Alif media
አንብብ { አንብቢ } ስታነብ ታሪክህን ታውቃለህ! ስታነብ የስኬት ማማ ላይ ትወጣለህ! ስታነብ ጉድለትህን ታውቃለህ!
Ko'proq ko'rsatish1 376
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-57 kunlar
-2130 kunlar
- Kanalning o'sishi
- Post qamrovi
- ER - jalb qilish nisbati
Ma'lumot yuklanmoqda...
Obunachilar o'sish tezligi
Ma'lumot yuklanmoqda...
Photo unavailableShow in Telegram
እንዲያው ለጨዋታ‼
===============
ጋዜጠኛ:—" የማውቅዎ ይመስለኛል"
አጎት ሃሰን:—" ይሆናል ለማንኛውም አጎት ሃሰን እባላለሁ"
ጋዜጠኛ:—" አጎት ሃሰን ሆይ! ስንት ሚስት አለዎት?"
አጎት ሃሰን:—" ፈጣሪየ ይመስገን አራት ናቸው"
ጋዜጠኛ:—" ለወንዶች ያለዎት ምክር ምንድን ነው?"
አጎት ሃሰን:—" ሶስትና አራት እንዲታገቡ"
ጋዜጠኛ:—" ለምን?"
አጎት ሃሰን:—" አየሽ! አራት ሚስት ያለው ሰው ማለት በሃይለኛ የገበያ ፉክክር ውስጥ እንዳሉ አራት የቴሌና መብራት ኃይል ኮርፖሬሽኖች ማለት ናቸው። ደንበኛቸውን ለማርካትና በገበያው ላይ ለመቆየት የማያደርጉት ነገር የለም"
ጋዜጠኛ:—" አንድ ሚስት ማለትስ?"
አጎት ሃሰን:—" አንድ ደካማ አገልግሎት ከሚያቀርብና በተደጋጋሚ ከሚቆራረጥ የቴሌ ወይም መብራት ኃይል ኮርፖሬሽን ጋር ልታመሳስይው ትችያለሽ የኔ ልጅ‼"
Copied
👏 3👍 2
Photo unavailableShow in Telegram
ኢና ሊላህ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን !
በማእከላዊ ጎንደር ደንቢያ ወረዳ አየንባ ቀበሌ የመስጅድ ኢማም የሆኑት ሸኽ ሲራጅ ተገደሉ!
...
(ሀሩን ሚዲያ፦ግንቦት 9/2016)
...
በማእከላዊ ጎንደር ደንቢያ ወረዳ አየንባ ቀበሌ የመስጂድ ኢማም የሆኑት ሸኽ ሲራጅ መግሪብ ሰላት ሰግደዉ ከመስጂድ ሲወጡ በታጣቂዎች ተይዘዉ ከሄዱ በሃላ በአሰቃቂ ሁኔታ በጥይት ደብድበዉ መገደላቸውን የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ዋና ፀሀፊ ገልፀዋል።
...
ሸኽ ሲራጅ በዛዉ መስጅ ለረጅም አመት ደረሳዎችን እስከዛሬዋ እለት ያቀሩ የነበሩ ሲሆን መግሪብን አሰግደዉ ሲወጡ ታጣቂዎቹ እየጎተቱ የወሰዷቸዉ መሆኑና ይህን የሀገር ሽማግሌ የሁሉ አባት የሆኑት የመስጅድ ታላቁን ሸኽ ገድለዉ ጥለዋቸዉ እንደሄዱ የክልሉ መጅሊስ ዋና ፀሀፊ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አስፍረዋል።
..
©ሀሩን ሚዲያ
አንተ ብቻ የኔ ጌታ
.
~ ሰዎች ሁሉ ይለፉኝ አንተ ግን እየኝ፡፡
~ ፍጥረታት ሁሉ ይርሱኝ አንተ ብቻ አስታውሰኝ፡፡
~ ህዝቦች ሁሉ ይዘንጉኝ አንተ ብቻ እወቀኝ፡፡
~ ፍጡራን ሁሉ ይጨክኑ አንተ ግን ራራልኝ፡፡
~ጌታዬ ሆይ! አንተ ከሆንክልኝ እኮ ሁሉም ነገር ሆነልኝ፡፡ አንተ ካልሆንክልኝ ግን አንድም ነገር አልሆነልኝ።
ሰባሐል ኸይር
በዚህ ሁኔታ ላይ ሆኜ ሞት የቀደመኝ እንደሆነ አቤቱ ጌታዬ ረሕመትህን እንጂ ምን ሥራ አለኝ.....
አብራሪው ማን እንደሆነ እንኳን ሳናውቅ አውሮፕላን ዉስጥ እንተኛለን፣ ዘዋሪዉን ሳናውቅ መርከብ ዉስጥ ለጥ ብለን እናንቀላፋለን።
ሕይወታችንን ማን እንደሚዘዉረው እያወቅን ተረጋግተን መኖርና መተኛት እንዴት ያቅተናል?።
Abx
አላህ ይሰጣል፣
አላህ ይነሳል።
አላህ ይወስዳል
አላህ ይክሳል።
አላህ ይሰብራል፣
አላህ ይጠግናል።
አንተን የሚያውቅ፣
ጉዳይህን የሚያውቅ፣
ሁኔታህን የሚያውቅ፣
ተጨባጭህን የሚያውቅ
ድክመት ጉድለትህን የሚያውቅ
አላህ ብቻ ነው።
ሁሌም አላህ አላህ በሉ
ከሥሞች ሁሉ መልካሙ አላህ ነውና።
https://t.me/Alif_media_1
Alif media
አንብብ { አንብቢ } ስታነብ ታሪክህን ታውቃለህ! ስታነብ የስኬት ማማ ላይ ትወጣለህ! ስታነብ ጉድለትህን ታውቃለህ!
የኦዳ ቡልቱም ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ ክብር ይገባቸዋል!!
ከላይ በምስሉ ላይ የሚታዬው አብርሐም የተባለ የሪሜድያል ተማሪ በቲክቶክ ስለ ቁርዓን ቁርዓን ላይ የሌለ ቃልን በመጠቀም በኦሮምኛ ቋንቋ ለ4 ደቂቃ የዘለቀ መልዕክት አስተላልፎ ነበር:: ከዚህ ክስተት ቡሃላ ጀመዓው ባደረገው እንቅስቃሴ ተማሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን ከዩኒቨርሲቲው ጋር በነበረ ንግግር ተማሪው ተማሪዎችን ወደ ሃይማኖት ግጭት ሊያስገባ የሚችል ንግግር በመናገር ወንጀል ተከሶ ለ2 አመት ከትምህርት እንዲታገድ ተወስኖበታል::
የኦዳቡልቱም ጀመዓ ስለ ትጋታችሁ ምስጋና ይገባችሗል:: የኦዳቡልቱም አካባቢ ፖሊስና የዩኒቨርሲቲው አካላት ስለ አፋጣኝ ምላሻችሁ ምስጋና ይገባችሗል::
@MohammadamminKassaw
👍 1
ወዳጄ!
አንዳንዴ ስላንተ መጥፎ በመጠርጠር ብቻ የተጠመዱ ሰዎችን ለማረምና እውነትህን ለማሳየት ብለህ ብዙ አትድከም፡፡
ተዋቸው ራሣቸዉን በልተው በልተው ይለቁ፡፡
ምክንያቱም ንጽሕናህን ለማሳየት በደከምክ ቁጥር ጥርጣሬያቸው እየጨመረ ይሄዳል፡፡
ለምን ካልክ በልባቸው ዉስጥ ትልቅ በሽታ አለ፡፡
ABX
https://t.me/Alif_media_1
Alif media
አንብብ { አንብቢ } ስታነብ ታሪክህን ታውቃለህ! ስታነብ የስኬት ማማ ላይ ትወጣለህ! ስታነብ ጉድለትህን ታውቃለህ!