂያ ፈተና የተሰጠው የማለፊያ ነጥብ የተለያየ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በዚህም መሰረት በመጀመሪያ ዙር ፈተናቸውን የወሰዱ የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች ውጤት የሚከተለውን ይመስላል በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ለመማር ለተፈጥሮ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞት ማለፊያ ነጥብ ለወንድ 363 ለሴት 351 ሲሆን በተፈጥሮ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 351 ለሴት 339 ማለፊያ ነጥብ መሆኑ ተገልጿል።ለተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 300 ሆኗል።በተፈጥሮ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ማለፊያ ነጥብም 380 ሆኖ መቆረጡ ተገልጿል። በመጀመሪያው ዙር የተፈተኑ እና በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የተፈጥሮ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ 300 ሆኗል። ለማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች የማለፊያ ነጥብ ለወንድ 264፣ ለሴት 254 ሲሆን በማህበራዊ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 254፣ ለሴት 250 ማለፊያ ነጥብ ሆኖ ተቆርጧል። ለማህበራዊ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታዎች ማለፊያ ነጥብ 250 መሆኑን እና በማህበራዊ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ለሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 280 እንደሆነ ተገልጿል። በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የማህበራዊ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ 250 ሆኗል። በሁለተኛ ዙር ፈተናቸውን የወሰዱ የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች ውጤትም ይፋ የሆነ ሲሆን በዚህም መሰረት በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ለመማር ለተፈጥሮ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞት ማለፊያ ነጥብ ለወንድ 423 ለሴት 409 ሲሆን በተፈጥሮ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 410 ለሴት 396 ማለፊያ ነጥብ መሆኑ ተገልጿል።ለተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 350 ሆኗል።በተፈጥሮ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ማለፊያ ነጥብም 443 ሆኖ መቆረጡ ተገልጿል። በሁለተኛ ዙር የተፈተኑ እና በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የተፈጥሮ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ ከ350 በላይ መሆኑ ተነግሯል። ለማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች የማለፊያ ነጥብ ለወንድ 317 ፣ ለሴት 305 ሲሆን በማህበራዊ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 305፣ ለሴት 300 ማለፊያ ነጥብ ሆኖ ተቆርጧል። ለማህበራዊ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታዎች ማለፊያ ነጥብ 300 መሆኑን እና በማህበራዊ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ለሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 335 እንደሆነ ተገልጿል። በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የማህበራዊ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ ከ 300 በላይ መሆኑም ተገለጿል። ውጤቱ ለመጀመርያ ዙር ተፈታኞች ለተፈጥሮ ሳይንስ ከ600 እዲሁም ለማህበራዊ ሳይንስ ከ500 የተያዘ መሆኑን እና በሁለተኛ ዙር ተፈታኞች ለተፈጥሮ ሳይንስ ከ700 እዲሁም ለማህበራዊ ሳይንስ ከ600 የተያዘ መሆኑ ተገልጿል። ምንጭ፦ ትምህርት ሚኒስቴር
Hammasini ko'rsatish...
በመንግሥት የአሰራር ሥርዓት ውስጥ ያለውን ሌብነትና ብልሹ አሰራር እንታገላለን ሲሉ የብልጽግና ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። ፍትኃዊ በሆነ መንገድ ጉዳይ ከማስፈጸም ይልቅ እጃቸውን በማስረዘም በመንግስትና በህዝብ መካከል ልዩነት እንዲፈጠር የሚያደርጉ ተገልጋዮች ከድርጊታቸው መታቀብ እንዳለባቸውም አሳስበዋል። በኢትዮጵያ ሙስናና ብልሹ አሰራር ከባለስልጣናት እስከ ታችኛው የማኅበረሰብ ክፍል እየተለመደና እየተባባሰ በመሆኑ ለውድቀት እየዳረገ ነው፡፡ የብልጽግና ፓርቲ ባለስልጣናት በኢትዮጵያ ሙስናና ብልሹ አሰራር በተወሳሰበ መንገድ እየተፈጸመ በመሆኑ ለፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ግሽበት እየዳረገን ነው ብለዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደርና የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር ዶክተር ነጋሽ ዋጌሾ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ሌብነት ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ብልሽት ውስጥ እየከተተን ነው። በኢትዮጵያ ሌብነትና ብልሹ አሰራር ከከፍተኛ ባለስልጣናት እስከ ታችኛው የማህበረሰብ ክፍል የተለመደ በመሆኑ እስከመጨረሻው መጥፋት እንዳለበት ገልጸዋል። ለዚህ ደግሞ የብልጽግና ፓርቲ አመራረና አባላት በመንግስት መዋቅር ውስጥ የሚፈጸመውን ሌብነት ግንባር ቀደም ሆነው የሚከላከሉበት ስርዓት እውን ይሆናል ብለዋል። የአማራ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ሀላፊና የብልጽግና ፓርቲ አመራር አቶ ቀለመወርቅ ምህረቴ፤  በኢትዮጵያ ሙስናና ብልሹ አሰራር በመንግስት መዋቅር ውስጥ ፈታኝ ሆነው ቀጥሏል። በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ሙስናን ለመከላከል የሚያስችሉ አሰራሮች ተዘርግተው የነበረ ቢሆንም ከዋና አላማቸው በተፃራሪ ንጹሃን የሚያጠቁበት በመሆኑ ትምህርት አልተወሰደበትም ብለዋል። በመሆኑም ሙስናና ብልሹ አሰራር ህዝቦችን ለችግር አገርን ለብተና የሚዳርግ በመሆኑ በእጅ መንሻ የሚሰጥን አገልግሎት መጸየፍ በአስተሳሰብ መስረጽ አለበት ብለዋል። የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሮ ሀቢባ ሲራጅና የትግራይ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ገብረፃድቅ ገብረመድህን፤ ሌብነትን መከላከል እንደ ፓርቲም እንደ መንግስትም ቅድሚያ የሚሰጠው ነው። ሌብነትን ለማስቀረት ግልጽነትና ተጠያቂነት መስፈን እንዳለበት ጠቅሰው፤ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ባለፉት አምስት ወራት ብቻ ከመሬት ጋር በተያያዘ 67 ሰዎች ለህግ እንዲቀርቡ ተደርጓል ብለዋል። በመንግሥት ተቋማት ግልጽ አሰራርና የተጠያቂነት ስርዓት በማስፈን ሙስናን ከምንጩ መከላከል ይቻላል፤ ለዚህ ደግሞ ገዥው ፓርቲ ብልጽግናና መንግስት ቁርጠኛ ናቸው ነው ያሉት። ሙስናና ብልሹ አሰራር በመንግስት ተቋማት በአመራሮችና ሰራተኞች ብቻ የሚፈጸም አይደለም ያሉት አስተያየት ሰጭዎቹ፤ ቅድሚያ አገልግሎት ለማግኘት ረጅም እጃቸውን የሚዘረጉ ተገልጋዮችም እንዳሉ ጠቁመዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማግኘት የሚገባውን አገልግሎት በነፃ ማግኘት፤ አገልጋዮችም ያለምንም የእጅ መንሻ ሰዎችን እንደ አመጣጣቸው በእኩልነት ማስተናገድ አለባቸው ብለዋል። ፍትኃዊ በሆነ መንገድ ጉዳይ ከማስፈጸም ይልቅ እጃቸውን በማስረዘም በመንግሥትና ህዝብ መካከል ልዩነት እንዲፈጠር የሚያደርጉ ተገልጋዮች ከድርጊታቸው እንዲታቀቡም የአማራ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ሀላፊና የብልጽግና ፓርቲ አመራር አቶ ቀለመወርቅ ምህረቴ ጠይቀዋል። በኢትዮጵያ አሁን ያለው ነባራዊ ሁኔታ ለሙስናና ብልሹ አሰራር ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን የገለጹት አቶ ቀለመወርቅ፤ አገር ስትረጋጋና ወደ ሰላም ስትመለስ ሁሉም ይስተካከላል፤ ለዚህ ደግሞ ተግተን እንሰራለን ብለዋል፡፡
Hammasini ko'rsatish...
የብልፅግና ፓርቲ ጉባኤ በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል 👉 ዝግጅቶቹ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቁ ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችም ይፋ ተደርገዋል፣ **** (ኢ ፕ ድ) ጉበኤው ተከትሎ የሚናወኑ ልዩ ልዩ ተግባራት ስኬታማ ሆነው እንዲጠናቀቁ ለማስቻል የፀጥታ አካላት አስፈላጊውን ዝግጅት አጠናቀው ወደ ስራ መግባታቸውን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቀ ፡፡ ከዛሬ መጋቢት 2 ቀን 2014 ዓ/ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ መጋቢት 4 ቀን 2014 ዓ/ም ከተማችን አዲስ አበባ አንደኛውን የብልፅግና ፓርቲ ጉባኤ እያስተናገደች ትገኛለች፡፡ ጉባኤውን ተከትሎ መጋቢት 2 ቀን እና መጋቢት 5 ቀን 2014 ዓ/ም በአዲስ አበባ ልዩ ልዩ ፕሮግሞች ይካሄዳሉ፡፡ ጉባኤው እና ተያያዥ ጉዳዮች በስኬት እንዲጠናቁ የፀጥታ አካላት አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አጠናቀው ወደ ስራ መግባታቸውን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል፡፡ 👉 በዚህ መሰረት መጋቢት 2 ቀን 2014 ዓ/ም ምሽት ድረስ አራት ኪሉ አካባቢ የሚካሄደው ፕሮግራም ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ከተለያዩ አቅጣጫዎች ወደ አራት ኪሎ የሚወስዱ መንገዶች፤  ከፍል ውሃ ወደ ሸራተን ሆቴል  ከኦርማ ጋራዥ በሸራተን ሆቴል ወደ ንግድ ማተሚያ  ከቴዎድሮስ አደባባይ ወደ ኮንሰን  ከአምባሳደር መናፈሻ ወደ ሸራተን ሆቴል 👉 በተመሳሳይ መጋቢት 5 ቀን 2014 ዓ/ም የሚካሄደው ተመሳሳይ ፕሮግራም ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ወደ አራት ኪሎ የሚውስዱ መንገዶች  ከቀበና በቤልኤር ወደ አራት ኪሎ የሚወስደው መንገድ ቤልኤር መብራት  ከስድስት ኪሎ ወደ አራት ኪሎ የሚወስደው መንገድ ቅድስተ ማርያም ትራፊክ መብራት  ከፒያሳ በሰባ ደረጃ ቅድስተ ማርያም የሚወስደው መንገድ አራዳ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ቢሮ  ከቴዎድሮስ አደባባይ በእሪ በከንቱ ወደ አራት ኪሎ የሚወስደው መንገድ እሪ በከንቱ መብራት  ከአዋሬ ገበያ በጥይት ቤት አራት ኪሎ የሚወስደው አዋሬ አደባባይ  ከኮንሰን ወደ ፓርላማ የሚወስዱት መንገዶች በተጠቀሱት ቀናት ዝግጅቶቹ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቁ ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ ስለሚሆኑ አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ እና ለትራፊክ ፖሊስ አባላት ትእዛዝ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል፡፡
Hammasini ko'rsatish...
ባንኩ ደንበኞች በማንኛውም ጊዜ መረጃቸውን በማስተካከል አገልግሎት ማግኘት እንደሚችሉ አስታወቀ መጋቢት 2/2014 (ዋልታ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደንበኞች በማንኛውም ጊዜ መረጃቸውን በማስተካከል አገልግሎት ማግኘት እንደሚችሉ አስታውቋል፡፡ ባንኩ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አ.ኤ.አ በ27/08/2021 ያወጣውን መመሪያ ተከትሎ የደንበኞችን መረጃ የማደራጀትና የማጥራት ሥራ ላለፉት 6 ወራት በመሥራት ላይ መሆኑን አስታውሷል፡፡ እስካሁን በርካታ ደንበኞች መረጃቸውን በባንኩ ቅርንጫፎች በመገኘት ወቅታዊ ማድረጋቻውን አስታውቋል፡፡ ሆኖም እስከ ዛሬው ዕለት ድረስ በተለያዩ ምክንያቶች መረጃቸውን ወቅታዊ ማድረግ ያልቻሉ ደንበኞች የባንኩ የዲጂታል ባንኪንግ አግልግሎቶች ብቻ ማለትም (የሞባይል ባንኪንግ፣ የኢንተርኔት ባንኪንግ እንዲሁም የኤቲኤም እና የፖስ አገልግሎት) እንደሚቋረጥባቸው ገልጿል። ይሁን እንጂ ደንበኞች በማንኛውም ጊዜ ግን ወደ ባንኩ ቅርንጫፎች በመምጣት መረጃቸውን ሲያስተካክሉ ወዲያውኑ አገልግሎቶችን ማግኘት እንደሚችሉ አስታውቋል፡፡
Hammasini ko'rsatish...