ወንጌል ያሸንፋል️
"ለአሕዛብም ሁሉ ምስክር እንዲሆን ይህ የመንግሥት ወንጌል በዓለም ሁሉ ይሰበካል፥ በዚያን ጊዜም መጨረሻው ይመጣል።" (የማቴዎስ ወንጌል 24: 14) ☞ ቻናላችንን በዩቲዩብ ለመከታተል👇 ይጫኑት። http://bit.ly/2KM5PzL ለሀሳብ አስተያየት👇 📨 @ApostleAbz ☞ አብረውን ለማገልገል #0930703775 ይደውሉ።
Ko'proq ko'rsatish- Kanalning o'sishi
- Post qamrovi
- ER - jalb qilish nisbati
Ma'lumot yuklanmoqda...
Ma'lumot yuklanmoqda...
መንፈሳዊ ስጦታዎች 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 ክፍል 39 ✍✍✍ የመፈወስ ስጦታ 🌾🌾🌾🌾🌾 የፈውስ ስጦታ በሰውነት ላይ ያለን ማንኛውንም ደዌ የምናራግፍበት ስጦታ ብቻ አይደለም።በብሉይ ኪዳን ያሉ መጵሐፍትን ስናነብ ሀገር እንደ ሀገር ከገባበት ውጥንቅጥ እንዲወጣ ምድሪቷ ህዝቦቿ እንዲሁም የሚያጨነግፍው ውሃዎች እንደተፈወሱ ተፅፎልናል። በኤርሚያስ የትንቢት መጵሐፍ ውስጥ እግዚአብሄርን ባለማወቅ እግዚአብሄርን በመበደልና በመካድ የረከሰችው እስራኤልና ይሁዳ ምድሪቱ በኃጢያት ምክንያት ፈፅማ የረከሰች ለጠላቶቿም ተላልፋ እንድትሰጥ የተፈረደባት እንደነበረች እና ኤርሚያስ ግን ፈውስን ይጠብቅ እንደነበር ተፅፎዓል። “ሰላምን ተስፋ አደረግን፤ መልካም ነገር ግን አልመጣም፤ የፈውስ ጊዜን ተመኘን፤ ነገር ግን ሽብር ብቻ ሆነብን።” ኤርምያስ 8፥15 (አዲሱ መ.ት) “ምድሪቱ በዝናብ እጦት የምትጐዳው፣ የሜዳውም ሣር ሁሉ በድርቅ የሚመታው እስከ መቼ ነው? ከነዋሪዎቿ ክፋት የተነሣ፣ እንስሳትና አዕዋፍ ጠፍተዋል፤ ደግሞም ሕዝቡ፣ “በእኛ ላይ የሚሆነውን አያይም” ብለዋል።”ኤርምያስ 12፥4 (አዲሱ መ.ት) በኤልሳ ዘመን የኢያሪኮ ከተማ ለኑሮ የተመቸች ከተማ ነበረች ዳሩ ግን ውሃው መጥፎ ከመሆኑ የተነሳ ምድሪቱ ፍሬ እንዳትሰጥ አድርጎት ነበር ወይም ምድሪቱን ጭንጋፍ አድርጓት ነበር።ኤልሳም በእግዚአብሄር መንፈስ ተመርቶ በአዲስ ማሰሮ ውስጥ ጨው በማድረግ ወደ ውሃው ምንጭ በመሄድ ጨው ጣለበትና እግዚአብሄር የተናገረውን ቃል ለህዝብ ተናገረ ።እግዚአብሄር ውሃውን ፈውሼዋለው አለ ውሃውም ተፈወሰ። 2ኛ ነገሥት 2 (አዲሱ መ.ት)¹⁹ የከተማዪቱም ሰዎች ኤልሳዕን፣ “እነሆ ጌታችን፤ እንደምታያት ይህች ከተማ ለኑሮ የተመቸች ናት፤ ይሁን እንጂ ውሃው መጥፎ ሲሆን ምድሪቱም ፍሬ የማትሰጥ ናት” አሉት።²⁰ እርሱም፣ “እስቲ በአዲስ ማሰሮ ጨው…
መንፈሳዊ ስጦታዎች 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 ክፍል 37 ✍✍✍ ተዓምራት የማድረግ ስጦታ 🌾🌾🌾🌾🌾🌾🌾🌾 ተዓምራዊ ምልክቶች እግዚአብሄር ህዝቦቹን በሙሉ ወደ እኛ የሚጠራበት የሚሰበስብበት መንገድ ነው።ሐዋሪያው ጴጥሮስና ዮሐንስ በኢየሩሳሌም ወደ ቤተመቅደስ ለዘጠኝ ሰዓቱ ፀሎት ሲሄዱ በዕብራይስጥ ውብ ወይም መልካም በሚሏት መመላለሻ ሰዎች እያመጡ የሚያስቀምጡት ከአርባ አመት የሚበልጠው መራመድ የማይችል ሽባ ሰው መዳን ህዝብን በሙሉ በሰለሞን አደባባይ ላይ ዕለት ዕለት ወደ ሚሰበሰብ ሐዋሪያት ስቦዓቸዋል። “እርሱም ጴጥሮስንና ዮሐንስን ይዞ ሳለ፥ ሕዝቡ ሁሉ እየተደነቁ የሰሎሞን ደጅ መመላለሻ በሚባለው አብረው ወደ እነርሱ ሮጡ።” — ሐዋርያት 3፥11 እግዚአብሄር ተዓምራቶችን የሚያደርገው ህዝብን አንተን አንቺን ለማስደነቅ ሳይሆን ባየውና በሰማው ነገር ተደንቆ ለመጣው ህዝብ የሚደንቀውን የክርስቶስን የመስቀል ላይ ስራ እንድንመሰክር ነው።ጴጥሮስ ወደ እነርሱ በመገረምና በመደነቅ ለተሰበሰበው ህዝብ አይኖቻቸውን ከእነርሱ ላይ በማንሳት ወደ እግዚአብሄር ወደ ኢየሱስ ዞር ለማድረግ ኢየሱስን ሰበከ ።እኛም እኛ እንደሰራነው መደነቅ የለብንም ይልቁንም እግዚአብሄር ለምን ታምራት ድንቆችችና ምልክቶችን እንዳደረገ በመረዳት አጋጣሚውን ተጠቅመን ራሳችንን ሳይሆን ኢየሱስንና የኢየሱስን መስበክ አለብን። ሐዋርያት 3 (አዲሱ መ.ት)¹² ጴጥሮስም ይህን ባየ ጊዜ እንዲህ አላቸው፤ “የእስራኤል ሕዝብ ሆይ፤ በዚህ ለምን ትደነቃላችሁ? ደግሞም በእኛ ኀይል ወይም በእኛ ጽድቅ ይህ ሰው ድኖ እንዲመላለስ እንዳደረግነው በመቊጠር፣ ለምን ወደ እኛ አትኵራችሁ ትመለከታላችሁ?¹³ የአባቶቻችን አምላክ፣ የአብርሃም፣ የይስሐቅና የያዕቆብ አምላክ ብላቴናውን ኢየሱስን አከበረው፤ እናንተ ግን እንዲሞት አሳልፋችሁ ሰጣችሁት፤ ጲላጦስ ሊፈታው ቢፈልግም እናንተ…
መንፈሳዊ ስጦታዎች 🔥🔥🔥🌾🌾🔥🔥 ክፍል 42 ✍✍✍ መናፍስትን የመለየት ስጦታዎች 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 መንፈሳዊ ስጦታዎችን ስናጠና አብዛኛዎቹ ስጦታዎች የመናገር ስጦታዎች ናቸው።“ለአንዱ በመንፈስ የጥበብን ቃል መናገር ይሰጠዋል፤ ለሌላው ደግሞ በዚያው መንፈስ የዕውቀትን ቃል መናገር ይሰጠዋል፤”1ኛ ቆሮንቶስ 12፥8 (አዲሱ መ.ት)ከጥበብና ዕውቀት ውጪ ትንቢትን መናገር ልሳን መናገር እነዚህ ሁሉ በንግግር የሚገለጡ ስጦታዎች ናቸው። መናፍስትን የመለየት ስጦታ ሰዎች የሚናገሩበት መንፈስ የመለየት ስጦታ ነው።የእግዚአብሄር የሚመስል ቃል የሚናገር ሁሉ የእግዚአብሄር ሰው አይደለም።በመቄዶኒያ ዋና ከተማ በፊሊጲሲዮስ እነ ጳውሎስን የፈተናቸው ጉዳይ ይህ ነበር። ሐዋርያት 16 (አዲሱ መ.ት)¹⁶ አንድ ቀን ወደ ጸሎት ስፍራ ስንሄድ፣ በጥንቈላ መንፈስ ትንቢት የምትናገር አንዲት የቤት አገልጋይ አገኘችን፤ እርሷም በዚህ የጥንቈላ ሥራዋ ለአሳዳሪዎችዋ ብዙ ገንዘብ ታስገኝላቸው ነበር።¹⁷ ይህችው አገልጋይ ጳውሎስንና እኛን እየተከተለች፣ “እነዚህ ሰዎች የመዳንን መንገድ የሚነግሯችሁ፣ የልዑል እግዚአብሔር አገልጋዮች ናቸው!” በማለት ትጮኽ ነበር፤¹⁸ ይህንም ብዙ ቀን ደጋገመችው፤ ጳውሎስ ግን በዚህ እጅግ በመታወኩ ዘወር ብሎ ያን መንፈስ፣ “ከእርሷ እንድትወጣ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አዝሃለሁ” አለው፤ መንፈሱም በዚያው ቅጽበት ወጣላት። ሴትዮዋ የምትናገረውን ንግግር ብቻ ከወሰድነው የእግዚአብሄር አገልጋይ እንጂ ጠንቋይ አትመስልም እንደውም ለነ ጳውሎስ እውቅና የምትሰጥ ሴት ነው የምትመስለው የምትናገርበት መንፈስን ግን እነ ጳውሎስ ራሱ የለዮት ከብዙ ጊዜ በዋላ ነው። መናፍስትን ስለመለየት ሳጠና በጣም የገረመኝን አንድ ክፍል ልንገራችሁ ሰይጣን ሰዎችን እውነተኛ አገልጋይ መሆን አለመሆናቸውን ያውቃል የኢየሱስን…
መንፈሳዊ ስጦታዎች 🍁🍁🍁🌾🍁🍁🍁 ክፍል 35 ✍✍✍ ተዓምራትን የማድረግ ስጦታዎች ✋🤚✋🤚✋🤚✋🤚✋🤚 ተዓምራት የሌለው የሚፈጠርበት ያለው አካላዊ ለውጥ የሚያደርግበት መለኮታዊ ችሎታ ነው።ለምሳሌ ውሃ የወይን ጠጅ ሲሆን አካላዊ ለውጥ አምጥቷል በደረቅ ግንባር አይን ሲፈጠር ደግሞ የሌለው ተፈጥሮአል። ኢየሱስ ሰባት ተዓምራዊ ምልክቶችን ማድረጉ በዮሐንስ ወንጌል ላይ ተመዝግቦልና እነዚህን ሰባት ተዓምራዊ ምልክቶችን በማጥናት ተዓምራዊ ምልክት ማለት ምን ማለት እንደሆነ መረዳት ይቻላል ስለዚህም እንድታጠኑት እጋብዛለው። ተዓምራዊ ምልክቶች የሚያደርገው እግዚአብሄር ሲሆን የሚደረጉበት ምክንያት እኛ የእግዚአብሄርን ቃል ስንሰብክ መልዕክቱ ከእኛ ሳይሆን ከራሱ መሆኑን ለማሳየት እግዚአብሄር ተዓምራዊ ምልክቶችን ያደርጋል። ተዓምራዊ ምልክቶች እግዚአብሄር የእኛ አገልግሎት እውነተኛ መሆኑን የሚመሰክርበት መንገድ ነው።እግዚአብሄር ለኢየሱስ እንዴት ባለ መልኩ እንደመሰከረለት ጴጥሮስ እንዲህ ብሎ ነበር፡"““የእስራኤል ሰዎች ሆይ፤ ይህን ቃል ስሙ፤ እናንት ራሳችሁ እንደምታውቁት፣ እግዚአብሔር በመካከላችሁ ታምራትን፣ ድንቅ ነገሮችንና ምልክቶችን በእርሱ በኩል በማድረግ ለናዝሬቱ ኢየሱስ መስክሮለታል።” — ሐዋርያት 2፥22 (አዲሱ መ.ት) በተጨማሩም በሐዋሪያቱ በበርናባስ በጳውሎስ የተሰበከውን ቃል ጌታ በብዙ ምልክቶችና ድንቅ ተዓምራት እንዳረጋገጠ ተፅፎዓል። “ጳውሎስና በርናባስም ስለ ጌታ በድፍረት እየተናገሩ ብዙ ጊዜ እዚያው ቈዩ፤ ጌታም የሚናገሩትን የጸጋውን ቃል በታምራዊ ምልክትና በድንቅ ሥራ እየደገፈ ያረጋግ ጥላቸው ነበር።” — ሐዋርያት 14፥3 (አዲሱ መ.ት) ስለዚህ በአጭር አማርኛ ታምራት ድንቆችና ምልክቶች እግዚአብሄር ለእኛ እየመሰከረልን ወይም በእኛ የሚሰበከው የምስራች እውነተኛ መሆኑን እያረጋገጠልን…
መንፈሳዊ ስጦታዎች 🔥🔥🔥🔥🔥🔥 ክፍል 40 ✍✍✍ መናፍስትን የመለየት ስጦታ 🗣🗣🗣🗣🗣🗣🗣🗣 መናፍስትን የመለየት ስጦታ በምድር የሚኖሩ ሰዎችን ከባህሪያቸውና ከድርጊቶቻቸው ተነስተን እንደምለየው የሰውን ውስጣዊ ማንነት በውስጣችን ባለው በሰው መንፈስ አማካኝነት እንደምናውቀው መንፈሳዊውም ዓለም በእግዚአብሄር መንፈስ የሚታወቅ የሚለይ ነው። መንፈሳዊው ዓለም በሁለት ይከፈላል።የእግዚአብሄር አለምና የዚህ ዓለም አምላክ የሆነው የክፋት ሰራዊቶች መንፈሳዊ አለም።የእግዚአብሄር መንፈስ የእግዚአብሄርን አለም ከክፋው ዓለም ለይተን የምናይበትን መንፈሳዊ ዓይን ሰጥቶናል። መናፍስትን መለየት ሲባል ዲያቢሎስ ያለበትን የዲያቢሎስ ስራ ብቻ ማየት ማለት አይደለም ልክ ነው የዲያቢሎስን ስራና አጋንት የተቆጣጠረውን ሰው መለየት አንዱ መናፍስትን መለየት ነው ዳሩ ግን ብቸኛ አገልግሎት አይደለም። መናፍስትን መለየት ማለት የእግዚአብሄርን መገኘት ስራውንና የእግዚአብሄር መንፈስ ያለበትን ከሌለበት መለየት የእግዚአብሄርን መላክና ራሱን የብርሃን መልአክ አድርጎ ከሚለውጠው ክፉ መለየት. መንፈስ ቅዱስ የሞላበትንና የክፉው የሞላበትን በንግግር በእይታ በልዮ ልዮ መንገድ መለየት ነው። መናፍስትን የመለየት ስጦታ ለቤተክርስቲያን እጅግ ጠቃሚ የሆነ ስጦታ ነው።መናፍስትን የሚለይ ሰው በቤተክርስቲያን ውስጥ ካለ በቤተክርስቲያን ውስጥ የኤልዛቤል መንፈስ መሰልጠን አይችልም።ነብይ ሳይሆኑ ነብይ ነን ሐዋሪያ ሳይሆኑ ሐዋሪያ ነን የሚሉ ሰዎች እንደ ልባቸው መፈንጨት አይችሉም። መናፍስትን የሚለዮ ሰዎች መርማሪዎች ወይም ፈታኞች ናቸው። በኤፌሶን ያለችው ቤተ ክርስቲያን የተመሰከረላት በዚህ ነው።“ሥራህን፣ ጥረትህንና ትዕግሥትህን ዐውቃለሁ። ክፉዎችንም ችላ ብለህ እንዳላለፍሃቸው፣ ሐዋርያት ሳይሆኑ ሐዋርያት ነን የሚሉትንም መርምረህ…
መንፈሳዊ ስጦታዎች ❤️🔥❤️🔥❤️🔥❤️🔥❤️🔥❤️🔥❤️🔥 ክፍል 38 ✍✍✍ የመፈወስ ስጦታ 🍁🍁🍁🍁🍁 የመፈወስ ስጦታ የመፈወስ ስጦታ በሶስት አይነት ሰዎች ላይ እንደሚገለጥ መፅሀፍ ቅዱስ ይናገራል።የመጀመሪያው በሁሉም አማኞች ላይ ሲሆን ለእምነታቸው እንደ ምልክት በእጆቻቸው ላይ ይፈፀማል።ማርቆስ 16 (አዲሱ መ.ት)¹⁷ የሚያምኑትን እነዚህ ምልክቶች ይከተሏቸዋል፤ በስሜ አጋንንትን ያወጣሉ፤ በአዲስ ልሳንም ይናገራሉ፤¹⁸ እባቦችን በእጃቸው ይይዛሉ፤ የሚገድል መርዝ ቢጠጡ እንኳ አይጐዳቸውም፤ እጃቸውንም በሕመምተኞች ላይ ይጭናሉ፤ እነርሱም ይፈወሳሉ።” ሁለተኛው ደግሞ ለቤተክርስቲያን ሽማግሌዎች የተሰጠ ሲሆን እነርሱም የታመመው ሰው ጋ በመሄድ በዘይት ሲፀልዮ የሚሆን የእምነት ፀሎት ሲሆን ይህም ለታመመው ፍፁም ፈውስን ያስገኝለታል። ያዕቆብ 5 (አዲሱ መ.ት)¹⁴ ከእናንተ መካከል የታመመ ሰው አለ? የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌዎችን ይጥራ፤ እነርሱም በጌታ ስም ዘይት ቀብተው ይጸልዩለት።¹⁵ በእምነት የቀረበ ጸሎት የታመመውን ሰው ይፈውሰዋል፤ ጌታም ያስነሣዋል፤ ኀጢአትም ሠርቶ ከሆነ፣ ይቅር ይባላል። ሶስተኛው ደግሞ ለክርስቶስ አካል ብልቶች እንዲታነፁበት መንፈስ ቅዱስ የሚሰጠው የመፈወስ ስጦታ ነው። '' ለአንዱም በአንዱ መንፈስ የመፈወስ ስጦታ”— 1ኛ ቆሮንቶስ 12፥9 የመፈወስ ስጦታ እንደሌሎቹ ስጦታዎች ሁሉ አንዱ መንፈስ ቅዱስ እንደ ወደደ ለወደደው ሰው የሚሰጠው ስጦታ ነው። የመፈወስ ስጦታ ደግሞ በተለያዮ ምክንያቶች መስራት ያቆሙ የሰውነት ክፍሎችን አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ ነው።ብልቶቻችን ታመሙ ሲባል መስራት አቆሙ ወይም ከአእምሮችን ጋር ግንኙነቱ ተቋርጧል ወይም በከፊል መስራት አቁሟል እንዳይሰራም የተጋረጠ ነገር አለ እንደ ማለት ነው። የሚሰራን የሰውነት ክፍል መልሶ እንዲሰራ ማድረግ…
መንፈሳዊ ስጦታዎች 🍁🍁🍁🌾🍁🍁🍁 ክፍል 36 ✍✍✍ ተዓምራት የማድረግ ስጦታ 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 ሐዋሪያት ተዓምራት ድንቆችና ምልክቶች ካልተደረጉ ብለው ፀልየው አያውቁም የሚፀልዮት አንድ ነገር ነው።የመጀመሪያው ቃሉን በግልጥ መናገር እንዲሰጣቸው ሲሆን ሁለተኛ ደግሞ እግዚአብሄር የሚሰብኩትን ብላቴና እንዲያከብር እጆቹንም በመዘርጋት ድንቆችን ተዓምራቶችንና ምልክቶችን በማድረግ አብሮአቸው እንዲሰራ ነው። ሐዋርያት 4 (አዲሱ መ.ት)²⁹ አሁንም ጌታ ሆይ፤ ዛቻቸውን ተመልከት፤ ባሪያዎችህም ቃልህን በፍጹም ድፍረት መናገር እንዲችሉ አድርጋቸው።³⁰ ለመፈወስ እጅህን ዘርጋ፤ በቅዱሱ ብላቴናህም በኢየሱስ ስም ድንቅና ታምራት አድርግ።” ሐዋሪያት ስጠን ብለው የሚለምኑት አለ ደግሞ እኛ እናድርግ ሳይሆን አድርግ ብለው እግዚአብሄርን የሚጠይቁት ጉዳይ አለ።ስለዚህም ቃሉን መስበክና የምትሰብኩት ቃል እንዲሰጣችሁ ቃሉንም በፍፁም ግልፅነት እንድትሰብኩ እንፀልይ ተዓምራት ድንቆችንና ምልክቶችን ግን እኛ እናድርግ ተብሎ አይፀለይም አንተ አድርግ ምክንያቱም እኛ ከእግዚአብሄር ጋር አብሮ ሰራተኞች ነን።ይህ ፀሎት መልስ ያገኘው ወዲያው ነበር።ወዲያው ያሉበት ስፍራ ተናወጠ መንፈስ ቅዱስን ተሞሉ ተዓምራት ግን አላደረጉም ያደረጉት ቃሉን መስበክ ነው ቃሉ ሲሰበክ ቃሉን የሚያፀናው ጌታ ነው ቃሉም የሚፀናው በተዓምራዊ ምልክት ነው። “ከጸለዩም በኋላ የነበሩበት ስፍራ ተናወጠ፤ ሁሉም በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ፤ የእግዚአብሔርንም ቃል በድፍረት ተናገሩ።” — ሐዋርያት 4፥31 (አዲሱ መ.ት) ቃሉን እንስበክ የቃሉ ባለቤት ቃሉን በምልክቶችና በተዓምራት ያፀናዋል። ኢየሱስ ወደ አባቱ ወደ አባታችን ሊያርግ ሲል ለሐዋሪያቱ የሰጠው አንድ ተልዕኮ ነው ይህውም ወንጌልን መስበክ ኢየሱስ ስበኩ አስተምሩ እያጠመቃችሁም ደቀ መዛሙርቴ አድርጉ ብሎ ብቻ…